uk
Feedback
𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'

𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'

ВіЎкрОтО в Telegram

Philosophy | Orthodox Muslim | Theology

ППказатО більше
КраїМа Ме вказаМаКатегПрія Ме вказаМа
3 292
ПіЎпОсМОкО
-124 гПЎОМО
+147 ЎМів
+16030 ЎеМь
Архів ЎПпОсів
ዝም ብላቜሁ ትመቹኛላቜሁ። ☺

እስኪ ዛሬ ሊስት ክርስቲያን አቃብያነ-እምነትን ያማኚለ ዚውይይት ጥሪ እናቅርብ። በሰሞኑን እንግዲህ እነዚህ ልጆቜ በዚህ በዲጂታል ሚዲያ ወጥተው "ሙስሊሞቜ እኛ ፊት ቆመው አይወያዩም፣ ኧሹ እንደውም
+2
እስኪ ዛሬ ሊስት ክርስቲያን አቃብያነ-እምነትን ያማኚለ ዚውይይት ጥሪ እናቅርብ። በሰሞኑን እንግዲህ እነዚህ ልጆቜ በዚህ በዲጂታል ሚዲያ ወጥተው "ሙስሊሞቜ እኛ ፊት ቆመው አይወያዩም፣ ኧሹ እንደውም ውይይት እንደ ጩር ነው ዚሚፈሩት" ያሉትንም አድምጫለሁ። እኔም ኹዚህ ንግግራ቞ው በመነሳት ለነዚህ ልጆቜ በሚኚተሉት ርዕሶቜ ዙሪያ ዚውይይት ጥሪ ላቅርብፊ 1,​ነቢዩ ሙሐመድ በመጜሐፍ ቅዱስ 2, ​በኢዚሱስ ስቅለት 3, ​ኚኒቂያ በፊት ዚነበሩ አባቶቜ ዚኒቂያ ሥላሎን ያውቃሉን? ​እንግዲህ በእነዚህ አርእስቶቜ ዙሪያ ዚሚወያዩ ኹሆነ መቀበላቾውን ሊያሳውቁኝ ይቜላሉፀ ማን ውይይትን እንደ ጩር እንደሚፈራ ዚምንመለኚት ይሆናል።
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

ሁልጊዜ ይህንን ኚተወዳጁ ኡስታዛቜን ዹተሰጠኝን ማበሚታቻ ስመለኚት፣ በንጜጜር ጥናት ላይ ይበልጥ እንድሠራ እና ለላቀ ምርምርና ጥናት እንድነሳሳ ትልቅ ዚሞራል ስንቅና ዚውስጥ ብርታት ይሆነኛል። ☑ᅵ
ሁልጊዜ ይህንን ኚተወዳጁ ኡስታዛቜን ዹተሰጠኝን ማበሚታቻ ስመለኚት፣ በንጜጜር ጥናት ላይ ይበልጥ እንድሠራ እና ለላቀ ምርምርና ጥናት እንድነሳሳ ትልቅ ዚሞራል ስንቅና ዚውስጥ ብርታት ይሆነኛል።
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

ቻሌንጁ (Challenge) ኹተጀመሹ ሁለት ቀን ሆኖታልፀ ኢብሮ ግን አሁንም እዚያው 400 ሺህ ቀት ነው ያለው። ወላሂ ይህ በጣም ያሳፍራል! ለመሆኑ ቜግሩ ምንድን ነው? ሙስሊም በሀገሩ ዹለም ማለት
ቻሌንጁ (Challenge) ኹተጀመሹ ሁለት ቀን ሆኖታልፀ ኢብሮ ግን አሁንም እዚያው 400 ሺህ ቀት ነው ያለው። ወላሂ ይህ በጣም ያሳፍራል! ለመሆኑ ቜግሩ ምንድን ነው? ሙስሊም በሀገሩ ዹለም ማለት ነው? ወይስ ወጥቶ ለሚጹፍርና ለሚዘፍን ብቻ ነው «ፎሎው» (Follow) እያደሚገ ዚሚኚታተለው? እኔ በበኩሌ በጣም አፍሬያለሁፀ በእርግጥም ያሳፍራል። ​ቀን ኚሌሊት ሳይታክተው በትጋት ለዲኑ ዚሚሠራን ሰው ለመደገፍና ለማጋራት ዚማን቞ኩል ኚሆነ፣ መቌ ነው ለዲናቜን ዹምንቆመው? ራሳቜን እንኳን በእርሱ ቊታ ሆነን ዲናቜንን ዹማገልገል አቅምና ብርታቱ ባይኖሚን፣ አቅሙና ወኔው ያለውን ሰው አንስበር!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

📢 Hmm... Are you guys ready for this? Goosebumps! ☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'👑 ➡ https://t.me/Anas_Apologetics
📢 Hmm... Are you guys ready for this? Goosebumps!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

Well well well... በጉጉት ስንጠብቀው ዹነበሹው ዚኢብን ታይሚያህ ሎሪስ [Series] እጃቜን ገብቷል! በዚሁ አጋጣሚ መጜሐፍቱን ዚላኚቜልን እህታቜን፣ ክብሚት ይስጥልኝ! ☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜ
Well well well... በጉጉት ስንጠብቀው ዹነበሹው ዚኢብን ታይሚያህ ሎሪስ [Series] እጃቜን ገብቷል! በዚሁ አጋጣሚ መጜሐፍቱን ዚላኚቜልን እህታቜን፣ ክብሚት ይስጥልኝ!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

ቁርአን ✹ Bყ ƳαɊყα
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ'👑

ቀኝህን በጥፊ ሲመቱህ ግራህን ስጠው' ዹሚለው ዚክርስቶስ አስተምህሮፀ ዛሬ መኖሪያ቞ውን ኚባሕር ማዶ አድርገው፣ በተደላደለ ሕይወት ውስጥ በሚኖሩ አንዳንድ ጜንፈኛ ሰባኪያን ዘንድ 'ዚይሁዳ አሳሳም' አካል ለብሶ በተግባር ዚተካደ ይመስላል። እነዚህ አካላት በራሱ በሕይወት ውጣ ውሚድ ዹደኹመውንና ዹቆሰለውን ሕዝባቜንን "በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ" እንዲሉ ማብቂያ ወደሌለው ዚሃይማኖት ግጭትና እልቂት ለመክተት ቆርጠው ዚተነሱ ይመስላሉ። ​እነዚህ አካላት ዹፋኖን ዚትጥቅ ቡድን ዓላማና አሠራር አንግበው፣ በውስጣ቞ው ለዘመናት ተሰግስጎ ዹቆዹውን ጥላቻ በተለያዩ ዚተፈጠሩ ትሚካዎቜ እያነሳሱ፣ ወደ ኹሹሹ ሁኚት ለማምራት ዕቅድ ይዘዋል። ወጣቱን በመቀስቀስና በማሰማራት በንጹሃን ሕዝብ ላይ ጥቃት እንዲቃጣ እያደሚጉ በመሆኑ፣ እያንዳንዱ ሙስሊም ኅብሚተሰብ በኹፍተኛ ንቃትና ጥንቃቄ ራሱንና ቀተሰቡን ኹዚህ አደጋ ሊጠብቅ ይገባል። መንግሥት በተጚባጭ ወጥቶ በአካባቢው ዹተፈጾመውን ጥቃት ዹፈጾመው ዹሾኔ ዚሜብር ቡድን መሆኑን በግልጜ በተናገሚበት አውድ ላይ፣ እነዚህ አካላት ጥፋቱን ወደ ሙስሊሙ ማኅበሚሰብ በመጠምዘዝ ለመፈሹጅ መሞኚራ቞ው ምን ዚሚሉት አስተዋይነት ነው? ይህ ለዘመናት ውስጣ቞ውን ሲበላ ዹኖሹውንና ዹሞተውን ዚአፄዎቹን አገዛዝ ሥርዓት ዳግም ዚማንገስ ፍላጎትና ስልታዊ ዓላማ መግለጫ ነው። (ይህ ዚአፄዎቹ አምባገነናዊ አገዛዝ ኚሞተበት እንደማይነሳና ለዘላለሙ እንደተቀበሚ ዚገባ቞ው አይመስልም!) ​እኛ ሙስሊሞቜ አስቀድመንም እንደተናገርነውፀ ዚንጹሃን ዜጎቜን ሞትና ስቃይ በማንኛውም ወገን ይፈጾም በጥብቅ እናወግዛለን። በተለይ ዹገዛ ዚሀገሬ ልጅ ሲገደልና ሲበደል ማዚት እጅግ ያመኛልፀ እኛ ሁላቜን ዚአንድ እናት ልጆቜ ነንና፣ እማማ ኢትዮጵያ! ስለዚህ፣ ክርስቲያን ወገኖቌ ሆይፀ ዹነዚህ ዚጥፋት ኃይሎቜ ሰለባ እንዳትሆኑ፣ በአጀንዳዎቻ቞ውም እንዳትታለሉ ሲል ወንድማዊ ምክሬን እለግሳቜኋለሁ። በአክሱም ሙስሊሞቜም ሆነ በአርሲ ክርስቲያኖቜ ላይ ዚተፈጞሙትን አሰቃቂ ግድያዎቜና ጥቃቶቜ በሙሉ ያለምንም ልዩነት በጥብቅ እንቃወማለን፣ እናወግዛለን!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

ጥቅሙ ምንድን ነው?' ለምትሉትፀ በመጀመሪያ ደሚጃ፣ መደበኛው ምእመን ትክክለኛውን ዕውቀት ኹማን መቅሰም እንዳለበት በመጠቆም ሚገድ ይህ ግምገማ መንገዱን በመጠሹግ ሁነኛ ሚና ይጫወታል። ​ሲቀጥልም፣ በዚህ ግምገማ ውስጥ ዚሚያልፉት አካላት ያሉበትን ዹአቅምና ዚዕውቀት ደሹጃ ቆም ብለው እንዲያሰላስሉ፣ እንዲሁም ደካማ ጎኖቻ቞ውን ፈትሞው ራሳ቞ውን እንዲያሻሜሉ በር ኚፋቜ ነው! 2 ደቂቃ ዹሚቆይ ፖስት...

በቅርቡ ሚዛናዊና ፍትሃዊ ዹሆነ ዚክርስቲያንና ዚሙስሊም አቃብያነ-እምነት [Apologists] ግምገማ በማድሚግ፣ ዹደሹጃ ሰንጠሚዥ ዚምናስቀምጥ ይሆናል። እንግዲህ ይህ ዹደሹጃ ሰንጠሚዥ በዕውቀት ላይ ብቻ ያተኮሚ ዹሚሆን ሲሆን፣ ዝነኝነትና ታዋቂነት ግን በመለኪያ መስፈርቱ ውስጥ በጭራሜ አይካተቱም። በመሆኑም፣ ይህ አካሄድ ልክ እንደ አክሱም ሐውልት ያለ ዕውቀት ወደ ላይ ዚተኚመሩና በባዶ ዝና ዹተንጠለጠሉ አካላትን ማስቆጣቱ አይቀሬ ነው!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ

ሰሞኑን በአርሲ ዞን ውስጥ በክርስቲያን ወገኖቻቜን ላይ ዹተፈጾመውን ዘግናኝ ግድያ በጥብቅ አወግዛለሁ። ዚአንድ ሀገር ልጆቜ ነንና ዚወገኖቻቜን ሞት እጅግ ይኚነክነኛል። ​እንዲህ ያሉት ጥቃቶቜና ግድያዎቜ በሀገራቜን ስፍራ እዚቀያዚሩ፣ አንዮ ኚአርሲ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በትግራይ አክሱም ንጹሃን ሙስሊሞቜ ላይ እዚተፈጞሙ ይገኛሉ። በንጹሃን ነፍስ ላይ ዚሚቃጡትን እነዚህን እኩይ ተግባራት ሁላቜንም በአንድነትና በአንድ ድምፅ ልናወግዛቾው ይገባል!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

በቅርቡ... ኚብዙ ዓመታት ጥልቅ ጥናትና ምርምር፣ ኹሹጅም ሰዓታት ንባብና ትንተና፣ ኚብዙ ልፋት፣ ጥሚትና ትጋት፣ ኚእንቅልፍ አልባ ሌሊቶቜና በድካም ኹተሞሉ ቀናት በኋላ አንድ ታላቅ ሥራ ወደ እናንተ አፍጥጊና አግጥጊ እዚመጣ ነው። ​ይህም አዲሱ መጜሐፋቜን ነው። ኚጥሚት በኋላ ስኬት፣ ኚድካም በኋላ ሐሎት ዚሚባለው ይሄው አይደለምን? ​ይህ ሥራ በዘርፉ ላይ ለብዙ ዓመታት ጥናትና ምርምር ሲያደርጉ በቆዩ በሊስት ዚሙስሊም አቃብያነ-እምነት (Apologists) ዹተዘጋጀ ሲሆን፣ እኔም ኚእነዚህ አዘጋጆቜ መካኚል አንዱ ዹመሆንን ክብር አግኝቻለሁ። ​መጜሐፉ በዋናነት ዚሚያጠነጥነውና ኚርዕሱም መገንዘብ እንደሚቻለው፣ ዚታላቁ ስብዕና እና ዹሰው ልጆቜ አውራ ዚሆኑት ነቢዩ ሙሐመድ ï·º በቀደሙት መጻሕፍት ላይ ስለመምጣታ቞ው አስቀድሞ ነቢያት ትንቢት ተናግሹዋል በሚለው መሠሚታዊ ሐሳብ ላይ ነው። ​በዚህ ሚድፍ ፈር ቀዳጅና ፋና ወጊ ዚሆኑት አንጋፋዎቹ ዚኢስላም አቃብያነ-እምነት (Apologists) እነ ሌክ አሕመድ ዲዳት እና ዶክተር ዛኪር ናይክ፣ ላለፉት አሥርት ዓመታት ጉዳዩን ለሰፊው ታዳሚ በተለያዩ መድሚኮቜ አቅርበውታል። ሆኖም ግን፣ በክርስቲያን አቃብያነ-እምነት በኩል ላለፉት ዓመታት በርካታ ዚትቜትና ዚቪቶ ምላሟቜ ሲሰነዘሩበት መቆዚቱ ይታወቃል። እኛም እነሆ ኹኹዚህ ቀደሙ በተለዹ መልኩ፣ አዳዲስ ምሁራዊ ግኝቶቜንና መሚጃዎቜን ያካተተ አቀራሚብ ይዘን ቀርበናል። ይበልጥ ዚሚያኮራው ደግሞ፣ በተለያዩ ጊዜያት በክርስቲያን ምሁራን በኩል ለሚነሱት ውስብስብ ጥያቄዎቜና ትቜቶቜ በማይናወጥ መሹጃ ላይ ተመርኩዘን በውሉ መልስ ዚሰጠንበት መሆኑ ነው። በእውኑ ይህ 'ዚዘመናቜን ተግዳሮታዊ መጜሐፍ' ቢባል እብለትም ሆነ ግነት ዚለበትም። ባጠቃላይ መጜሐፉ ምሁራዊ ደርዙንና ፈርጁን ዹጠበቀ ሲሆን፣ በውስጡም ኹ400 በላይ ዹሚጠጉ ዋቢ መጻሕፍትን ያቀፈ፣ በይዘቱም በጥሚቱም በእውነቱ ተወዳዳሪ ዹሌለው ትልቅ ሥራ ይዘን ቀርበናል። ለአንባቢ "እልል" ዚሚያስብል ነው። "ለመሆኑ ዚራስህ መጜሐፍ ስለሆነ ይሆን እንዎ እንዲህ ዚምታቆለጳጵሰው ?" ዹሚል ጥያቄ በአእምሯቜሁ ብልጭ ይል ይሆናል። እርግጥ ነው፣ "ሰው ስለ ገዛ ሥራው አይመሰክርም" ዹሚለው ብሂል እኔንም ትንሜ ሞገት አድርጎኝ ነበር። ይሁን እንጂ ብትሉኝ እንኳ አይገደኝምፀ ምክንያቱም ምንም እንኚን ዚማይወጣለትና በእውነት ዚሚያኮራ ሥራ ስለሆነ ነው። እንግዲህ ይህንን በራስ ሥራ መተማመን አድርጋቜሁ ውሰዱት። ባጠቃላይ ይህ መጜሐፍ በቅርቡ እጃቜሁ ላይ ዚሚገባ ይሆናል። ሁላቜሁም በዚዲጂታል ሚዲያ ገጟቻቜሁና ፕሮፋይሎቻቜሁ ላይ በማጋራት ይህንን መልካሙን ዜና ለወዳጅ ዘመዶቻቜሁ (በተለይም እውነትን ለሚፈልጉ ክርስቲያን ወገኖቻቜን) እያበሰራቜሁ በጉጉት ጠብቁን። በሰላም ቆዩልን!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

እንዎት ናቜሁ? እያነበባቜሁ ነው? ጠቃሚና መሠሚታዊ ዚጥናት ጜሑፍ ስለሆነቜ፣ እስቲ ገሹፍ ገሹፍ አድርጓት። ፈጣሪ ኚፈቀደ፣ ነገ ታላቅ ዚምሥራቜ አለን። ዚቻናላቜንን ሊንክ ለወዳጅ ዘመዶቻቜሁ እያጋራቜሁ፣ በጉጉት ጠብቁን። ዹነገ ሰው ይበለን! ለዛሬው መልካም ዚንባብ ጊዜ ይሁንላቜሁ።

-وهي حف؞ النفوس من الهلاك أو ؎دة الضرر إذ الضرورات تؚيح المح؞ورات (إلا الآدمي) فلا يجوز أكله للضرورة لأن ميتته سم فلا تزيل الضرورة، وكذا الخمر لا يجوز تناوله الضرورة عط؎ لأنه مما يزيده
"እርሷም ነፍሳትን ኚጥፋት ወይም ኚባድ ጉዳት መጠበቅ ናትፀ ምክንያቱም አስገዳጅ ሁኔታዎቜ ዹተኹለኹሉ ነገሮቜን ይፈቅዳሉና (ኹሰው ልጅ በስተቀር)። በመሆኑም ዹሰው ልጅ በድን (ሬሳ) መርዛማ በመሆኑና አስገዳጅነቱን (አደጋውን) ዚማያስወግድ በመሆኑ፣ በአስገዳጅ ሁኔታ (በሚሃብ አደጋ) ወቅት እንኳ ዚእርሱን ሥጋ መብላት አይፈቀድም። በተመሳሳይ መልኩ፣ ጠጅ (ኾምር) ጥማትን ይበልጥ ዹሚጹምርና ዚሚያባብስ በመሆኑ፣ በጥማት አስገዳጅነት ምክንያት እርሱን መጠጣት አይፈቀድም።" [ؚلغة السالك لأقرؚ المسالك ال؎يخ احمد الصاوي\١١٩]
-وكل ما حرم الله عز وجل من المأكل والم؎ارؚ من خنزير أو صيد حرام، أو ميتة، أو دم؛ أو لحم سؚع طا؊ر، أو ذي أرؚع ؛ أو ح؎رة، أو خمر، أو غير ذلك : فهو كله عند الضرورة حلال - حا؎اً لحوم ؚني آدم - وما يقتل من تناوله - : فلا يحل من ذلك ؎يء أصلاً لا ؚضرورة ولا ؚغيرها
​"አላህ ኚምግቊቜና ኚመጠጊቜ ዹኹለኹለው (ዚሐራም ያደሚገው) ማናቾውም ነገርፀ እርሱም አሳማ፣ ወይም ዹተኹለኹለ አደን፣ ወይም በድን (ሬሳ)፣ ወይም ደም፣ ወይም ዚአዳኝ ወፍ ሥጋ፣ ወይም ባለ አራት እግር አዳኝ እንስሳ ሥጋ፣ ወይም ነፍሳት፣ ወይም ጠጅ (ኾምር)፣ ወይም ሌላም ቢሆንፊ ሁሉም በአስገዳጅ ሁኔታ (በደሩራህ) ወቅት ፍጹም ዹተፈቀደ (ሐላል) ይሆናል፣ ኹሰው ልጅ ሥጋ (لحوم ؚني آدم) እና ኚተመገቡት ዚሚገድል (መርዛማ) ነገር በስተቀር። ኚተጠቀሱት ኚእነዚህ ሁለት ነገሮቜ መካኚል ማናቾውም ቢሆን፣ በአስገዳጅ ሁኔታም ሆነ በሌላ፣ በፍጹም እና በምንም ዓይነት ሁኔታ መፈቀጃ ዚለውም።" [المحلى ؚالآثار الإمام أؚو محمد علي ØšÙ† أحمد ØšÙ† سعيد ØšÙ† حزم الأندلسي\١٠٥] በአጠቃላይ ይህ ጉዳይ በእስልምና አስተምህሮ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ዹተወገዘ ነውፀ ዹሰው ልጅ በሕይወት እያለ ቀርቶ፣ ኚህልፈቱ በኋላም ቢሆን አስኚሬኑን መንካትና ሥጋውን መመገብ በጥብቅ ዹተኹለኹለ (ሐራም) ነው። ነጭ ይሁን ጥቁር፣ ፀይም ይሁን ቀይ፣ ሹጅም ይሁን አጭር፣ አልፎ ተርፎም አማኝ ይሁን ኢ-አማኝ ዹሰው ልጅ በመሰሚቱ በፈጣሪ ዘንድ ዹተኹበሹ ፍጡር ነው! በመሆኑም፣ ዚእርሱን ሥጋ መመገብ በማንኛውም ዓይነት አስጚናቂና "ነፍስ አውጪ ነፍስ አግኚ" በሆነ አስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ እንኳ ቢሆን፣ በሞሪዓው ፈጜሞ ዚሚፈቀድ አይደለም።
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics

እውን ዹሰው ሥጋ መብላት ይፈቀዳልን ? ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ፣ አንዳንድ አካላት በዓለም ዙሪያ በኹፍተኛ ሁኔታ ዕድገት እያሳዚ ያለውን ዚእስልምና ሃይማኖታዊ ንቅናቄ ለመግታት ዚማይፈነቅሉት ድንጋይ፣ ዚማይንዱት ተራራ ዚለም። እንዲሁም ሃይማኖቱን ለማጠልሞት ዚማይጎነጉኑት ዚሎራ ድር ዚለም። በዚህም ዚጥላቻ ሂደታ቞ው፣ ያለ ዹሌለ አቅማቾውን አሟጠው በርካታ ሂሶቜንና ዚፈጠራ ክሶቜን በዚህ በዲጂታል ሚዲያ ላይ ሲሰነዝሩ እያደመጥን ነው። በሰሞነኛው ዚዲጂታል ሚዲያ ክትትላቜን ካደመጥና቞ው ክሶቜ መካኚልፀ ያለ ምንም ሐፍሚት አደባባይ ወጥተውፊ 'እስልምና ዹሰው ሥጋ መብላትን ይፈቅዳል' ዹሚል ድፍሚት ዚተሞላበት ዚውሞት ወሬ ሲያናፍሱ ታዝበናል። ይባስ ብለውም፣ ሙስሊሞቜም በላተ-ሰብ (Cannibals) ናቾው" እስኚማለት ደርሰዋል። ለመሆኑ እነርሱ እንደሚሉት እስልምና ዹሰው ሥጋ መብላትን ይፈቅዳልን? ሙስሊሞቜስ 'በላዕተ-ሰብ' (ሰው በላዎቜ) ናቾውን? እስኪ ይህንን እዚህ ግባ ዚማይባልና መሠሹተ-ቢስ ክስ፣ ዚእስልምና መዛግብትን ገልብጠንና አገላብጠን በውሉ በመፈተሜ፣ እንዲሁም ጉዳዩን በአንክሮ በሚመሚምሩት ዚጥንታውያን ሊቃውንቶቻቜን ድርሳናት ላይ ተመርኩዘን፣ ጥርስና ምላሱን በጥሰን እያደማን በጥንቃቄ እንመርምሚውፊ ​ዹሰው ልጅ በፈጣሪ መለኮታዊ አምሳል ዚተበጀ፣ አምላክም በሉዓላዊ ፈቃዱ ኹአፈር አበጅቶ ሕያው ነፍስን ዚዘራበት ልዩ ፍጥሚቱ ነው። ዹሰው ልጅ በዚቜ ሹቂቅ ጥበብ በተዋቀሚቜ ዓለም ውስጥ እንዲኖርና እንዲበለጜግ ዹተመሹጠ ዚታላቁ ጥበበኛ እጅ-ሥራ ሲሆን፣ ይህንን ሕይወቱን ይመራ ዘንድም ሙሉ ፍላጎትና ዚማስተዋል ፀጋ ተሰጥቶታል። ዚዓለማት ጌታ ዹሰው ልጅን ኚሌሎቜ እንስሳትና ግዑዛን ፍጥሚታት ሁሉ በላይ አድርጎ፣ እጅግ ዹላቀ ክብርና ልዕልናን አጎናጜፎታል። ይህንኑ መሠሚታዊ ሐቅ ፈጣሪ በተኹበሹው መለኮታዊ ቃሉ ውስጥ እንዲህ ሲል ያጞናዋልፊ
« ዹአደምንም ልጆቜ በእርግጥ (ኹሌላው ፍጡር) አኚበርና቞ው፡፡ በዚብስና በባህርም አሳፈርና቞ው፡፡ ኚመልካሞቜም (ሲሳዮቜ) ሰጠና቞ው፡፡ ኹፈጠርናቾውም ፍጡሮቜ በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጥና቞ው፡፡» [ሱሚቱ አል-ኢስራእ 17፥70]
​እዚህ ላይ ዚአጜናፈ ዓለሙ ፈጣሪ አላህ፩ «ዚአዳምንም ልጆቜ በእርግጥ [ኹሌላው ፍጡር በላይ] አኹበርናቾው...» (ሱራ 17:70) ሲል ዹተናገሹውን መለኮታዊ ቃል ልብ በማለት እንጀምር። ይህ ቃል ቀደም ሲል ዚገለጜኩትን ሐቅ በተግባር ዚሚያሚጋግጥ ነው። ዹሰው ልጅ ክቡር ነውፀ ዹሰው ልጅ ዹተኹበሹ ነውፀ አዎን፣ ኚፍጥሚታት ሁሉ በላይ ዹላቀ ልዕልና ዹተቾሹው ፍጡር ነው! ታዲያ አምላክ ያኚበሚውንና ዹላቀ ደሹጃ ዹሰጠውን ዹሰውን ልጅ፣ በዚትኛው ቀመርና ስሌት፣ ቀምሮና አስቊ ነው ደፍሮ ሥጋውን ቀርጥፎ፣ አኝኮና አላምጩ መመገብ ይፈቀዳል ዹሚለው? ይህ ዚፈጠራ ክስ ኚእስልምና መሠሚታዊ አስተምህሮ እና ኚፈጣሪ መለኮታዊ ቃል ጋር ዹሚጋጭ ነው። ዹሰው ልጅ ክቡር ነው ሲል አምላካቜን፣ በሕይወት እያለም ሆነ ኹሞተ በኋላ ሥጋውና አካሉ ዹተኹበሹ መሆኑን በማሚጋገጥ ነው። ሊቃውንቶቻቜንም ይህንን መለኮታዊ ድንጋጌ ሲያብራሩ በትክክል እንዲህ ነበር ያሉትፊ
أَنَّ مِن إكرامِ َؚنِي آدَمَ حماية جسدِه مِنَ الاعتداء حَيًّا ومَيَّتًا؛ فلا يُؚاحُ لأحدٍ أكله.
"ዹሰው ልጅን ማክበር ሲባል በሕይወት እያለም ሆነ ኹሞተ በኋላ አካሉ ላይ ጥቃት እንዳይሰነዘርበት መጠበቅን ያካትታልፀ ስለሆነም ዚእርሱን ሥጋ መብላት ለማንም ቢሆን ዹተፈቀደ አይደለም።" ኹዚህ በግልጜ መገንዘብ እንደሚቻለው፣ በእስልምና ይህ ዓይነቱ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት በጥብቅ ዹተወገዘ መሆኑን ነው። በተጚማሪም፣ ነቢዩ ሙሐመድ ï·º በአንድ ወቅት ያስተማሩት ትምህርት ይህንኑ እውነት ዚሚያጠናክር ነው። ነቢዩ እንዲህ ነበር ያሉትፊ
أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ -صلى الله عليه وسلم - قَالَ: { كَسْرُ عَ؞ْمِ الْمَيِّتِ كَكَسْرِهِ حَيًّا}
ዹአላህ መልክተኛ (ዹአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳ቞ው ላይ ይሁንና) እንዲህ አሉ ፊ 'ዚሙትን አጥንት መስበር በሕይወት እያለ እንደ መስበር በትክክል እኩል ነው። [ؚلوغ المرام Ù¥Ù§Ù¥] ሆኖም ግን፣ አንዳንድ ዹሕግ ሊቃውንት ኹጠቅላላው ድንጋጌ ወጣ ባለ መልኩ፣ ለዚት ያለና በጥንቃቄ ሊመሹመር ዚሚገባው ምልኚታ ይዘው ቀርበዋል። እነዚህ አካላት፣ ምንም እንኳ በመደበኛ ሁኔታ ዹሰው ሥጋ መብላት ፍጹም ዹተወገዘ ቢሆንም፣ አንድ ሰው በሕይወትና በሞት መካኚል በሚያደርገው ዹህልውና ትግል (Extreme Necessity) ውስጥ ኚወደቀ፣ ድርጊቱ በጥፋተኝነት አያስጠይቀውም ዹሚል ዚራሳ቞ውን ዹፊቅህ መላምት አስቀምጠዋል። «ጠጅ በብርሌ፣ ነገር በምሳሌ» ነውና፣ ሐሳቡን ይበልጥ ግልጜ ለማድሚግ ዹሚኹተለውን ክስተት ለአብነት እንጥቀስፊ አንድ መንገደኛ በሰሃራ በሹሃ ላይ በደሚሰበት አደጋ ምክንያት በሚሃብና በጥማት ለህልፈት ዚሚያደርስ አፋፍ ላይ ተገኘ እንበል። ይህ ሰው በሕይወትና በሞት መገናኛ መስመር ላይ ቆሞ፣ ዚሞት መልአክም ወደ እርሱ ቀርቩ ሞትን እያነፈነፈ ባለበት በዚያ አስጚናቂ ቅጜበት፣ ድንገት ዚአንድ ዹሞተ ሰው አስኚሬን ቢያገኝና ሕይወቱን ለማዳን ብቻ ኚዚያ ቢመገብ እንዎት ያስወቅሰዋል? ዹሚል ነው። ልክ ዚኚርኚሮ (ዚአሳማ) ሥጋ መብላት በነባራዊ ሁኔታው ክልክል (ሐራም) ቢሆንም፣ አንድ ሰው በዚህ ዓይነት ዚሞት አፋፍ ላይ ሆኖ ዚአሳማ ሥጋ ቢመገብ ወንጀል አንድማይሆንብት ሁሉ፣ ይህ ዹሰው ሥጋ ጉዳይም በተመሳሳይ ዹሕግ ሚዛን ላይ ዹቆመ ነው ዹሚል አቋም ነው። ​ይህ ዓይነቱ ምልኚታ በጥቂት ዚሻፊዒይ መዝሃብ ሊቃውንት ዘንድ ዹተሰነዘሹ ዹግል ዹፊቅህ መላምት (Interpretation) እንጂ፣ በፍጹም ዚጋራ ስምምነት ያለበት ድንጋጌ አይደለም። ይልቁኑ በሌሎቹ ሊስት ታላላቅ መዝሃቊቜ፣ ማለትም በማሊኪይ፣ በሐንበሊይ እና በሐነፊይ፣ አልፎ ተርፎም ኚራሱ ኚሻፊዒይ መዝሃብ አንጋፋ ሊቃውንት ሳይቀሩ በጥብቅ ዹተወገዘና ውድቅ ዹተደሹገ አስተምሮ ነው። በዚያ ላይ ጉዳዩን በብዙ መንገዶቜ ስንቃኘውና ስንፈትሞው ሙሉ በሙሉ ስህተት መሆኑን እንገነዘባለን። በቅድሚያ፣ ይህ አካሄድ ኚታላቁ ቁርዓንና ኚነቢዩ ï·º አስተምሮ ጋር በቀጥታ ዚሚጻሚር፣ እንደ 'ጀርባና ሆድ' ዚተራራቀ ሐሳብ በመሆኑ በአጭሩ ሊወገዝ ዚሚገባው ነው። ​በሁለተኛ ደሚጃ፣ ይህ አቋም በሊቃውንቱ አብላጫ ድምፅ (Majority)፣ ይልቁኑ በሊቃውንቱ አጠቃላይ ስምምነት (ኢጅማዕ - الإجماع) ደሹጃ ዹተወገዘና ውድቅ ዹተደሹገ በመሆኑ፣ በእስልምና ዹሕግ ሥርዓት ውስጥ ፍጹም ተቀባይነት ዹሌለው አስተምሮ መሆኑን በድጋሚ ያሚጋግጣል። ​በሊስተኛ ደሚጃ፣ ጉዳዩ "አድ-ደሩራቱ ቱቢሑል መሕዙራት" (الضرورات تؚيح المح؞ورات)ማለትም 'አስገዳጅ ሁኔታዎቜ ዹተኹለኹሉ ነገሮቜን ይፈቅዳሉ' ኹሚለው ዚታወቀው ዹፊቅህ መርህ መሚብ ውጭ ነው። ምክንያቱም በሕክምናው ሳይንስ ዘርፍ እንደተሚጋገጠው፣ ዹሰው ሥጋን መመገብ ነፍስን ሊያድን ቀርቶ፣ ለሌላ አስኚፊ በሜታና ለኹፋ ጉዳት ዚሚዳርግ በመሆኑ ነው። ይህንኑ እውነት ታላላቆቹ ሊቃውንቶቻቜን በድርሳናቶቻ቞ው ላይ እንደሚኚተለው በግልጜ አስፍሚውታልፊ

🎯 በቅድሚያ ሁላቜሁም ወደዚህ ገጜ እንኳን ደህና መጣቜሁ👋 ➖➖➖➖➖ ኢንሻአላህ በቅርቡ አስተማሪና ጠቃሚ ዹሆኑ አዳዲስ መጣጥፎቜን ለእናንተ ዚምናጋራ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን። ​በተጚማሪም፣ ዚቻናሉን ሊንክ በግልም ሆነ በተለያዩ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ገጟቻቜሁ ላይ በማጋራት ኚጎናቜን ለቆማቜሁ መምህራን፣ ወንድሞቜና እህቶቜ በሙሉ ዹላቀ ምስጋናዬን ኚልብ አቀርባለሁ። እነሆ ይህንኑ ሰናይ ተግባራቜሁን አሁንም ይፋዊ ድሚ-ገጻቜንን በማስተዋወቅ እንድትቀጥሉበት በአክብሮት እጠይቃለሁፀ ክብሚት ይስጥልኝ!
☑𝐀ŋα𝐬 'ˢᶜʰᵒˡᵃˢᵗⁱᶜ Ꭼⁿˢʷᵉʳ' 👑
➡ https://t.me/Anas_Apologetics