የቀጠናው ተመልካች
Open in Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 332
Subscribers
+424 hours
-367 days
-7930 days
Posts Archive
4 333
+4
🇮🇷🇺🇸⚡️ኢራን፣ በሁሉም አቅጣጫ ወደ ኩዌት መተኳኮስ ጀምራለች።
በኩዌትም፣ በቀጥታ የመታችው የራዳር እና የHIMARS ሚሳዬል ሲስተሞች እንዳሉ በሚወጡ መረጃዎች እየተነገረ ነው። ተከታታይ ፍንዳታዎችም ጥቃቱን ተከትሎ ተሰምተዋል።
የኢራን የአየር ትራንስፖርት ባለሥልጣን በበኩሉ፣ የሀገሩ አየር ክልል ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ወስኗል።
የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች፣ ድልድዮች፣ አየር ማረፊያዎች እና ሌሎች መሠረተ ልማቶች፣ እስካሁን ባለው መረጃ፣ የአሜሪካ የጥቃት ሰለባ ሆነዋል።
በሁለቱም በኩል ውጊያውን የማቆም አዝማሚያ አይታይም።
4 333
🇮🇷🇺🇸⚡️ትራምፕ፣ በቀጣይ 'መሠረተ-ልማት ማፍረስ' የሚለውን ቃሉን ጠበቀ ይሆን?
ዛሬ ምሽቱን፣ በዚህች ሰዓት፣ የአሜሪካ ጦር ኃይሎች በኢራን ላይ ከፍተኛ ድብደባ እየፈጸሙ ናቸው።
እስከ አሁን ድረስ ከተመቱት መካከል፣ በሆርሞዝጋን እና በኮርስታን ክፍለ ሀገሮች የሚገኙ፣ ሁለት ቁልፍ ድልድዮች ይገኙበታል።
4 333
🇺🇦⚡️በዩክሬን፣ ዘለንስኪ በሕዝብ እና በጦሩ ዘንድ ድጋፍ የነበረውን የመከላከያ ሚኒስቴሩን ማንሳቱን በመቃወም፣ ሰልፎች ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ሲደረጉ ውለዋል።
ዘለንስኪ ወደ ሥልጣን ከመጣ ጀምሮ፣ እንዲህ ያለው ሰልፍ የመጀመሪ ነው ተብሏል።
የትናንቱን ክስተት ተከትሎ፣ በዩክሬን ፖለቲካዊ ውጥረቶች አይለዋል።
4 333
🇺🇸⚡️🇮🇷 የአሁኑን የCENTCOM መረጃ፣ ካስተዋላችሁ፣ ከሌላ ጊዜ የሚለየው፣ ጥቃቱ ያነጣጠረው 'በኢራን ወታደራዊ አቅም' ላይ ነው ማለቱ ነው። ይሄ አደገኛ መባባስ ያመጣል። እስከዛሬ የነበረው መግለጫ፣ 'የኢራንን በሆርሙዝ ላይ ያላትን አቅም' ለማዳከም የሚል ነበር፣ ጀልባዎችን፣ ድሮኖችን … ወደብ አካባቢ ያሉ ኢላማዎችን።
4 333
🇺🇸❌🇮🇷 - CENTCOM በኢራን 'ወታደራዊ አቅም' ላይ አዲስ ዙር ጥቃት መጀመሩን አስታውቋል። እስካሁን ድረስ፣ በደቡብ ኢራን ክፍለ ሀገሮች እና በሆርሙዝ ባሕር ላይ በኢራን ግዛት ውስጥ ፍንዳታዎች ተከስተዋል።
4 333
🇺🇦⚡️ዘሌንስኪ በዩናይትድ ስቴትስ እና በሌሎች በርካታ ሀገራት አምባሳደሮችን ለመተካት ማቀዱን አስታውቋል።
*-*-*-*-
እቺ ሰው በቃ፣ ምርጫ የለ ምን የለ፣ ዝ ብለሽ ኑሪ! ሆነች። ብራቦ!
"አተ ና እዚጋ፣ አቺ ሂጂ እዛ፣ ግብዳው፣ ቡና በወተት ቶሎ በል" እያለች … ኧረ ጎበዝ ናት እቺ ቅመም።
ነገሩ ውነቱን ነው፣ ምን ያደርጋል ምርጫ??? ምርጫ ለደላው ነው። ምርጫ ለሰለጠኑ ሀገሮች ነው፣ ለሀብታሞች ነው። ዩክሬንም የሰለጠነች ናት፣ ሀብታምም ናት፣ ግን ጦርነት ውስጥ ናት። ታድርግ?
ዩክሬን ከፍተኛ የፖለቲካ አጣብቂኝ ውስጥ ገብታለች። በጦር ሜዳ ሰራዊቷ ነገሩን ለውጦታል፣ ሩሲያን ማድከም ችለዋል፣ ዘልቀው ገብተው ማጥቃት ችለዋል። ግን፣ በፖለቲካው ዘርፍ፣ በፖለቲከኞቿ የስልጣን ሽኩቻ፣ የገነባችው ሊፈርስባት ይመስላል። አስታውሱ፣ ከጦርነቱ በፊት ዩክሬን ከአውሮፓ አሕጉር ካመት ዓመት፣ በሙስና አንደኛ ደረጃ ነበረች።
ይሄ ሁሉ ፑቲንንና ሩሲያን ይጠቅማል። ሊገለብጡኝ ይችላሉ ብሎ የፈራቸውን ይሆን እያስወገደ ያለው ዘለንስኪ?
4 333
+1
🇺🇦 የዩክሬን ብሔራዊ ባንክ፣ የአዲሱን 2,000 ሂሪቪንያ የባንክ ኖት ንድፍ፣ ሊለውጥ ነው መባሉ ተሰማ።
ምክንያቱም፣ ጥቅም ላይ የዋለው የጽሑፍ ቅርጽ የተፈጠረው፣ በሩሲያዊው ዲዛይነር አሌክሳንድራ ሆፍማን በመሆኑ ነው።
4 333
🇷🇺 የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደሮች በሩሲያ ላይ በ21ኛው የማዕቀብ ፓኬጅ ላይ ለመስማማት ያደረጉት ሙከራ፣ ሳይሳካ ቀርቷል።
ስምምነት ሳይኖር በመቅረቱም፣ ውይይቱ እስከሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ለሌላ ጊዜ ተላልፏል።
4 333
🇺🇦⚡️በዩክሬን፣ መከላከያ ሚኒስትሩ በዘለንስኪ መነሳቱን ተከትሎ፣ ቁጣው በከፍተኛ ሁኔታ፣ በጦሩና በሲቪሊያኑ ማሕበረሰብ ዘንድ፣ አይሏል።
ዛሬ፣ በተለያዩ የዩክሬን ከተሞች፣ የዘለንስኪን ውሳኔ በመቃወም ሰልፍ ለማድረግ ዝግጅት የጀመሩ እንዳሉ ሰምተናል።
ዘለንስኪ፣ እንደ ዩክሬን ምንጮች፣ እስካሁን ግልፅ ባልሆነ ምክኒያት፣ የመከላከያ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችንም አንስቷል። ይህን የዘለንስኪን ውሳኔ፣ "ለሩሲያ የተበረከተ ግልፅ ስጦታ" ሲሉ ኮንነውታል።
በምትኩ ወደ ስልጣን የመጣውንም የመከላከያ ሚንስቴር፣ ዩክሬነኛ የማያወራ የሞስኮ አሰት (ሰላይ)" ሲሉ ገልፀውታል።
በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ ታዋቂ የዩክሬን የጦሩ ቻናሎች እና በመሬት ያለው ሰራዊት በከፍተኛ ምሬትና ቁጣ እንዲሁም ውዥንብር ውስጥ ይገኛሉ።
4 333
🇸🇾🇺🇸 የሶሪያ ፕሬዝዳንት፣ አሕመድ አል ሻራ፣ "ከሶሪያ ግዛት የመውጣት ርዕስ ሲነሳ እስራኤል ድርድሩን አቋርጣለች" በማለት ለትራምፕ ተናግሯል። አክሎም፣ "ለመውጣት ፈቃደኛ እስካልሆኑ ድረስ፣ ለምን ከእነሱ ጋር ስምምነት እንፈርማለን?" ብሏል።
አል-ሻራ በተጨማሪም፣ እስራኤል ከሊባኖስ ከመውጣቷ በፊት ሂዝቦላህን ትጥቅ ማስፈታት እንደማይቻል ለትራምፕ አሳውቋል። "ሂዝቦላህን በግዳጅ ትጥቅ ማስፈታት ቀጠናውን ወደ ትርምስ ይገፋፋዋል"፣ ሲልም ተከራክሯል።
የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋንም እንዲሁ ለትራምፕ ተመሳሳይ አቋም ማስተላለፉ ይታወቃል። እስራኤል የቀጠናውን መረጋጋት እያዳከመች እና የኢራንን አጋሮች ለመቆጣጠር እንዳይቻል ማንኛውንም የፖለቲካ መንገድ እያደናቀፈች መሆኑን አፅንዖት ሰጥቶበታል።
4 333
🇺🇸🇮🇷 - ፕሬዝዳንት ትራምፕ-
ኢራን፣ በታህሳስ 2024 በእንቅልፋሙ "ፕሬዝዳንት" ጆ ባይደን ሥር፣ በስህተት ታስራ የነበረችውን አሜሪካዊት፣ ሀገሩን ለቅቃ እንድትወጣ ፈቅዳለች። እሷ አሁን ከኢራን ውጭ በደህና ትገኛለች፣ እና በጥሩ ሁኔታ ላይ ናት። ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ፣ ይህንን የኢራንን የበጎ ፈቃድ ምልክት ታደንቃለች! ፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ. ትራምፕትራምፒና ከጦርነቱ ማምለጫ፣ ለጊዜውም ቢሆን፣ ጥሩ ሰበብ አገኘ።
4 333
🇷🇺❌🇺🇦 የሩሲያ ትልቁ የሆነው፣ በኡራልስ የሚገኘው፣ ሳላቫት ፔትሮኬሚካል ኮምፕሌክስ፣ ትናንት ማክሰኞ፣ የዩክሬን ድሮኖች ያደረሱበትን ጥቃት ተከትሎ፣ ሥራውን አቁሟል - ሮይተርስ
4 333
+1
🇺🇦 ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ፣ ዛሬ ጠዋት፣ በዩክሬን ሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የነበረውን የመከላከያ ሚኒስቴሩን፣ Mykhailo Fedorovን በማባረሩ፣ በመንግሥቱ እና በጦር ሠራዊት ውስጥ ከፍተኛ መከፋፈል እና ሽኩቻ ተነስቷል።
እንደ KIYV INDEPENDENT እና The New York Times ዘገባ መሠረት፣ በጦሩ ውስጥ ያለው ሽኩቻ የቆየ ሲሆን፣ ሲብላላ መጥቶ፣ አሁን ከሚኒስትሩ መባረር ጋር፣ እንዳይባባስ ተፈርቷል።
በአንዳንድ የዩክሬን ከተሞች፣ ሕዝቡ የዘለንስኪን ውሳኔ በመቃወም ሰልፍ ለመውጣት እየተነጋገሩ ናቸው።
4 333
+1
🇺🇦 ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ፣ ዛሬ ጠዋት፣ በዩክሬን ሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የነበረውን የመከላከያ ሚኒስቴሩን በማባረሩ፣ በመንግሥቱ እና በጦር ሠራዊት ከፍተኛ መከፋፈል እና ሽኩቻ ተነስቷል።
በአንዳንድ የዩክሬን ከተሞች፣ ሕዝቡ የዘለንስኪን ውሳኔ በመቃወም ሰልፍ ለመውጣት እየተነጋገሩ ነው።
4 333
🇰🇼🇮🇷🇺🇸⚡️ኩዌት እና ባሕሬን ግዛታቸውን ለአሜሪካ ሰጥተው ኢራንን እያስመቱ ናቸው። በሌላ አባባል፣ ኢራንን እያጠቁ ያሉት ባሕሬንና ኩዌት ናቸው።
እነ ሳዑዲ፣ ኳታር እና ኤሜሬት፣ ለአሁን አርፈው ተቀምጠዋል። ግዛቶቻቸውን ለአሜሪካ ኢራን ላይ ጥቃት እንድትከፍት እያስጠቀሙ አይደሉም፣ ከመጀመሪያው ዙር ጦርነት ኢራን በአሳማሚ ቅጣት ትልቅ ትምህርት አስተምራቸዋለችና።
አሁን ለኢራን ያስቸገሩት እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ሁለቱ ሀገሮች ናቸው።
እንደ እኔ፣ ኢራን እነዚህን ሀገሮች በቶሎ አንድ ነገር ካላደረገቻቸው፣ አሜሪካ በእነሱ በኩል ትወራታለች።
ትውረራቸው ይሆን? የማይቻል አይደለም። በ91 ሳዳም ኩዌትን በሁለት ሰዓታት ኩዌትን መውረር ችሏል።
