en
Feedback
𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'

𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'

Open in Telegram

Philosophy | Orthodox Muslim | Theology

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
3 292
Subscribers
-124 hours
+147 days
+16030 days
Posts Archive
ዝም ብላችሁ ትመቹኛላችሁ። ☺️

እስኪ ዛሬ ሦስት ክርስቲያን አቃብያነ-እምነትን ያማከለ የውይይት ጥሪ እናቅርብ። በሰሞኑን እንግዲህ እነዚህ ልጆች በዚህ በዲጂታል ሚዲያ ወጥተው "ሙስሊሞች እኛ ፊት ቆመው አይወያዩም፣ ኧረ እንደውም
+2
እስኪ ዛሬ ሦስት ክርስቲያን አቃብያነ-እምነትን ያማከለ የውይይት ጥሪ እናቅርብ። በሰሞኑን እንግዲህ እነዚህ ልጆች በዚህ በዲጂታል ሚዲያ ወጥተው "ሙስሊሞች እኛ ፊት ቆመው አይወያዩም፣ ኧረ እንደውም ውይይት እንደ ጦር ነው የሚፈሩት" ያሉትንም አድምጫለሁ። እኔም ከዚህ ንግግራቸው በመነሳት ለነዚህ ልጆች በሚከተሉት ርዕሶች ዙሪያ የውይይት ጥሪ ላቅርብ፦ 1,​ነቢዩ ሙሐመድ በመጽሐፍ ቅዱስ 2, ​በኢየሱስ ስቅለት 3, ​ከኒቂያ በፊት የነበሩ አባቶች የኒቂያ ሥላሴን ያውቃሉን? ​እንግዲህ በእነዚህ አርእስቶች ዙሪያ የሚወያዩ ከሆነ መቀበላቸውን ሊያሳውቁኝ ይችላሉ፤ ማን ውይይትን እንደ ጦር እንደሚፈራ የምንመለከት ይሆናል።
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

ሁልጊዜ ይህንን ከተወዳጁ ኡስታዛችን የተሰጠኝን ማበረታቻ ስመለከት፣ በንጽጽር ጥናት ላይ ይበልጥ እንድሠራ እና ለላቀ ምርምርና ጥናት እንድነሳሳ ትልቅ የሞራል ስንቅና የውስጥ ብርታት ይሆነኛል። ☑️�
ሁልጊዜ ይህንን ከተወዳጁ ኡስታዛችን የተሰጠኝን ማበረታቻ ስመለከት፣ በንጽጽር ጥናት ላይ ይበልጥ እንድሠራ እና ለላቀ ምርምርና ጥናት እንድነሳሳ ትልቅ የሞራል ስንቅና የውስጥ ብርታት ይሆነኛል።
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

ቻሌንጁ (Challenge) ከተጀመረ ሁለት ቀን ሆኖታል፤ ኢብሮ ግን አሁንም እዚያው 400 ሺህ ቤት ነው ያለው። ወላሂ ይህ በጣም ያሳፍራል! ለመሆኑ ችግሩ ምንድን ነው? ሙስሊም በሀገሩ የለም ማለት
ቻሌንጁ (Challenge) ከተጀመረ ሁለት ቀን ሆኖታል፤ ኢብሮ ግን አሁንም እዚያው 400 ሺህ ቤት ነው ያለው። ወላሂ ይህ በጣም ያሳፍራል! ለመሆኑ ችግሩ ምንድን ነው? ሙስሊም በሀገሩ የለም ማለት ነው? ወይስ ወጥቶ ለሚጨፍርና ለሚዘፍን ብቻ ነው «ፎሎው» (Follow) እያደረገ የሚከታተለው? እኔ በበኩሌ በጣም አፍሬያለሁ፤ በእርግጥም ያሳፍራል። ​ቀን ከሌሊት ሳይታክተው በትጋት ለዲኑ የሚሠራን ሰው ለመደገፍና ለማጋራት የማንቸኩል ከሆነ፣ መቼ ነው ለዲናችን የምንቆመው? ራሳችን እንኳን በእርሱ ቦታ ሆነን ዲናችንን የማገልገል አቅምና ብርታቱ ባይኖረን፣ አቅሙና ወኔው ያለውን ሰው አንስበር!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

📢 Hmm... Are you guys ready for this? Goosebumps! ☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'👑 ➡️ https://t.me/Anas_Apologetics
📢 Hmm... Are you guys ready for this? Goosebumps!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

Well well well... በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው የኢብን ታይሚያህ ሴሪስ [Series] እጃችን ገብቷል! በዚሁ አጋጣሚ መጽሐፍቱን የላከችልን እህታችን፣ ክብረት ይስጥልኝ! ☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜ
Well well well... በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው የኢብን ታይሚያህ ሴሪስ [Series] እጃችን ገብቷል! በዚሁ አጋጣሚ መጽሐፍቱን የላከችልን እህታችን፣ ክብረት ይስጥልኝ!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

ቁርአን ✨ Bყ Ƴαɦყα
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ'👑

ቀኝህን በጥፊ ሲመቱህ ግራህን ስጠው' የሚለው የክርስቶስ አስተምህሮ፤ ዛሬ መኖሪያቸውን ከባሕር ማዶ አድርገው፣ በተደላደለ ሕይወት ውስጥ በሚኖሩ አንዳንድ ጽንፈኛ ሰባኪያን ዘንድ 'የይሁዳ አሳሳም' አካል ለብሶ በተግባር የተካደ ይመስላል። እነዚህ አካላት በራሱ በሕይወት ውጣ ውረድ የደከመውንና የቆሰለውን ሕዝባችንን "በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ" እንዲሉ ማብቂያ ወደሌለው የሃይማኖት ግጭትና እልቂት ለመክተት ቆርጠው የተነሱ ይመስላሉ። ​እነዚህ አካላት የፋኖን የትጥቅ ቡድን ዓላማና አሠራር አንግበው፣ በውስጣቸው ለዘመናት ተሰግስጎ የቆየውን ጥላቻ በተለያዩ የተፈጠሩ ትረካዎች እያነሳሱ፣ ወደ ከረረ ሁከት ለማምራት ዕቅድ ይዘዋል። ወጣቱን በመቀስቀስና በማሰማራት በንጹሃን ሕዝብ ላይ ጥቃት እንዲቃጣ እያደረጉ በመሆኑ፣ እያንዳንዱ ሙስሊም ኅብረተሰብ በከፍተኛ ንቃትና ጥንቃቄ ራሱንና ቤተሰቡን ከዚህ አደጋ ሊጠብቅ ይገባል። መንግሥት በተጨባጭ ወጥቶ በአካባቢው የተፈጸመውን ጥቃት የፈጸመው የሸኔ የሽብር ቡድን መሆኑን በግልጽ በተናገረበት አውድ ላይ፣ እነዚህ አካላት ጥፋቱን ወደ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በመጠምዘዝ ለመፈረጅ መሞከራቸው ምን የሚሉት አስተዋይነት ነው? ይህ ለዘመናት ውስጣቸውን ሲበላ የኖረውንና የሞተውን የአፄዎቹን አገዛዝ ሥርዓት ዳግም የማንገስ ፍላጎትና ስልታዊ ዓላማ መግለጫ ነው። (ይህ የአፄዎቹ አምባገነናዊ አገዛዝ ከሞተበት እንደማይነሳና ለዘላለሙ እንደተቀበረ የገባቸው አይመስልም!) ​እኛ ሙስሊሞች አስቀድመንም እንደተናገርነው፤ የንጹሃን ዜጎችን ሞትና ስቃይ በማንኛውም ወገን ይፈጸም በጥብቅ እናወግዛለን። በተለይ የገዛ የሀገሬ ልጅ ሲገደልና ሲበደል ማየት እጅግ ያመኛል፤ እኛ ሁላችን የአንድ እናት ልጆች ነንና፣ እማማ ኢትዮጵያ! ስለዚህ፣ ክርስቲያን ወገኖቼ ሆይ፤ የነዚህ የጥፋት ኃይሎች ሰለባ እንዳትሆኑ፣ በአጀንዳዎቻቸውም እንዳትታለሉ ሲል ወንድማዊ ምክሬን እለግሳችኋለሁ። በአክሱም ሙስሊሞችም ሆነ በአርሲ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸሙትን አሰቃቂ ግድያዎችና ጥቃቶች በሙሉ ያለምንም ልዩነት በጥብቅ እንቃወማለን፣ እናወግዛለን!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

ጥቅሙ ምንድን ነው?' ለምትሉት፤ በመጀመሪያ ደረጃ፣ መደበኛው ምእመን ትክክለኛውን ዕውቀት ከማን መቅሰም እንዳለበት በመጠቆም ረገድ ይህ ግምገማ መንገዱን በመጠረግ ሁነኛ ሚና ይጫወታል። ​ሲቀጥልም፣ በዚህ ግምገማ ውስጥ የሚያልፉት አካላት ያሉበትን የአቅምና የዕውቀት ደረጃ ቆም ብለው እንዲያሰላስሉ፣ እንዲሁም ደካማ ጎኖቻቸውን ፈትሸው ራሳቸውን እንዲያሻሽሉ በር ከፋች ነው! 2 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት...

በቅርቡ ሚዛናዊና ፍትሃዊ የሆነ የክርስቲያንና የሙስሊም አቃብያነ-እምነት [Apologists] ግምገማ በማድረግ፣ የደረጃ ሰንጠረዥ የምናስቀምጥ ይሆናል። እንግዲህ ይህ የደረጃ ሰንጠረዥ በዕውቀት ላይ ብቻ ያተኮረ የሚሆን ሲሆን፣ ዝነኝነትና ታዋቂነት ግን በመለኪያ መስፈርቱ ውስጥ በጭራሽ አይካተቱም። በመሆኑም፣ ይህ አካሄድ ልክ እንደ አክሱም ሐውልት ያለ ዕውቀት ወደ ላይ የተከመሩና በባዶ ዝና የተንጠለጠሉ አካላትን ማስቆጣቱ አይቀሬ ነው!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ

ሰሞኑን በአርሲ ዞን ውስጥ በክርስቲያን ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ዘግናኝ ግድያ በጥብቅ አወግዛለሁ። የአንድ ሀገር ልጆች ነንና የወገኖቻችን ሞት እጅግ ይከነክነኛል። ​እንዲህ ያሉት ጥቃቶችና ግድያዎች በሀገራችን ስፍራ እየቀያየሩ፣ አንዴ ከአርሲ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በትግራይ አክሱም ንጹሃን ሙስሊሞች ላይ እየተፈጸሙ ይገኛሉ። በንጹሃን ነፍስ ላይ የሚቃጡትን እነዚህን እኩይ ተግባራት ሁላችንም በአንድነትና በአንድ ድምፅ ልናወግዛቸው ይገባል!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

በቅርቡ... ከብዙ ዓመታት ጥልቅ ጥናትና ምርምር፣ ከረጅም ሰዓታት ንባብና ትንተና፣ ከብዙ ልፋት፣ ጥረትና ትጋት፣ ከእንቅልፍ አልባ ሌሊቶችና በድካም ከተሞሉ ቀናት በኋላ አንድ ታላቅ ሥራ ወደ እናንተ አፍጥጦና አግጥጦ እየመጣ ነው። ​ይህም አዲሱ መጽሐፋችን ነው። ከጥረት በኋላ ስኬት፣ ከድካም በኋላ ሐሴት የሚባለው ይሄው አይደለምን? ​ይህ ሥራ በዘርፉ ላይ ለብዙ ዓመታት ጥናትና ምርምር ሲያደርጉ በቆዩ በሦስት የሙስሊም አቃብያነ-እምነት (Apologists) የተዘጋጀ ሲሆን፣ እኔም ከእነዚህ አዘጋጆች መካከል አንዱ የመሆንን ክብር አግኝቻለሁ። ​መጽሐፉ በዋናነት የሚያጠነጥነውና ከርዕሱም መገንዘብ እንደሚቻለው፣ የታላቁ ስብዕና እና የሰው ልጆች አውራ የሆኑት ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ በቀደሙት መጻሕፍት ላይ ስለመምጣታቸው አስቀድሞ ነቢያት ትንቢት ተናግረዋል በሚለው መሠረታዊ ሐሳብ ላይ ነው። ​በዚህ ረድፍ ፈር ቀዳጅና ፋና ወጊ የሆኑት አንጋፋዎቹ የኢስላም አቃብያነ-እምነት (Apologists) እነ ሼክ አሕመድ ዲዳት እና ዶክተር ዛኪር ናይክ፣ ላለፉት አሥርት ዓመታት ጉዳዩን ለሰፊው ታዳሚ በተለያዩ መድረኮች አቅርበውታል። ሆኖም ግን፣ በክርስቲያን አቃብያነ-እምነት በኩል ላለፉት ዓመታት በርካታ የትችትና የቪቶ ምላሾች ሲሰነዘሩበት መቆየቱ ይታወቃል። እኛም እነሆ ከከዚህ ቀደሙ በተለየ መልኩ፣ አዳዲስ ምሁራዊ ግኝቶችንና መረጃዎችን ያካተተ አቀራረብ ይዘን ቀርበናል። ይበልጥ የሚያኮራው ደግሞ፣ በተለያዩ ጊዜያት በክርስቲያን ምሁራን በኩል ለሚነሱት ውስብስብ ጥያቄዎችና ትችቶች በማይናወጥ መረጃ ላይ ተመርኩዘን በውሉ መልስ የሰጠንበት መሆኑ ነው። በእውኑ ይህ 'የዘመናችን ተግዳሮታዊ መጽሐፍ' ቢባል እብለትም ሆነ ግነት የለበትም። ባጠቃላይ መጽሐፉ ምሁራዊ ደርዙንና ፈርጁን የጠበቀ ሲሆን፣ በውስጡም ከ400 በላይ የሚጠጉ ዋቢ መጻሕፍትን ያቀፈ፣ በይዘቱም በጥረቱም በእውነቱ ተወዳዳሪ የሌለው ትልቅ ሥራ ይዘን ቀርበናል። ለአንባቢ "እልል" የሚያስብል ነው። "ለመሆኑ የራስህ መጽሐፍ ስለሆነ ይሆን እንዴ እንዲህ የምታቆለጳጵሰው ?" የሚል ጥያቄ በአእምሯችሁ ብልጭ ይል ይሆናል። እርግጥ ነው፣ "ሰው ስለ ገዛ ሥራው አይመሰክርም" የሚለው ብሂል እኔንም ትንሽ ሞገት አድርጎኝ ነበር። ይሁን እንጂ ብትሉኝ እንኳ አይገደኝም፤ ምክንያቱም ምንም እንከን የማይወጣለትና በእውነት የሚያኮራ ሥራ ስለሆነ ነው። እንግዲህ ይህንን በራስ ሥራ መተማመን አድርጋችሁ ውሰዱት። ባጠቃላይ ይህ መጽሐፍ በቅርቡ እጃችሁ ላይ የሚገባ ይሆናል። ሁላችሁም በየዲጂታል ሚዲያ ገጾቻችሁና ፕሮፋይሎቻችሁ ላይ በማጋራት ይህንን መልካሙን ዜና ለወዳጅ ዘመዶቻችሁ (በተለይም እውነትን ለሚፈልጉ ክርስቲያን ወገኖቻችን) እያበሰራችሁ በጉጉት ጠብቁን። በሰላም ቆዩልን!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

እንዴት ናችሁ? እያነበባችሁ ነው? ጠቃሚና መሠረታዊ የጥናት ጽሑፍ ስለሆነች፣ እስቲ ገረፍ ገረፍ አድርጓት። ፈጣሪ ከፈቀደ፣ ነገ ታላቅ የምሥራች አለን። የቻናላችንን ሊንክ ለወዳጅ ዘመዶቻችሁ እያጋራችሁ፣ በጉጉት ጠብቁን። የነገ ሰው ይበለን! ለዛሬው መልካም የንባብ ጊዜ ይሁንላችሁ።

-وهي حفظ النفوس من الهلاك أو شدة الضرر إذ الضرورات تبيح المحظورات (إلا الآدمي) فلا يجوز أكله للضرورة لأن ميتته سم فلا تزيل الضرورة، وكذا الخمر لا يجوز تناوله الضرورة عطش لأنه مما يزيده
"እርሷም ነፍሳትን ከጥፋት ወይም ከባድ ጉዳት መጠበቅ ናት፤ ምክንያቱም አስገዳጅ ሁኔታዎች የተከለከሉ ነገሮችን ይፈቅዳሉና (ከሰው ልጅ በስተቀር)። በመሆኑም የሰው ልጅ በድን (ሬሳ) መርዛማ በመሆኑና አስገዳጅነቱን (አደጋውን) የማያስወግድ በመሆኑ፣ በአስገዳጅ ሁኔታ (በረሃብ አደጋ) ወቅት እንኳ የእርሱን ሥጋ መብላት አይፈቀድም። በተመሳሳይ መልኩ፣ ጠጅ (ኸምር) ጥማትን ይበልጥ የሚጨምርና የሚያባብስ በመሆኑ፣ በጥማት አስገዳጅነት ምክንያት እርሱን መጠጣት አይፈቀድም።" [بلغة السالك لأقرب المسالك الشيخ احمد الصاوي\١١٩]
-وكل ما حرم الله عز وجل من المأكل والمشارب من خنزير أو صيد حرام، أو ميتة، أو دم؛ أو لحم سبع طائر، أو ذي أربع ؛ أو حشرة، أو خمر، أو غير ذلك : فهو كله عند الضرورة حلال - حاشاً لحوم بني آدم - وما يقتل من تناوله - : فلا يحل من ذلك شيء أصلاً لا بضرورة ولا بغيرها
​"አላህ ከምግቦችና ከመጠጦች የከለከለው (የሐራም ያደረገው) ማናቸውም ነገር፤ እርሱም አሳማ፣ ወይም የተከለከለ አደን፣ ወይም በድን (ሬሳ)፣ ወይም ደም፣ ወይም የአዳኝ ወፍ ሥጋ፣ ወይም ባለ አራት እግር አዳኝ እንስሳ ሥጋ፣ ወይም ነፍሳት፣ ወይም ጠጅ (ኸምር)፣ ወይም ሌላም ቢሆን፦ ሁሉም በአስገዳጅ ሁኔታ (በደሩራህ) ወቅት ፍጹም የተፈቀደ (ሐላል) ይሆናል፣ ከሰው ልጅ ሥጋ (لحوم بني آدم) እና ከተመገቡት የሚገድል (መርዛማ) ነገር በስተቀር። ከተጠቀሱት ከእነዚህ ሁለት ነገሮች መካከል ማናቸውም ቢሆን፣ በአስገዳጅ ሁኔታም ሆነ በሌላ፣ በፍጹም እና በምንም ዓይነት ሁኔታ መፈቀጃ የለውም።" [المحلى بالآثار الإمام أبو محمد علي بن أحمد بن سعيد بن حزم الأندلسي\١٠٥] በአጠቃላይ ይህ ጉዳይ በእስልምና አስተምህሮ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የተወገዘ ነው፤ የሰው ልጅ በሕይወት እያለ ቀርቶ፣ ከህልፈቱ በኋላም ቢሆን አስከሬኑን መንካትና ሥጋውን መመገብ በጥብቅ የተከለከለ (ሐራም) ነው። ነጭ ይሁን ጥቁር፣ ፀይም ይሁን ቀይ፣ ረጅም ይሁን አጭር፣ አልፎ ተርፎም አማኝ ይሁን ኢ-አማኝ የሰው ልጅ በመሰረቱ በፈጣሪ ዘንድ የተከበረ ፍጡር ነው! በመሆኑም፣ የእርሱን ሥጋ መመገብ በማንኛውም ዓይነት አስጨናቂና "ነፍስ አውጪ ነፍስ አግኚ" በሆነ አስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ እንኳ ቢሆን፣ በሸሪዓው ፈጽሞ የሚፈቀድ አይደለም።
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics

እውን የሰው ሥጋ መብላት ይፈቀዳልን ? ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፣ አንዳንድ አካላት በዓለም ዙሪያ በከፍተኛ ሁኔታ ዕድገት እያሳየ ያለውን የእስልምና ሃይማኖታዊ ንቅናቄ ለመግታት የማይፈነቅሉት ድንጋይ፣ የማይንዱት ተራራ የለም። እንዲሁም ሃይማኖቱን ለማጠልሸት የማይጎነጉኑት የሴራ ድር የለም። በዚህም የጥላቻ ሂደታቸው፣ ያለ የሌለ አቅማቸውን አሟጠው በርካታ ሂሶችንና የፈጠራ ክሶችን በዚህ በዲጂታል ሚዲያ ላይ ሲሰነዝሩ እያደመጥን ነው። በሰሞነኛው የዲጂታል ሚዲያ ክትትላችን ካደመጥናቸው ክሶች መካከል፤ ያለ ምንም ሐፍረት አደባባይ ወጥተው፦ 'እስልምና የሰው ሥጋ መብላትን ይፈቅዳል' የሚል ድፍረት የተሞላበት የውሸት ወሬ ሲያናፍሱ ታዝበናል። ይባስ ብለውም፣ ሙስሊሞችም በላተ-ሰብ (Cannibals) ናቸው" እስከማለት ደርሰዋል። ለመሆኑ እነርሱ እንደሚሉት እስልምና የሰው ሥጋ መብላትን ይፈቅዳልን? ሙስሊሞችስ 'በላዕተ-ሰብ' (ሰው በላዎች) ናቸውን? እስኪ ይህንን እዚህ ግባ የማይባልና መሠረተ-ቢስ ክስ፣ የእስልምና መዛግብትን ገልብጠንና አገላብጠን በውሉ በመፈተሽ፣ እንዲሁም ጉዳዩን በአንክሮ በሚመረምሩት የጥንታውያን ሊቃውንቶቻችን ድርሳናት ላይ ተመርኩዘን፣ ጥርስና ምላሱን በጥሰን እያደማን በጥንቃቄ እንመርምረው፦ ​የሰው ልጅ በፈጣሪ መለኮታዊ አምሳል የተበጀ፣ አምላክም በሉዓላዊ ፈቃዱ ከአፈር አበጅቶ ሕያው ነፍስን የዘራበት ልዩ ፍጥረቱ ነው። የሰው ልጅ በዚች ረቂቅ ጥበብ በተዋቀረች ዓለም ውስጥ እንዲኖርና እንዲበለጽግ የተመረጠ የታላቁ ጥበበኛ እጅ-ሥራ ሲሆን፣ ይህንን ሕይወቱን ይመራ ዘንድም ሙሉ ፍላጎትና የማስተዋል ፀጋ ተሰጥቶታል። የዓለማት ጌታ የሰው ልጅን ከሌሎች እንስሳትና ግዑዛን ፍጥረታት ሁሉ በላይ አድርጎ፣ እጅግ የላቀ ክብርና ልዕልናን አጎናጽፎታል። ይህንኑ መሠረታዊ ሐቅ ፈጣሪ በተከበረው መለኮታዊ ቃሉ ውስጥ እንዲህ ሲል ያጸናዋል፦
« የአደምንም ልጆች በእርግጥ (ከሌላው ፍጡር) አከበርናቸው፡፡ በየብስና በባህርም አሳፈርናቸው፡፡ ከመልካሞችም (ሲሳዮች) ሰጠናቸው፡፡ ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጥናቸው፡፡» [ሱረቱ አል-ኢስራእ 17፥70]
​እዚህ ላይ የአጽናፈ ዓለሙ ፈጣሪ አላህ፦ «የአዳምንም ልጆች በእርግጥ [ከሌላው ፍጡር በላይ] አከበርናቸው...» (ሱራ 17:70) ሲል የተናገረውን መለኮታዊ ቃል ልብ በማለት እንጀምር። ይህ ቃል ቀደም ሲል የገለጽኩትን ሐቅ በተግባር የሚያረጋግጥ ነው። የሰው ልጅ ክቡር ነው፤ የሰው ልጅ የተከበረ ነው፤ አዎን፣ ከፍጥረታት ሁሉ በላይ የላቀ ልዕልና የተቸረው ፍጡር ነው! ታዲያ አምላክ ያከበረውንና የላቀ ደረጃ የሰጠውን የሰውን ልጅ፣ በየትኛው ቀመርና ስሌት፣ ቀምሮና አስቦ ነው ደፍሮ ሥጋውን ቀርጥፎ፣ አኝኮና አላምጦ መመገብ ይፈቀዳል የሚለው? ይህ የፈጠራ ክስ ከእስልምና መሠረታዊ አስተምህሮ እና ከፈጣሪ መለኮታዊ ቃል ጋር የሚጋጭ ነው። የሰው ልጅ ክቡር ነው ሲል አምላካችን፣ በሕይወት እያለም ሆነ ከሞተ በኋላ ሥጋውና አካሉ የተከበረ መሆኑን በማረጋገጥ ነው። ሊቃውንቶቻችንም ይህንን መለኮታዊ ድንጋጌ ሲያብራሩ በትክክል እንዲህ ነበር ያሉት፦
أَنَّ مِن إكرامِ بَنِي آدَمَ حماية جسدِه مِنَ الاعتداء حَيًّا ومَيَّتًا؛ فلا يُباحُ لأحدٍ أكله.
"የሰው ልጅን ማክበር ሲባል በሕይወት እያለም ሆነ ከሞተ በኋላ አካሉ ላይ ጥቃት እንዳይሰነዘርበት መጠበቅን ያካትታል፤ ስለሆነም የእርሱን ሥጋ መብላት ለማንም ቢሆን የተፈቀደ አይደለም።" ከዚህ በግልጽ መገንዘብ እንደሚቻለው፣ በእስልምና ይህ ዓይነቱ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት በጥብቅ የተወገዘ መሆኑን ነው። በተጨማሪም፣ ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ በአንድ ወቅት ያስተማሩት ትምህርት ይህንኑ እውነት የሚያጠናክር ነው። ነቢዩ እንዲህ ነበር ያሉት፦
أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ -صلى الله عليه وسلم - قَالَ: { كَسْرُ عَظْمِ الْمَيِّتِ كَكَسْرِهِ حَيًّا}
የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁንና) እንዲህ አሉ ፦ 'የሙትን አጥንት መስበር በሕይወት እያለ እንደ መስበር በትክክል እኩል ነው። [بلوغ المرام ٥٧٥] ሆኖም ግን፣ አንዳንድ የሕግ ሊቃውንት ከጠቅላላው ድንጋጌ ወጣ ባለ መልኩ፣ ለየት ያለና በጥንቃቄ ሊመረመር የሚገባው ምልከታ ይዘው ቀርበዋል። እነዚህ አካላት፣ ምንም እንኳ በመደበኛ ሁኔታ የሰው ሥጋ መብላት ፍጹም የተወገዘ ቢሆንም፣ አንድ ሰው በሕይወትና በሞት መካከል በሚያደርገው የህልውና ትግል (Extreme Necessity) ውስጥ ከወደቀ፣ ድርጊቱ በጥፋተኝነት አያስጠይቀውም የሚል የራሳቸውን የፊቅህ መላምት አስቀምጠዋል። «ጠጅ በብርሌ፣ ነገር በምሳሌ» ነውና፣ ሐሳቡን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ የሚከተለውን ክስተት ለአብነት እንጥቀስ፦ አንድ መንገደኛ በሰሃራ በረሃ ላይ በደረሰበት አደጋ ምክንያት በረሃብና በጥማት ለህልፈት የሚያደርስ አፋፍ ላይ ተገኘ እንበል። ይህ ሰው በሕይወትና በሞት መገናኛ መስመር ላይ ቆሞ፣ የሞት መልአክም ወደ እርሱ ቀርቦ ሞትን እያነፈነፈ ባለበት በዚያ አስጨናቂ ቅጽበት፣ ድንገት የአንድ የሞተ ሰው አስከሬን ቢያገኝና ሕይወቱን ለማዳን ብቻ ከዚያ ቢመገብ እንዴት ያስወቅሰዋል? የሚል ነው። ልክ የከርከሮ (የአሳማ) ሥጋ መብላት በነባራዊ ሁኔታው ክልክል (ሐራም) ቢሆንም፣ አንድ ሰው በዚህ ዓይነት የሞት አፋፍ ላይ ሆኖ የአሳማ ሥጋ ቢመገብ ወንጀል አንድማይሆንብት ሁሉ፣ ይህ የሰው ሥጋ ጉዳይም በተመሳሳይ የሕግ ሚዛን ላይ የቆመ ነው የሚል አቋም ነው። ​ይህ ዓይነቱ ምልከታ በጥቂት የሻፊዒይ መዝሃብ ሊቃውንት ዘንድ የተሰነዘረ የግል የፊቅህ መላምት (Interpretation) እንጂ፣ በፍጹም የጋራ ስምምነት ያለበት ድንጋጌ አይደለም። ይልቁኑ በሌሎቹ ሦስት ታላላቅ መዝሃቦች፣ ማለትም በማሊኪይ፣ በሐንበሊይ እና በሐነፊይ፣ አልፎ ተርፎም ከራሱ ከሻፊዒይ መዝሃብ አንጋፋ ሊቃውንት ሳይቀሩ በጥብቅ የተወገዘና ውድቅ የተደረገ አስተምሮ ነው። በዚያ ላይ ጉዳዩን በብዙ መንገዶች ስንቃኘውና ስንፈትሸው ሙሉ በሙሉ ስህተት መሆኑን እንገነዘባለን። በቅድሚያ፣ ይህ አካሄድ ከታላቁ ቁርዓንና ከነቢዩ ﷺ አስተምሮ ጋር በቀጥታ የሚጻረር፣ እንደ 'ጀርባና ሆድ' የተራራቀ ሐሳብ በመሆኑ በአጭሩ ሊወገዝ የሚገባው ነው። ​በሁለተኛ ደረጃ፣ ይህ አቋም በሊቃውንቱ አብላጫ ድምፅ (Majority)፣ ይልቁኑ በሊቃውንቱ አጠቃላይ ስምምነት (ኢጅማዕ - الإجماع) ደረጃ የተወገዘና ውድቅ የተደረገ በመሆኑ፣ በእስልምና የሕግ ሥርዓት ውስጥ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው አስተምሮ መሆኑን በድጋሚ ያረጋግጣል። ​በሦስተኛ ደረጃ፣ ጉዳዩ "አድ-ደሩራቱ ቱቢሑል መሕዙራት" (الضرورات تبيح المحظورات)ማለትም 'አስገዳጅ ሁኔታዎች የተከለከሉ ነገሮችን ይፈቅዳሉ' ከሚለው የታወቀው የፊቅህ መርህ መረብ ውጭ ነው። ምክንያቱም በሕክምናው ሳይንስ ዘርፍ እንደተረጋገጠው፣ የሰው ሥጋን መመገብ ነፍስን ሊያድን ቀርቶ፣ ለሌላ አስከፊ በሽታና ለከፋ ጉዳት የሚዳርግ በመሆኑ ነው። ይህንኑ እውነት ታላላቆቹ ሊቃውንቶቻችን በድርሳናቶቻቸው ላይ እንደሚከተለው በግልጽ አስፍረውታል፦

🎯 በቅድሚያ ሁላችሁም ወደዚህ ገጽ እንኳን ደህና መጣችሁ👋 ➖➖➖➖➖ ኢንሻአላህ በቅርቡ አስተማሪና ጠቃሚ የሆኑ አዳዲስ መጣጥፎችን ለእናንተ የምናጋራ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን። ​በተጨማሪም፣ የቻናሉን ሊንክ በግልም ሆነ በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችሁ ላይ በማጋራት ከጎናችን ለቆማችሁ መምህራን፣ ወንድሞችና እህቶች በሙሉ የላቀ ምስጋናዬን ከልብ አቀርባለሁ። እነሆ ይህንኑ ሰናይ ተግባራችሁን አሁንም ይፋዊ ድረ-ገጻችንን በማስተዋወቅ እንድትቀጥሉበት በአክብሮት እጠይቃለሁ፤ ክብረት ይስጥልኝ!
☑️𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ ᴬⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡️ https://t.me/Anas_Apologetics