Usmanic Islamic psychology/ ስለ ሰው ልቡና
Open in Telegram
በኢስላማዊ ሳይኮሎጂስት ኡስማን ሙስጠፋ የተመሠረተ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የሙስሊሞች የስነልቦና ህክምና The Virtual Center for Usmanic Islamic Psychology was founded by Usman Mustofa, a psychology student, researcher in Islamic psychology, and writer ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @usmanoman ላይ ያናግሩን።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
579
Subscribers
+424 hours
+487 days
+17930 days
Posts Archive
5,ተስፋ መቁረጥ ሲሰማን ይህን ዱአ በማለት የአላህ ምራቻ እንጠይቅ
اللهم إني أسألك رحمةً من عندك وعملًا صالحًا تقربني إليك.
አላህ ሆይ ምህረትህን እንዲሁም ወደ አንተ የምታቀርበኝን መልካም ስራ ትለግሰኝ ዘንድ እጠይቅሃለሁ።
የዚህ ዱአ ስነልቦናዊ ጠቀሜታዎች
- በጎ የማድረግ ሞራላችን ያነቃቃል
- በአላህ በመመራት እና በመመካት ውስጥ መስከን ውስጥ እንገባለን።
ፅሁፉን የማስገቢያ ጊዜ የመግሪብ አዛን ላይ ይጠናቀቃል። መሳተፍ የምትፈልጉ የቀሩትን ሰአታት ተጠቀሙበት።
ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ/ኢልመ- ነፍስ
ክፍል 4. አቅል
-ፊጥራ
-ነፍስ
-ሩህ
-አቅል/አይምሮ
-ቀልብ/ልብ
-ተዝኪየቱ ነፍስ/ራስን ከወንጀል ማፅዳት
ለዛሬ አቅልን በጣም በአጭሩ እናያለን ኢንሸአላህ!
አቅል ምንድነው?
የአቅል (عقل) (mind) ስርወ - ቃል መሠረተ ትርጉም መገንዘብ ፣ መረዳት ፣ ማወቅ የሚል ትርጉም አለው።
ይህ የሰው ልጅ በምክንያት/አምክንዮ የሚያስብበት ክፍል ሲሆን ፥ እውነትን ከውሸት የሚለይበት ፍጥረተ አለሙ የሚረዳበት እና የሚገነዘብበት የማስተዋያ ክፍሉ ነው።
አቅል እስካሁን ካየናቸው የሰው ልጅ መሰረታዊ የማንነት ክፍሎች አንዱ ሲሆን ስለራሱ ስለሰዎች እና ስለፈጣሪው በትክክል እና በጥራት እንዲያስብ የሚያደረገው መሣሪያ ነዉ
አቅል በኢስላሚክ ሳይኮሎጂ ጥናት ውስጥ
በኢስላሚክ/በኡስማኒክ ሳይኮሎጂ ውስጥ አቅል መስታወት ሆኖ ሰው አለምን የሚያይበት የመመልከቻ መነፅሩ ነወ።
በተለያዩ ምክንያቶች የእውነት እና የፍትህ ሚዛኑ የተዛባ አይምሮን እና በሀቅ ላይ ቆሞ በጥራት ህይወትን መገንዘብ ያቃተውን አይምሮ በማገዝ የሰዎችን የማመዛዘን ተፈጥሯዊ ማንነት የማስመለስ ህክምናዊ እና ስነዘዴያዊ መንገዶችን ይከተላል።
ኢስላማዊ ሳይኮሎጂ መፅሀፍ
አዘጋጅ እና ፀሀፊ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂስት ኡስማን ሙስጠፋ)
ኢንሻአላህ ይቀጥላል...
#2 ሽልማት የሚያስገኝ ሀሳብን በፅሁፍ የመግለፅ ውድድር
ርእስ እና የመወዳደሪያ መንገድ :- ምድር ላይ የሰው ልጅ ስለሚያጋጥመው ፈተና እና ተስፋ ከ 4-7 መስመር ባልበለጠ በጥሩ አገላለጽ እና ሳቢ የአፃፃፍ ስልት ኮሜንት መስጫው ላይ በማስቀመጥ ተወዳደሩ!
አሪፉ ፅሁፍ ታይቶ አሸናፊው ሽልማቱን ይወስዳል።ኢንሻአላህ!
ሽልማቱ:- የ ፍፁም ሰው ፍፁም ነብይ መፅሀፍ እና የሳምንታዊ 780 ሜ.ባ የኢንተርኔት ፖኬጅ
#ከኡስማኒክ_ኢስላሚክ_ሳይኮሎጂ
መልካም እድል!
ጥያቄ 3
ልማር ወይስ ላቁም?
እኔ የ18 ወጣት ስሆን ቀጣይ አመት የ 12ተኛ ክፍል ተፈታች ነኝ። ትምህርት የሚሆንልት አይነት ሰው ብሆንም ታላላቆቼ ተምረው ያሰቡትን ማሳካት አለመቻላቸውን ሳይ እና 'ትምህርት አያሳልፍልህም አርፈህ ተፍ ተፍ በል' የሚሉ መሰል ተደጋጋሚ ምክሮችን ስሰማ ተስፋ ስለቆረጥኩኝ።
የ ቀጣይ አመት የ12ተኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ወስጄ የትምህርት አለምን ልሰናበት ወይ? በሚል ጥያቄ ራሴን እያፋጠጥኩኝ አለው። እባክህን ለኔ እና ለመሰል ጓደኞቼ በትምህርት ጉዳይ ያለህን አቋም ብታሳውቀን። አመሠግናለሁ።
(መልስ እሰኪሰጥ ድረስ አስተያየታችሁን ታች አሰፍሩ)
-ናፍቆት'
ወዳለፈው ዘመን የሚጎትት የኋሊት ሀዲድ ነው። በትዝታ ተሳፍረን ትናንትናችንን ልንጎበኝ የምንሄድበት የምልሰት ኑሮ።
የናፍቆት ወላፈን በልጅነታችን ካለፍንባቸው መንገዶች ፣ ከወላጆቻችን አልባሳት ፣ ቤታችን ውስጥ ከቆመችው የዛፍ ጥላ ፣ ከእህት ወንድሞቻችን ድምፅ እየተነሳ ወደ ህሊናችን ይተናል።
ናፍቆት የሰው ልጆች የማያመልጡት ያለፈ ታሪካቸው ዶሴ ላይ የተፃፈ ሰቀቀን ፣ የትካዜ ሀገራቸው መሠደጃ ነው።
"መነገር ያለበት ሁሉ አስቀድሞ ተነግሯል። ግን ማንም ሰው ስለማያዳምጥ፣ ሁሉም ነገር እንደገና መነገር አለበት።"
- copy
ሂስድ/ምቀኝነት መንስኤዎች እና መዳኛዎቹ
መልስ/ ክፍል ሁለት (የማጠቃለያ መልስ)
የሰው ልጅ ትልቁ ፈተናው በነፍሱ ጉትጎታ ወንጀል ለመስራት ሲፈተን ባለው ትግል ውስጥ ነው።ይህን ሀሳብም ይበልጥ ግልፅ የሚያደርግ ዘውትር የምንሰማው ወይም የምንለው ግን ትርጉሙን ብዙም ያላስተዋልነው ታላቅ ዱአ አለ።
أعوذ بالله من شرور أنفسنا ومن سيئات أعمالنا
ትርጉሙም 'ከነፍሳችን ሸር እና ከመጥፎ ስራችን ውጤት ወይም ህይወታችን ላይ ከሚያስከትለው ተፅእኖ በአላህ እንጠብቃለን' ማለት ነው።
የሰው ልጅ ትልቁ ጀሀዱ/ትግሉ ከሌሎች ጋር አይደለም። ከውስጣዊ መሻቱ እና ከተፈጥሮው መጥፎ ዝንባሌ ጋር የሚያደርገው እንጂ።
ሰው በብስጭት ፣ በዝሙት በስርቆት እና በብዙ እኩይ የተግባር ዝንባሌዎች እንደሚፈተነው ሁላ በምቀኝነት/ሌሎችን በመመቅኘት ሊፈተን ይችላል።
እህቴም ያጋጠማት ተመሳሳይ የችግር አይነት ነው።ይህ በሽታም ነፍስን ሳያቋርጡ በመፈተሽ ፣ በማፅዳት ፣ እና በመመርመር ወደ አላህ በተውበት በመመላለስ የሚድን የልብ ህመም ነው።
እህቴ አንቺ የተፈተነሽበት ጉዳይ የአለምን ህዝብ እና የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ኡማ እየተገዳደረ ያለ የብዙ ቤተሰቦችን ህብረት የበጠሰ ለበርካታ ወንጀሎች መንስኤ በሆነው ነገር ነው።
እህት እህቷን በመመቀኝነት ምክንያት ጎድታለች ፣ እናት እና ልጅ በዚህ ምክንያት ተቆራርጠዋል ፣ ልጅ አባቱን ገድሎ ወደ ዘላለማዊ የህሊና ወህኒ እና ለምድር እስር ቤት ተዳርጓል ፣ ወንድም ወንድሙ ላይ ተነስቷል ጓደኛማችነት ፈርሷል።
የብዙ ሲህር የማድረግ መሠረታዊ መንስኤ ከስሩ ያልታከመ ምቀኝነት እንጂ ሌላ አይደለም። ቅናት የወለደው መጠላለፍ የሰው ልጆች የተተበተቡበት የፅልመት ድር ነው።
እንዳንቺ የነፍሱን እኩይ ባህሪ ለይቶ እና አውቆ ፣አምኖ የሚፀፀት ሰው ጥቂት ነው። ይልቅስ ራሱን በማፅደቅ እና ነፍሱን ከእንከን የጠራች አድርጎ የሌሎችን ጎዶሎ ለማየት ሁሉም በሚጥርበት አለም ያንቺ ራስን የመፈተሽ አቅም እና እንከንን ለራስ ሳያደሉ ከነፍስያ መንቀስ መቻል ትልቅ የሚደነቅ ባህሪ ስለሆነ ቀጥይበት ለማለት እወዳለሁ።
ለዛሬ ግን ለብዙ ቀናት ያንከባለልነውን ጥያቄ መፍትሔዎቹ ያልናቸውን የተወሰኑ ነጥቦች በመጥቀስ እናጠቃልላለን።
1ኛ, ይህ ስሜት ሲሰማሽ 'አኡዙቢላሂ ሚነሸይጧን ረጂም' (ከሰይጣን ተንኮል በአላህ እጠበቃለው) በማለት እኩይ የሆነውን የሰይጣን አላማ ቶሎ አክሽፊበት
2ኛ, እኛን ሊያስቀናን የሚችል ፀጋን ሰዎች ዘንድ ስናይ 'ማሻአላህ' ወይም 'ተባረከላህ' ማለት መርሳት የለብንም አላህ የተባረከ እና ብሩክ ነገሮችም በሙሉ ከሱ መገኘታቸውን እውቅና መስጠት እና የፀጋውን ምንጭ ወደሱ በመመለስ አስገኚውን ማክበር በማድነቅ እና በማመስገን ልብን በአላህ ውሳኔ ማረጋጋት ያስችላል ።
3ተኛ, ምንም ነገር ላንቺ ተፅፎልሽ የቀረ ወይም የሚቀር አለመኖሩን አስታውሺ በቀደር ያለሽን እምነት አዳብሪ።
4ተኛ, የዚችን አለም ማጣት እና ማግኘትም ፈተና ብቻ እንደሆኑ አውቀሽ የተመኘሽው ፀጋ ወዳንቺ ቢመጣ ምንአልባት ከአላህ ጎዳና የሚያርቅ እና ለሁለት አለም ኪሳራ ሊዳርግ በሚችል ፊትና ልትወድቂ ስለምትችይ አላህ ጠብቆሽ ሊሆን እንደሚችል በማስታወስ አላህን ማመስገን እና ውሳኔውን መውደድን ልመጂ።
5,ካንቺ በታች ያሉትን ሰዎች አስታውሺ። አንቺ ያለሽን ነገር ዘወትር እንዲያገኙ አላህን በሚማፀኑ ሰዎች እና አንቺ ያገኘሽውን ፀጋ ላንዳፍታ ቢያገኙ ትልቁ ህልማቸው እንደተሳካ በሚያልሙ ሚሊዮን የአለም ህዝቦች ጎን እራስሽን አስተያዪ።
6, ይህን ስሜት እንዲያጠፋልሽ አላህን በመጠየቅ በዱአ በርቺ።
7,የጠዋት እና የማታ አዝካሮችን አዘውትሪ። በተለይ ከሸር እና በሂስድ የሚታደጉትን ሁለቱን አያ አዘውትሪ :- ቁል አኡዙ ቢረቢናስ እና ቁልአኡዙ ቢረቢል ፈለቅ
✍️ ኡስማን ሙስጠፋ ከኡስማኒክ ሳይኮሎጂ።
ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @psychosman1 ላይ ያናግሩን
ከህመም እረፍት በኋላ በምን እንጀምር ? (ከ8 ሰአት በኋላ የምርጫ ፖሉ ይዘጋል)
ተጨንቃችሁ ለደወላችሁልኝ ለፃፋችሁልኝም እንዲሁም በድብቅ ዱአቹህ ላሰባችሁኝ በሙሉ በአላህ ስም ከልብ አመሠግናለሁ።
አሁን በተሻለ የጤንነት ደረጃ ላይ ስልምገኝ ጉዟችንን እንቀጥላለን።ኢንሻአላህ
እስከዛው ያለፋችሁን ከዚህ ውስጥ መርጣችሁ አንብቡ
(ኢልመ ነፍስን ጨምሮ በአደዲስ ፀሁፎች እመለሳለሁ ኢንሻአላህ )
ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ/ኢልመ- ነፍስ አጭር ፅሁፎች
ክፍል 1 ፊጥራ 👈
ክፍል 2. ነፍስ 👈
ክፍል 3. ሩህ
ሌሎች እስካሁን የተለቀቁ የቻናሉ ጠቃሚ ፅሁፎች
- የመፅሐፍ ሽያጭ
የስነልቦናጥያቄ ና መልሶች (case studies)
ጥያቄ 1
ሙስሊም የ 31 አመት ሴት ስሆን እስካሁን የትዳርን ወግ አላየሁም።
መልስ .1
መረጃዎች እንደሚያሳዩት በአለም አቀፍ ደረጃ የሴቶች የጋብቻ እድሜ ድሮ ከነበረበት በብዙ እጥፍ ከፍ ብሏል።
ጥያቄ ሁለት
አሰላሙአለይኩም እኔ የ 27 አመት ወጣት ወንድ ነኝ።በአንድ አሳሳቢ ነገር ተለክፍያለው።
መልስ ሁለት ክፍል 1
በአይን የሚገባው የዘመኑ አደገኛው እፅ (የፖርን ፊልም)
መልስ/ ክፍል ሁለት
ይህን የወንድማችንን ጥያቄ በሁለት ዙር እንድናየው ያስገደደን ነገር...
"በታመመኩኝ ጊዜ እሱ ይፈውሰኛል!"
እኔ የናንተ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂስት ከብዙ በጤና መንቀባረር እና መንደላቀቅ በኋላ ከህመም እንቅፋት ጠጠሯ አደናቀፈችኝ! 🥹😭
አልሃምዱሊላህ! 🙏
እመለሳለሁ! እስከዛው በዱአቹህ አትርሱኝ ሰላሙላሂ አለይኩም! ✨
+1
የሰው ልጅ ህይወት በብዙ የደሰታ እና የሀዘን ትዕይንት የተሞላ እስከ ሞት የተዘረጋ የእንቆቅልሽ መስመር ነው። ይህም የህይወት ታሪክ እህታችን ከዲያሪዋ (ከማስታወሻ ደብተሯ) ላይ የተወሰኑ መስመሮችን ከላከችልን የተወሰደ እና ለሰው እንዲጋራ የፈቀደችው ነው።
በተውበት/በንስሀ ውሀ ታጥበን ፣ በኢስቲግፋር ብርሀን የወንጀላችንን ትብታብ በጣጥሰን ፣ በአዝካር ጌጥ ደምቀን በሰለዋት ቁልፍ የህይወታችንን በር እንከፍታለን።
የሳምንታዊ የኢንተርኔት ጥቅል ተሻለሚ 🏅🏆
- ሀያት በድሩ - ከ አዲስ አበባ -
ቀድማ በመመለስ የሽልማቱ አሸናፊ መሆን ችላለች።
ሁላችሁም ስለተሳተፋችሁ ከልብ እናመሠግናለን።
ቀጣዩን ለማሸነፍ ዝግጁ ይሁኑ።
