የቀጠናው ተመልካች
Open in Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 318
Subscribers
-824 hours
-117 days
-8230 days
Posts Archive
4 316
🇮🇷🇺🇸⚡️ፕሬዚዳንት ትራምፕ ኢራንን በድጋሚ አሸንፈዋል!
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ምሽቱን ለአሜሪካ ሕዝብ፡
አሜሪካ በቅርቡ ከኢራን ጋር በተፈጠረው ግጭት ተጠቃሚ ትሆናለች - በጦር ሰራዊታችን ላይ ሪከርድ መጠን ኢንቨስት እያደረግን ነው፣ እና ዛሬ በዓለም ላይ በጣም ጠንካራው ወታደር አለን። በመጀመሪያው የስልጣን ዘመኔ ነው የገነባሁት፣ እና በሚያሳዝን ሁኔታ፣ አሁን ልንጠቀምበት እንገደዳለን። አሁን፣ በሚሊዮን የሚቆጠር በርሜል ዘይት ከቬንዙዌላ እየዛቅን ነው፣ አሸንፈናላ። በኢራን ውስጥም ትልቅ ድሎችን እያገኘን ነው፣ እና የዚህን የጉልበት ፍሬ በጣም እና በቅርቡ እናጣጥመዋለን።
4 316
🇮🇷⚡️🇧🇭/ 🇸🇦 ኢራን ባሕሬን እና ሳዑዲ አረቢያን የሚያገናኘውን የኪንግ ፋህድ ድልድይን ኢላማ አድርጋለች።
*-*-*-
ያነቡናል ማለት ነው? ይከታተሉናል እንዴ IRGCዎች? ሄደናል ማለት ነው ከሚጠበቀው በላይ፣ ኧረ ቀስ በል!
ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ፣ እረ ይሄ ድልድል ስንል ነበር። ተሰማን።
ድልድዩ ተቆረጠ ማለት ሳዑዲ ከባሕሬን ተቆረጠች ማለት ነው፣ ፓትሮል ነድታ በባሕሬን የውስጥ ጉዳይ እንደልቧ ጣልቃ አትገባም። ከዛ ኢራን ቀስ ብላ ባሕሬንን ታንቃታለች፣ ኳስ በመሬት ብላ።
4 316
🇮🇷🇺🇸⚡️ኢራን፣ በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ እና በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙትን የዶናልድ ትራምፕ ንብረቶችን፣ ለጥቃት ሕጋዊ ኢላማ አድርጋ አውጃለች፣ ሲል IRGC (እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጓዶች) በሰጠው መግለጫ ገልጿል። እነዚህም የሚከተሉትን ያካትታሉ ትራምፕ ኢንተርናሽናል ሆቴል እና ታወር (ዱባይ)፣ ትራምፕ ፕላዛ (ጂዳ) እና ትራምፕ ታወር (ሪያድ)።
4 316
🇮🇷🇺🇸⚡️ትናንት እንዳልኩት፣ ኢራን ቆርጦላት ባሕሬንን ወይም ኩዌትን (ሁለቱንም በሂደት) የማትወር ከሆነ፣ አዝናለሁ፣ ኢራንን በእነዚህ በሁለት ሀገሮች በኩል ትወራታለች።
ይቅደሙ ወይስ ይቀደሙ?
የሚወሯቸው ከሆነ፣ በቀጠናው የአሜሪካ የጀርባ አጥንት፣ ሙሉ በሙሉ ይሰበራል። የማይወሯቸው ከሆነ ግን፣ በእነዚህ ነጥብ በሚያክሉ ሀገሮች በኩል፣ ዘላለማቸው ሲደሙ ይኖራሉ።
ሁለቱንም ሀገሮች የምታዝበት አሜሪካ ነች፣ መሪዎቻቸው እና ሕዝባቸው ነገ ጠዋት ተነስተው 'አይ በቃ!' ቢሉ እንኳ፣ አይችሉም፣ ድምጣቸውንም፣ ኃይላቸውንም ተቀምተዋልና።
ስለዚህ፣ ያለው አማራጭ ወረራ ነው። የማይቻል አይደለም። ትናንት እንዳነሳሁት፣ ሳዳም ኩዌትን በሁለት ሰዓታት መውረር ችሏል።
ባሕሬኖች ሺዓ ስለሆኑ፣ ኢራኖች 'እንመጣለን' ቢሉ፣ ሕዝቡ እራሱ ከውስጥ ይነሳል።
4 316
+1
🇲🇾🇮🇱 የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስቴር አንዋር ኢብራሒም፡ በማሌዢያ የሚኖሩ እስራኤላዊያን ዜጎች እንደታወቁ፣ ያለ ምንም ቅድመ-ሁኔታ ወደ ሀገራቸው ይጠረዛሉ፣ ሲል አውጇል።
4 316
🇷🇺🇺🇦⚡️የዩክሬን የኔቶ ስፖንሰሮች ጥቁር ባሕርን ወደ ሩሲያ ሆርሙዝ ለመቀየር እየሞከሩ ናቸው።
የአሜሪካ ሚዲያዎችም፣ ዩክሬን በአዞቭ ባሕር ላይ የጀመረችውን የድሮን ዘመቻ በድል አድራጊነት እየዘገቡላት ነው። CNN "ሩሲያ ወደ ጥቁር ባሕር መግቢያ በር ላይ ያላት ቁጥጥር እየተንሸራተተ ነው" ሲል፣ እንደ Washington Post ዓይነቶቹ፣ ዩክሬን ክራይሚያን ለመቁረጥ እና የሩስያ መርከቦችን ለማደናቀፍ ያለመውን ጦርነቷን፣ "አስገራሚ ስኬት" እያሉ ይገልጹታል።
የዩክሬን ጦር፣ ሩሲያ ፔትሮሊየም ምርቶችን ለማጓጓዝ የምትጠቀምባቸውን፣ Shadow Fleet በመባል የሚጠራው አካል የሆኑትን፣ ከ100 በላይ መርከቦችን በአዞቭ ባሕር ውስጥ ኢላማ አድርጎ እንደመታና ብዙዎቹን እንዳይጓዙ አድርጎ እንደሰበረ ያወራል። "ይህ ገና ጅምር ነው" ብሏል።
4 316
+4
🇮🇷🇺🇸⚡️ኢራን፣ በሁሉም አቅጣጫ ወደ ኩዌት መተኳኮስ ጀምራለች።
በኩዌትም፣ በቀጥታ የመታችው የራዳር እና የHIMARS ሚሳዬል ሲስተሞች እንዳሉ በሚወጡ መረጃዎች እየተነገረ ነው። ተከታታይ ፍንዳታዎችም ጥቃቱን ተከትሎ ተሰምተዋል።
የኢራን የአየር ትራንስፖርት ባለሥልጣን በበኩሉ፣ የሀገሩ አየር ክልል ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ወስኗል።
የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች፣ ድልድዮች፣ አየር ማረፊያዎች እና ሌሎች መሠረተ ልማቶች፣ እስካሁን ባለው መረጃ፣ የአሜሪካ የጥቃት ሰለባ ሆነዋል።
በሁለቱም በኩል ውጊያውን የማቆም አዝማሚያ አይታይም።
4 316
🇮🇷🇺🇸⚡️ትራምፕ፣ በቀጣይ 'መሠረተ-ልማት ማፍረስ' የሚለውን ቃሉን ጠበቀ ይሆን?
ዛሬ ምሽቱን፣ በዚህች ሰዓት፣ የአሜሪካ ጦር ኃይሎች በኢራን ላይ ከፍተኛ ድብደባ እየፈጸሙ ናቸው።
እስከ አሁን ድረስ ከተመቱት መካከል፣ በሆርሞዝጋን እና በኮርስታን ክፍለ ሀገሮች የሚገኙ፣ ሁለት ቁልፍ ድልድዮች ይገኙበታል።
4 316
🇺🇦⚡️በዩክሬን፣ ዘለንስኪ በሕዝብ እና በጦሩ ዘንድ ድጋፍ የነበረውን የመከላከያ ሚኒስቴሩን ማንሳቱን በመቃወም፣ ሰልፎች ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ሲደረጉ ውለዋል።
ዘለንስኪ ወደ ሥልጣን ከመጣ ጀምሮ፣ እንዲህ ያለው ሰልፍ የመጀመሪ ነው ተብሏል።
የትናንቱን ክስተት ተከትሎ፣ በዩክሬን ፖለቲካዊ ውጥረቶች አይለዋል።
4 316
🇺🇸⚡️🇮🇷 የአሁኑን የCENTCOM መረጃ፣ ካስተዋላችሁ፣ ከሌላ ጊዜ የሚለየው፣ ጥቃቱ ያነጣጠረው 'በኢራን ወታደራዊ አቅም' ላይ ነው ማለቱ ነው። ይሄ አደገኛ መባባስ ያመጣል። እስከዛሬ የነበረው መግለጫ፣ 'የኢራንን በሆርሙዝ ላይ ያላትን አቅም' ለማዳከም የሚል ነበር፣ ጀልባዎችን፣ ድሮኖችን … ወደብ አካባቢ ያሉ ኢላማዎችን።
4 316
🇺🇸❌🇮🇷 - CENTCOM በኢራን 'ወታደራዊ አቅም' ላይ አዲስ ዙር ጥቃት መጀመሩን አስታውቋል። እስካሁን ድረስ፣ በደቡብ ኢራን ክፍለ ሀገሮች እና በሆርሙዝ ባሕር ላይ በኢራን ግዛት ውስጥ ፍንዳታዎች ተከስተዋል።
4 316
🇺🇦⚡️ዘሌንስኪ በዩናይትድ ስቴትስ እና በሌሎች በርካታ ሀገራት አምባሳደሮችን ለመተካት ማቀዱን አስታውቋል።
*-*-*-*-
እቺ ሰው በቃ፣ ምርጫ የለ ምን የለ፣ ዝ ብለሽ ኑሪ! ሆነች። ብራቦ!
"አተ ና እዚጋ፣ አቺ ሂጂ እዛ፣ ግብዳው፣ ቡና በወተት ቶሎ በል" እያለች … ኧረ ጎበዝ ናት እቺ ቅመም።
ነገሩ ውነቱን ነው፣ ምን ያደርጋል ምርጫ??? ምርጫ ለደላው ነው። ምርጫ ለሰለጠኑ ሀገሮች ነው፣ ለሀብታሞች ነው። ዩክሬንም የሰለጠነች ናት፣ ሀብታምም ናት፣ ግን ጦርነት ውስጥ ናት። ታድርግ?
ዩክሬን ከፍተኛ የፖለቲካ አጣብቂኝ ውስጥ ገብታለች። በጦር ሜዳ ሰራዊቷ ነገሩን ለውጦታል፣ ሩሲያን ማድከም ችለዋል፣ ዘልቀው ገብተው ማጥቃት ችለዋል። ግን፣ በፖለቲካው ዘርፍ፣ በፖለቲከኞቿ የስልጣን ሽኩቻ፣ የገነባችው ሊፈርስባት ይመስላል። አስታውሱ፣ ከጦርነቱ በፊት ዩክሬን ከአውሮፓ አሕጉር ካመት ዓመት፣ በሙስና አንደኛ ደረጃ ነበረች።
ይሄ ሁሉ ፑቲንንና ሩሲያን ይጠቅማል። ሊገለብጡኝ ይችላሉ ብሎ የፈራቸውን ይሆን እያስወገደ ያለው ዘለንስኪ?
4 316
+1
🇺🇦 የዩክሬን ብሔራዊ ባንክ፣ የአዲሱን 2,000 ሂሪቪንያ የባንክ ኖት ንድፍ፣ ሊለውጥ ነው መባሉ ተሰማ።
ምክንያቱም፣ ጥቅም ላይ የዋለው የጽሑፍ ቅርጽ የተፈጠረው፣ በሩሲያዊው ዲዛይነር አሌክሳንድራ ሆፍማን በመሆኑ ነው።
4 316
🇷🇺 የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደሮች በሩሲያ ላይ በ21ኛው የማዕቀብ ፓኬጅ ላይ ለመስማማት ያደረጉት ሙከራ፣ ሳይሳካ ቀርቷል።
ስምምነት ሳይኖር በመቅረቱም፣ ውይይቱ እስከሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ለሌላ ጊዜ ተላልፏል።
4 316
🇺🇦⚡️በዩክሬን፣ መከላከያ ሚኒስትሩ በዘለንስኪ መነሳቱን ተከትሎ፣ ቁጣው በከፍተኛ ሁኔታ፣ በጦሩና በሲቪሊያኑ ማሕበረሰብ ዘንድ፣ አይሏል።
ዛሬ፣ በተለያዩ የዩክሬን ከተሞች፣ የዘለንስኪን ውሳኔ በመቃወም ሰልፍ ለማድረግ ዝግጅት የጀመሩ እንዳሉ ሰምተናል።
ዘለንስኪ፣ እንደ ዩክሬን ምንጮች፣ እስካሁን ግልፅ ባልሆነ ምክኒያት፣ የመከላከያ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችንም አንስቷል። ይህን የዘለንስኪን ውሳኔ፣ "ለሩሲያ የተበረከተ ግልፅ ስጦታ" ሲሉ ኮንነውታል።
በምትኩ ወደ ስልጣን የመጣውንም የመከላከያ ሚንስቴር፣ ዩክሬነኛ የማያወራ የሞስኮ አሰት (ሰላይ)" ሲሉ ገልፀውታል።
በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ ታዋቂ የዩክሬን የጦሩ ቻናሎች እና በመሬት ያለው ሰራዊት በከፍተኛ ምሬትና ቁጣ እንዲሁም ውዥንብር ውስጥ ይገኛሉ።
4 316
🇸🇾🇺🇸 የሶሪያ ፕሬዝዳንት፣ አሕመድ አል ሻራ፣ "ከሶሪያ ግዛት የመውጣት ርዕስ ሲነሳ እስራኤል ድርድሩን አቋርጣለች" በማለት ለትራምፕ ተናግሯል። አክሎም፣ "ለመውጣት ፈቃደኛ እስካልሆኑ ድረስ፣ ለምን ከእነሱ ጋር ስምምነት እንፈርማለን?" ብሏል።
አል-ሻራ በተጨማሪም፣ እስራኤል ከሊባኖስ ከመውጣቷ በፊት ሂዝቦላህን ትጥቅ ማስፈታት እንደማይቻል ለትራምፕ አሳውቋል። "ሂዝቦላህን በግዳጅ ትጥቅ ማስፈታት ቀጠናውን ወደ ትርምስ ይገፋፋዋል"፣ ሲልም ተከራክሯል።
የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋንም እንዲሁ ለትራምፕ ተመሳሳይ አቋም ማስተላለፉ ይታወቃል። እስራኤል የቀጠናውን መረጋጋት እያዳከመች እና የኢራንን አጋሮች ለመቆጣጠር እንዳይቻል ማንኛውንም የፖለቲካ መንገድ እያደናቀፈች መሆኑን አፅንዖት ሰጥቶበታል።
