en
Feedback
​🌹قَـــنَـــاةُ بِـــنـــتْ مُـــحَـــمَّـــد 🌹

​🌹قَـــنَـــاةُ بِـــنـــتْ مُـــحَـــمَّـــد 🌹

Closed channel

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
546
Subscribers
-224 hours
+177 days
+5730 days
Posts Archive
« እህቴ ለማንም ብለሽ ሳይሆን ለራስሽ ስትይ መጠንከርን ተለማመጅ የትኛውም ቦታ ደካሞችን አይቀበልም! ማንም ሰዉ ከወደቅሽበት እንዲያነሳሽ ህመምሽን እንዲታመምልሽ አይዞሽ እንዲልሽ መንገድ እንዲመራሽ
« እህቴ ለማንም ብለሽ ሳይሆን ለራስሽ ስትይ መጠንከርን ተለማመጅ የትኛውም ቦታ ደካሞችን አይቀበልም!  ማንም ሰዉ ከወደቅሽበት እንዲያነሳሽ ህመምሽን እንዲታመምልሽ አይዞሽ እንዲልሽ መንገድ እንዲመራሽ አትጠብቂ ! ከሰዉ ብዙ መጠበቅ ትርፉ ህመም ነዉ። «አስታዉሺ ለራስሽ ያለሽዉ ራስሽ ነሽ መንገድሽን ጀምሪ ማንም የአላህ በር ሊዘጋብሽ አይችልምና በጌታሽ ላይ ተደገፊ!» https://t.me/+o7ZrQFQjILVhNDVk

ዛሬ አዲስ ሕይወት ለምትጀምሪው ውዷ እህቴ፣ እህት ዓለም! ዛሬ የሕይወትሽ አዲስ ምዕራፍ የሚከፈትበት፣ ከምትወጅውና ካደግሽበት ቤታሽ ወጥተሽ የራስሽን ዓለም የምትጀምሪበት ታላቅ ቀን ነው። ይህንን ምክሬን የምፅፍልሽ አይኖቼ በናፍቆት እንባ እየረጠቡ፣ ልቤ ግን ላንቺ ባለው ታላቅ ደስታ እየጨፈረ ነው። ውድ እህቴ! ትዳር አላህ በቁርአኑ ‹ታላቅ ቃል ኪዳን› ብሎ የጠራው የተቀደሰ መንገድ ነው። በዚህ መንገድ ላይ ስትጓዢ እንደ ታላቅም እንዴ ታናሽም እህትሽ እነዚህን ጥቂት የልብ ምክሮች አደራ እልሻለሁ፦ 1.የአላህን ድኔ የቤታችሁ ምሰሶ አድርጊው፦ በቤታችሁ ውስጥ ሶላት፣ ዚክርና ቁርአን አይጥፋ። ሱና ያለበት ቤት በረካው አይጠፋም፣ሰላሙም አይታወክም። ባለቤትሽን ለአላህ ብለሽ ውደጂው፣ እሱንም ወደ አላህ የሚቃረብበት መከታ ሁኚው። 2. የባለቤትሽ ሰላምና መረጋጋት (መረጋገጫ) ሁኚ፦ አላህ ሴትን የፈጠራት ለወንድ ልጅ የሰላም ወደብ እንድትሆን ነው። ባለቤትሽ ከውጭ ደክሞትና ዛለው ሲመጣ፣ ያንቺ ፈገግታ ድካሙን የሚያስረሳ፣ ያንቺ ለስላሳ ንግግር ጭንቀቱን የሚያቀልል ይሁን። ለእሱ ምድር ሁኚለት፣ እሱ ሰማይ ይሆንልሻል፤ አንቺ ምሰሶ ሁኚለት፣ እሱ ጣራ ይሆንልሻል። 3. የቤታችሁን ሚስጥር እንደ ነፍስሽ ጠብቂ፦ የትዳር ውበቱ ሚስጥሩ ነው። በናንተ መካከል የሚፈጠረውን ማንኛውንም ነገር (ደስታም ይሁን ቅሬታ) በሩን ዘግታችሁ በመካከላችሁ ብቻ ፍቱት። ለቤትሽ ሚስጥር ታማኝ ካዝና ሁኚ፤ ያኔ ክብርሽ በባለቤትሽ ዘንድ እጥፍ ይሆናል። 4. በትዕግስት በሶብር አጊጪ፦ ትዳር ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ ላይሆን ይችላል። አንዳንዴ ማዕበል ሲመጣ በትዕግስት እለፊው። ቁጣን በዝምታ፣ ኩርፊያን በፈገግታ አሸንፊው። በሰጠሽ ነገር ላይ አመስጋኝ (ሻኪር) ሁኚ፤ አላህ ይጨምርልሻል። 5. የባለቤትሽን ቤተሰቦች እንደ ገዛ ቤተሰብሽ እያቸው፦ የእሱን እናት እንደ እናትሽ፣ እህቶቹን እንደ እህትሽ አቅፈሽ ያዢ። እነሱን ማክበርሽ ባለቤትሽን ማክበርሽ ነው። የእነሱን ልብ ካሸነፍሽ የባለቤትሽን ልብ በቁልፍ እንደቆለፍሽው ቁጠሪው። ውድ እህቴ! በሐላል ጎጆሽ ውስጥ በደስታና በበረካ እንድትኖሪ ዘወትር ዱዓዬ ነው። አላህ ትዳራችሁን የፍቅር፣ የራህመትና የጀነት መንገድ ያድርግላችሁ። ባረከላሁ ለኩማ ወባረከ ዐለይኩማ ወጀመዐ በይነኩማ ፊል ኸይር! ///ግጥም ለሙሽሮች/// ሙሺሪት ሙሺራዉ እኮን ደስ አላችሁ አላህ እድሜ ሰቶ ለዚህ አበቃችሁ ፡ በደስታ ኑሩ ይስመር ትዳራችሁ ፡ ትዳር ደስ የሚል ነው የነብዩ ሱና የመልካሞች መንገድ የሶሀቦች ፋና ((የኔዋ ሙሽራ)) እኮን አደረሰሽ የኔዋ ሙሽራ ዉስጤን ደስ ይለዋል ስለ አንች ሲወራ ከጎንሽ ባልሆንም ዛሬ በሰርግሽ ቀን ሁልጊዜ አስባለሁ ስለ አንች ቀን በቀን አብሽሪ ሙሺሪት ዛሬ ነው አለምሽ ትዳርሽም ይስመር ኑሪልኝ ሳይከፋሽ ((ምክር ለሙሺሪት)) ሀቁን ጠብቂለት አደራ ሙሽሪት ስበብሽ ነው እና መግቢያሽ ወደጀነት በጥሩ እስካዘዘሽ መረሀባ እሽ በይዉ ክብር ይገባዋል የሀላል ባልሽ ነው ፡ ወደ ቤት ሲመጣ ተዉበሽ ጠብቂዉ ሌላ ሴት እዳያይ ባልሽን ሰትሪዉ ፡ ///ምክር ለሙሽራዉ /// ሙሺራዉ አደራ እህቴን አክብራት, ፡ አምነን ሰተንሀል የቤታችን ንግሥት " ዉድናት ልጃችን የቤቱ አይነታ ሁሌም ' ከጎኗ ሁን እዳትገላታ ሙሺራዉ አደራ, ሀቋን ጠብቅላት የነብዩ አደራ ትልቅ ወስያ ናት በተሠብ ሲሰጥህ ሀላፍትና አለብህ በአካል ልጠብቃት ልትወዳት በልብህ የልጆህ እናት አይንህ ማረፊያ ናት መጥፎ አትናገራት በል ተከባከባት በተሰቦን ትታ ወደ አንተ መታለች የህይወቷ አጋር እድትሆን መርጣለች የቤታችን ንግሥት ለአንተ ነው የተሰጠው ሀቋን ጠብቅላት አደራ ሙሺራዉ ፡ ​በአላህ ስም ጀምሬ በከሪሙ ጌታ በራህመቱ አዝንቦ ሰጠን ትልቅ ደስታ ሙራዲና ሀዩን አጣምሮ በደስታ እንኳን ደስ አላችሁ በዛሬዋ ማታ። ​ሙራድ ወንድማችን የሱናው አርበኛ በሰለፎች መንገድ ነቅቶ የማይተኛ አላህ አድሎሀል የቤት ውስጥ ጀግና ሀዩን መርጦልሃል በሱናው ጎዳና። ​ሀያት እህታችን የሀያእ ተምሳሌት በሂጃብሽ ንግስት አንች የቤት እመቤት ከኢምራን ሸጋ አባት ጋር ዛሬ ስትጣመሪ የጀነትን ሪዝቅ በጋራ ጀምሪ። ​ተውሂድ ይሁንላችሁ የቤቱ መሰረት በሱናው ያሸብርቅ የቤታችሁ ማብራት የሰለፎች ምክር ይሁንላችሁ መሪ በፍቅር ተሳስራችሁ ለዘላለም ኑሩ። ​ውለዱና ክበዱ ተውሂድን አንጋቢ ሱናን የሚወዱ ቢድዓን ሰላቢ አላህ ያቆያችሁ በኸይር ስራ ላይ ለአኼራ ስንቅ ጀነተል ፊረደውስ ላይ ። ​ባረከላሁ ለኩም ወባረከ አለይኩም ወጀመዐ በይነኩማ ፊል ኸይር የኔ ምርጥ ጥንዶች ትዳራችሁ ያማረ የሰመረ አላህ ያድርገዉ መብሩክ ክክክ በጣም ከምወዳችሁ እህታችሁ ኡሙ ሓቲም መኪያ

ዛሬ እቤታችን ሰርግ አለ ፏፏፏ እንበል
+8
ዛሬ እቤታችን ሰርግ አለ ፏፏፏ እንበል

​بَارَكَ اللهُ لَكُمَا، وَبَارَكَ عَلَيْكُمَا، وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ. اللَّهُمَّ اجْعَلْ بَيْنَهُمَا مَوَدَّةً وَرَ
​بَارَكَ اللهُ لَكُمَا، وَبَارَكَ عَلَيْكُمَا، وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ. اللَّهُمَّ اجْعَلْ بَيْنَهُمَا مَوَدَّةً وَرَحْمَةً، وَارْزُقْهُمَا ذُرِّيَّةً صَالِحَةً، وَبَارِكْ لَهُمَا فِي رِزْقِهِمَا، وَاجْعَلْ حَيَاتَهُمَا سَعَادَةً وَطَاعَةً. مبروك اختي الكريمة يا حبيبة قلبي، أتمنى لكِ من أعماق قلبي السعادة الأبدية في حياتك الزوجية. أسأل الله أن يجعلكِ أسعد عروس ويرزقكِ الذرية الصالحة. أنتِ تستحقين كل خير، وكم أنا سعيدة برؤيتكِ في هذا اليوم المميز. بارك الله لكِ وبارك عليكما وجمع بينكما في خير." "أدعو الله أن يجعل حياتكما مليئة بالحب والسعادة والخير." " مبروك يا أجمل عروس، أتمنى لكِ التوفيق في حياتك الجديدة." "اللهم اجعله زواج الدهر، وبارك لهما وعليهما." "أتمنى لكِ حياة زوجية سعيدة مليئة بالحب والود." "اللهم اجعله زواجًا مباركًا، واجعله بداية لحياة سعيدة."." https://t.me/+EMcH10oKjWdjZDVk

Repost from N/a
በድብቅ ወንጀሎች ምክንያት ስራዎቻችን እንዳይበላሹ .... https://t.me/MerkezulimamiAhmed

የፍቅራችን ቅኔ~~~~ በፍቅር ሰሌዳ በመዋደድ ቅኔ፣ የኔ ልብ ባንተ ያንተም ልብ በኔ። የነፍስያችን ወግ ካሳባችን ሰርፆ፣ በልባችን ሀዉልት ፍቅራችን ተቀርፆ። ደምህና ደሜ ፍፁም ተዋህዶ፣ ባንደበት ሊ
የፍቅራችን ቅኔ~~~~ በፍቅር ሰሌዳ በመዋደድ ቅኔ፣ የኔ ልብ ባንተ ያንተም ልብ በኔ። የነፍስያችን ወግ ካሳባችን ሰርፆ፣ በልባችን ሀዉልት ፍቅራችን ተቀርፆ። ደምህና ደሜ ፍፁም ተዋህዶ፣ ባንደበት ሊገለፅ በቃላት ተጋምዶ። ቀና ብለህ እያት ዉቢቷን ጨረቃ፣ የብርሃን ዝናር በወገቧ ታጥቃ። ተስፋ ልታድል ጽልመት ለጋረደዉ፣ በትዝታ ጋሪ ሞሽራ ልትሸኘዉ። ያቺ ዉብ ጨረቃ ምስክር ትሁንህ፣ በሷ ብርሃን የኔ መልክ ይታይህ። ከዋክብትን ስታይ ከደጃፉ ቆመህ፣ በአንተ ብርሃን ድምቀቴ ይታወስህ። የኔና አንተ ፍቅር በወርቅ ይመሰላል፣ ካፈር ተደባልቆ ከሳት ይፈተናል። ከጭቃዉ ይጠራል ነበልባሉን አልፎ፣ ከነፍስ ተራቆ ከህሊና ገዝፎ *አለች አፍቃሪዋ🙌* ከማቃላት ኡሙ ሂክማ https://t.me/+o7ZrQFQjILVhNDVk

Repost from N/a
የኡስታዝ ኸድር አሕመድ ደርሶች 01) ሠላሠቱል ኡሱል (24) 02) ፊርቀቱ ናጂያ (53) 03) ኹዝ ዐቂደተክ  (25) 04) ጂናየቱ ተመዩዕ (19) 05) ፈትሑ ረቢል በሪያ (85) 06) ቡሉጉል መራም (300) 07) ተብሲሩል ኸለፍ (22) 08) ተብሲሩል ኸለፍ (27) 09) ኪታቡ ተውሒድ (70) 10) ተብሲሩል ባዲኢን (44) 11) ረውዶቱል ባዲኢን (17) 12) ተቅሪቡ ተድሙሪያ (81) 13) አልአርበዑነ ነወዊያ (29) 14) ሉምዐቱል ኢዕቲቃድ (70) 15) አልቀዋዒዱል አርበዕ (05) 16) ሙስጦለሑል ሐዲሥ (87) 17) ዑምደቱል አሕካም (140) 18- አልቀዋዒዱል አርበዕ (06) 19) አልቀዋዒዱል ሙሥላ (43) 20) ተንቢሁ ዘዊል አፍሃም (52) 21) አልቀዋዒዱል ሙሥላ (102) 22) አልአጅዊበቱል ሙፊዳ (153) 23) ኩን ሰለፊየን ዐለል ጃዳ (98) 24) ሙተሚመቱል አጁሩሚያ (169) 25) ሀዚሂ ደዕወቱና ወዐቂደቱና (22) 26) ኹላሶቱ ኑሪል የቂን ጁዝ1 (28) 27) ኪታቡ ተውሒድ የፈውዛን (99) 28) ኢስቲቅባሉ ሸህሪ ረመዷን (09) 29) ሀዚሂ ደዕወቱና ወዐቂደቱና (08) 30) ሠላሠቱል ኡሱል ወአዲለቱሃ (21) 31) ኪታቡ ተውሒድ የፈውዛን (68) 32) ተሕፈቱ ሰኒያ ሸርሑል ሓኢያ (52) 33) ኡሱሉ ሱንና የኢማም አሕመድ (23) 34) አልኡሱል ሚን ዒልሚል ኡሱል (28) 35) ዐቂደቱ አህሊ ሱነቲ ወልጀማዐ (17) 36) ሸርሑ ሐዲሢ ኢና ኩና ጃሂሊያ (30) 37) ዐቂደቱ ሰለፍ አስሓቢል ሐዲሥ (48) 38) ሸርሑ ነዋቂዲል ኢስላም የፈውዛን (21) 39) ኡሱሉ ሲታ በኢብኑ ዑሠይሚን ሸርሕ (30) 40) ሸርሑ ዐቂደቱል ዋሲጢያ የሀራስ (185) 41) አልሙምቲዕ ፊ ሸርሒል አጁሩሚያ (202) 42) ሸርሑል ዐቂደቲል ዋሲጢያ ሊልሀራስ (126) 43) ከሽፉ ሹቡሃት በኢብኑ ዑሠይሚን ሸርሕ (59) 44) ሓኢየቱ ኢብኒ አቢ ዳውድ የፈውዛን ሸርሕ (89) 45) ሚን ኡሱሊ ዐቂደቲ አህሊ ሱነቲ ወልጀማዐ (19) 46) ሚን ኡሱሊ ዐቂደቲ አህሊ ሱነቲ ወልጀማዐ (19) 47) አዳቡ ጧሊቢል ዒልም (33) 48) አልሙዕተቀዱ ሶሒሕ (39) 49) መትኑል አጁሩሚያ (95) እንደዚህ ዓይነቶች ሱናን የሚያሰራጩ ብርቅየ የሱና ኡስታዞች እያሉ ኢንግሊዘኛ ተናጋሪ ጋር ምን አያያዛችሁ

ፈጥኖ ማን ይመልስ ! ✈️✈️ ትክክለኛውን  መልስ ያገኝ ሰው  add የሚለውን በመጫን የብዙ የሱና ቻናሎች ሰጦታ ያገኛል። 📝 ጥያቄ በቅዱስ ቁርአን ውስጥ "ሱረቱል ፋቲሐ" መጀመሪያ ላይ የወረደች የመጀመሪያዋ የቁርአን ሱራ ናት።

⚠️ለኻሊድ ክብሮም ሹቡሃቶች የተሰጠ አጠር ያለች ረድ❗️ ⚠️ኻሊድ ክብሮም የተባለው ግለሰብ የሚዘራው መርዝ በአሁኑ ሰዓት በብዙ የዋህ ሙስሊሞች ዘንድ "አዲስና ዘመናዊ እይታ" እየመሰለ ቀልብን እየሰረቀ ይገኛል። ነገር ግን ንግግሩንና አካሄዱን ላስተዋለ ሰው፣ ይህ ግለሰብ የጥንቶቹን "ቁርኣንዮች" መንገድ በመከተል የኢስላምን መሰረት ለመናድ እየሰራ መሆኑን መረዳት ይቻላል። ⚠️ አላህ ዲኑን የሚጠብቁለትና የጠማሞችን ትርጓሜ የሚያጋልጡለት ኡለሞችንና ተማሪዎችን በየዘመኑ ያስነሳል። ዛሬ ላይ ደግሞ "ቁርኣን በራሱ ተብራርቷል፣ የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይሻም" በሚል የቀለም ቅብ ዲኑን ሊበርዙ የሚሞክሩ ግለሰቦች ተከስተዋል። ይህ ካሊድ ክብሮም የሚባል ግለሰብ በተናገራቸው ንግግሮች ላይ "ቁርኣንን ከቁርኣን ውጭ ያለ አካል የሚያብራራው የለም" በማለት የነቢዩን ﷺ ሱና ሙሉ በሙሉ ዋጋ ቢስ ለማድረግ ደፍሯል። 1ኛ. "ቁርኣን የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይሻም" የሚለው ንግግር ሁክም (ፍርድ) ምንድን ነው የሚለውን እንይ፦ ⚠️አንድ ሰው "ቁርኣን የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይፈልግም" ወይም "ቁርኣን ብቻ ይበቃናል፣ ሱና አያስፈልግም" ካለ በዑለሞች ዘንድ ያለው ፍርድ ከባድ ኩፍር (ከኢስላም መውጣት) ነው። ⚠️ ኢማም አስ-ሱዩጢይ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ "አዋጅ! እወቁ... የነቢዩን ﷺ ሐዲስ (ንግግርም ይሁን ተግባር) በንግግርም ይሁን በተግባር ውድቅ ያደረገ፣ ሐዲሱ ሐሰን ይሁን ሶሒሕ መረጋገጡን እያወቀ ውድቅ ያደረገ ሰው፤ ከኢስላም ክበብ ወጥቷል፤ ከአይሁዶችና ከነሳራዎች ጋር (በፍርዱ) ይመደባል ብለዋል።" (ሚፍታሕ አል-ጀናህ፡ 14) ⚠️ኢብኑ ሐዝም (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ "አንድ ሰው 'እኛ የምንይዘው ቁርኣን ላይ ያገኘነውን ብቻ ነው' ካለ፤ እርሱ በሁሉም ሙስሊሞች ስምምነት (ኢጅማዕ) ካፊር ነው።" (አል-ኢሕካም፡ 2/80) ለምን ካፊር ይባላል? ምክንያቱም አላህ በቁርኣን ውስጥ ነቢዩን ﷺ እንድንታዘዝ፣ የሳቸውን ማብራሪያ እንድንይዝ በብዙ ቦታዎች አዝዟል። የሳቸውን ማብራሪያ "አያስፈልግም" የሚል ሰው የአላህን ትዕዛዝ "ስህተት ነው" እያለ ስለሆነ ነው። 2ኛ. የሰለፎችና የታላላቅ ኡለሞች ንግግር ስለ ሱና አስፈላጊነት እንመልከት ፦ ⚠️ኢማም አል-አውዛዒይ (ረሒመሁላህ)፦ "ቁርኣን ወደ ሱና ያለው ፍላጎት፣ ሱና ወደ ቁርኣን ካለው ፍላጎት ይበልጣል።" (ማለትም ቁርኣን ጠቅለል ያለ (ሙጅመል) በመሆኑ፣ ሱና ካላብራራው በስተቀር ልንተገብረው አንችልም)። ⚠️ ያሕያ ቢን አቢ ከሢር (ረሒመሁላህ)፦ "ሱና በቁርኣን ላይ ፈራጅ (መሪ) ነው እንጂ ቁርኣን በሱና ላይ ፈራጅ አይደለም።" (ይህ ማለት ሱናው ቁርኣኑ እንዴት መረዳት እንዳለበት ይወስናል ማለት ነው)። ⚠️ ኢማም አል-በርበሃሪ (ረሒመሁላህ)፦ "አንድ ሰው ሐዲስን ሲሰማ 'ይህንን ተወውና ቁርኣንን አምጣልኝ' ካለ፤ እወቅ እርሱ ዚንዲቅ (ከሀዲ) መሆኑን!" (ሸርሕ አስ-ሱናህ) ⚠️ኢማም አሕመድ፦"ሱና ቁርኣንን ያብራራል፣ ይመራልም።" ⚠️ሸይኽ ቢን ባዝና ሸይኽ አልባኒ፦** ሱናን የሚክዱ ወይም የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይሻም የሚሉ ግለሰቦች ከኢስላም መንገድ የወጡ (ሙርተድ) መሆናቸውን በሰፊው አስረድተዋል። ⚠️ኻሊድ ክብሮም "ቁርኣን በራሱ ተብራርቷል" ሲል አላህ ለነቢዩ ﷺ የሰጣቸውን ስልጣን እየካደ ነው። - ﴿وَأَنزَلْنَا إِلَيْكَ الذِّكْرَ لِتُبَيِّنَ لِلنَّاسِ مَا نُزِّل إِلَيْهِمْ﴾ “ለሰዎችም ወደ እነርሱ የተወረደውን (ቁርኣን) ታብራራላቸው ዘንድ ቁርኣንን ወደ አንተ አወረድን።” (አን-ነሕል 44)። አላህ "ቁርኣን በራሱ ይብራራል" አላለም፤ "አንተ መሐመድ ሆይ ታብራራላቸው ዘንድ" ነው ያለው። ⚠️ነቢዩ ﷺ ይህ ዓይነቱ ጥመት ወደፊት እንደሚመጣ ቀድመው አስጠንቅቀው ነበር፦ «أَلَا إِنِّي أُوتِيتُ الْقُرْآنَ وَمِثْلَهُ مَعَهُ، أَلَا يُوشِكُ رَجُلٌ شَبْعَانُ عَلَى أَرِيكَتِهِ يَقُولُ: عَلَيْكُمْ بِهَذَا الْقُرْآنِ...» “አዋጅ! እኔ ቁርኣንንና መሰሉን (ሱናን) አብሮ ተሰጥቻለሁ። አዋጅ! አንድ በምቾት ወንበሩ ላይ የተደገፈ ሆዱ የጠገበ ሰው፦ 'ቁርኣን ብቻ ይበቃችኋል' የሚልበት ጊዜ ሊመጣ ተቃርቧል...ብለዋል።” (አቡ ዳውድ፡ 4604) ኻሊድ ክብሮም ልክ ነቢዩ ﷺ እንዳሉት የቁርኣን አንቀጾችን እየቆነጸለ፣ የነቢዩን ﷺ ትምህርት "አያስፈልግም" እያለ ነው። የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ ውድቅ ማድረግ ማለት፦ * እንዴት እንደምንሰግድ (በቁርኣን ውስጥ የረከዓ ብዛት የለም!) * እንዴት ዘካት እንደምንከፍል (በቁርኣን ውስጥ ኒሷብ የለም!) * እንዴት ሐጅ እንደምናደርግ... ይህንን ሁሉ የኢስላም መሰረት ማፍረስ ማለት ነውና። ከዚህ ጠሞ አጥማሚ ሰውዬ ተጠንቀቁ ⚠️ ይሄ ጠሞ አጥማሚ ካሊድ ክብሮም ከዚህ በፊትም ስለ ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም) እና ስለ ተውራት የዘባረቃቸው ውሸቶችም አሉ ፦ ⚠️ የዕቁብ ኢስራኢል አይደለም ማለቱ ይሄ የግለሰቡን የቋንቋና የታሪክ ድንቁርና ብቻ ሳይሆን ግልጽ የሆነ ቅጥፈት ያሳያል። * ስለ ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም)፦ አላህ በቁርኣኑ እንዲህ ይላል፦ ﴿كُلُّ الطَّعَامِ كَانَ حِلًّا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ إِلَّا مَا حَرَّمَ إِسْرَائِيلُ عَلَىٰ نَفْسِهِ﴾ *“ምግብ ሁሉ ለእስራኤል ልጆች የተፈቀደ ነበር፤ እስራኤል (ያዕቆብ) በራሱ ላይ እርም ካደረገው በስተቀር።”* (አል-ዒምራን 3:93) ሙፈሲሮች በሙሉ "እስራኤል" ማለት ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም) መሆኑን በአንድ ድምጽ (ኢጅማዕ) ተስማምተዋል። * ካሊድ ክብሮም ስለ ተውራትም የቀጠፈው ቅጥፈት አለ፦ ተውራት ለሙሳ (ዐለይሂ ሰላም) የወረደ መሆኑን ቁርኣን በብዙ ቦታዎች ይገልጻል። ﴿ثُمَّ آتَيْنَا مُوسَى الْكِتَابَ تَمَامًا عَلَى الَّذِي أَحْسَنَ وَتَفْصِيلًا لِّكُلِّ شَيْءٍ﴾ (አል-አንዓም 154) (አል-አንዓም 154፣ አል-አዕራፍ 145)። ይህንን የሚክድ ሰው የአላህን ቃል እያስተባበለ ነው። ሌሎችም ብዙ ማስረጃዎች አሉ ። ⚠️ኻሊድ ክብሮም የተባለው ግለሰብ የሚከተለው መንገድ "ቁርኣን ብቻ በቂ ነው " በሚል ሽፋን ኢስላምን የማፍረስ መንገድ ነው። ቁርኣንን ከነቢዩ ﷺ ትርጓሜና ከሰለፎች ግንዛቤ ነጥሎ "በራሴ ጭንቅላት እተረጉማለሁ" ማለት፣ ቁርኣንን ለስሜት መጫወቻ ማድረግ ነው። ሱናን የካደ ሰው ደግሞ ሶላቱንም፣ ዘካውንም፣ ሐጁንም መተግበር አይችልም፤ ምክንያቱም የእነዚህ ሁሉ ዝርዝር ሕግጋት የሚገኙት በሱና ውስጥ ብቻ ነውና። ወንድምና እህቶቼ ይህንን "ጠሞ አጥማሚ" ግለሰብ ከመስማት ተጠንቀቁ! ዲናችሁን ከታማኝና የሰለፎችን መንገድ ከሚከተሉ ኡለሞችና ኡስታዞች ተማሩ። አላህ በቁርኣን አጥርቶ የነገረንን እውነት "አይደለም" የሚል ሰው፣ ነገ የአላህን ሕግጋት በሙሉ "አያስፈልጉም" ማለቱ አይቀሬ ነውና ተጠንቀቁ አስጠንቅቁ። ሸር በማድርገ ለሌሎችም አድርሱ t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

🔖  ዛሬ ምሽት 3:00 እንዳያመልጥዎ! ሳምንታዊ የጥያቄና መልስ ውድድር ዛሬ ምሽት 3:00 ላይ ይቀጥላል። ✅ ይሳተፉ፣ ይማሩ፣ እውቀትዎን ይፈትሹ! ለመቀላቀል እና ለመሳተፍ ከታች ይጫኑ  👇 👉 t.me/FKR_ESKE_JENET

የጁሙአ ግብዣ 🎙ሱረቱል ካህፍ سورة_الكهف 📚][]ሱረቱል ከህፍ 📎🥀ውብ ቲላዋ@[] ቁርአን የልብ መርጊያ ለደረቀ ልብ ማረስረሻ ነው። 💐የጁመዓ ቀን ሱናዎች💐 ➖➖➖➖➖➖➖ ↩️💎 ‏سنن يوم الجمعة ➊ 💎الغسل ➋💎 الطيب ➌ 💎السواك ➍💎 لبس الجميل ➎💎 قراءة سورة الكهف ➏💎 التبكير لصلاة الجمعة ➐💎الإكثار من الدعاء والصلاة على النبي 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ➊ 🌺መታጠብ ➋ 🌺ሽቶ መቀባት ➌🌺 ሲዋክ መጠቀም ➍ 🌺ጥሩ ልብስ መልበስ ➎ 🌺ሱረቱል ካህፍን መቅራት ከቻልን ➏ 🌺ለጁመዓ ሶላት መጣድ ➐ 🌺በነብዩ ﷺ ላይ ሰለዋት ማብዛት 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 «اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ   🌺በሰለዋት በዚክርያውለን ﷺ 🌹 .................🌹 ﷺ ﷺ🌹 ..................🌹 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ🌹🔹🔹🌹  ﷺ ﷺ ﷺ 🌹🔹🔹🌹 በነብዩ ላይ ሰለዋት ማውረድን እናብዛ !!                

☪☪☪☪️ 🦋 ተጋባዥ ኡስታዞች :- 1️⃣:-ሸይኽ- ኑር ፈለቅ ከመድና ዩኒቨርስቲ 2️⃣:-ኡስታዝ- አቡ ኢምራን 3️⃣:-ኡስታዝ ሙሀመድ አያሌው 4️⃣:-ኡስታዝ አቡ ረያን 5️⃣:-ኡስታዝ አቡል መአሊ
☪☪☪☪️ 🦋 ተጋባዥ ኡስታዞች :- 1️⃣:-ሸይኽ- ኑር ፈለቅ ከመድና ዩኒቨርስቲ 2️⃣:-ኡስታዝ- አቡ ኢምራን 3️⃣:-ኡስታዝ ሙሀመድ አያሌው 4️⃣:-ኡስታዝ አቡ ረያን 5️⃣:-ኡስታዝ አቡል መአሊ 6️⃣:-ኡስታዝ አቡ ኡበይዳ 7️⃣:-ኡስታዝ አቡ አምር ኑርየ ጎቤ 8️⃣:-ኡስታዝ አቡ ነሚር 9️⃣:-ኡስታዝ አቡ ሻኪራ 1⃣2⃣:-ኡስታዝ አቡ ሂበቲላህ ሁሰይን 1⃣3⃣:-ኡስታዝ አቡ ሙሀመድ ሰኢድ 1⃣4⃣:-ኡስታዝ ሙሀመድ ሲራጅ 1⃣5⃣:-ኡስታዝ አቡ ረስላን 1⃣6⃣:-ዶክተር ሰኢድ (አቡል አባስ ) 1⃣7⃣:-ወንድም  አቡ ፋሩቅ ኑረድን 1⃣8⃣:-ወንድም አቡ አመቲ ረህማን ኡስማን 1⃣9⃣:-ወንድም አቡ ሙነወር ሙሀመድ ሲራጂ 2⃣0⃣:-ወንድም አቡ ረያን አብዲ ረህማን 2⃣1⃣:ኡስታዝ- አህመድ አማን  ቲለዋ :- 🔊🔊🔊 2⃣2⃣:ቃሪዕ- መሀመድ አህመድ ከአድስ አበባ 2⃣3⃣:ቃሪዕ- ጀማል ኡመር ከአድስ አበባ 2⃣4⃣:በ-'ወንድም አቡ ሀይደር 2⃣5⃣:-በ'ወንድም አቡ መርየም 2⃣6⃣:በ-'ወንድም ኢድሪስ አቡ የህያ በተጨማሪ በሙሽራው የቲለዋ ግብዣ ይኖረናል 🔹 :- ፕርግራም መሪዎች🔹🔹🔹🔹 ❶:- ኡስታዝ :-አቡ ሹራ አህመድ ❷ :-ወንድም አቡ ሁዘይፋ ሰኢድ ❸:በተጨማሪ- በሙሽራው የቁርኣን ግብዣ ይኖረናል። ፕሮግራሙ የሚተላለፋው 📎 ⬇⬇⬇⬇⬇⬇ https://t.me/Mf11q ✉️✉️

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል መብሩክ የሀፍሷዬ ማሚ የኔዉብ 👏👏👏👏🌹🌹🌹🌹 ማሻአላህ ማሻአላህ ማሻአላህ

....➽በተለይ በስደት ላለነው ...✍️‼️ ------------------------------ .... በዛሬዋ ቀን ብቻ ስንት አይነት ስሜት ተመላለሰባችሁ በዒዱ ቀን መዋል ካለባችሁ ሰዎች ጋር ሆናችኋል...⁉️ ......ህይወት ተቃራኒ ነች ጀግኖቼ... ዙሪያችሁን ስትመለከቱ ሁሉም ሰው የህይወቱን መንገድ ያገኘ ይመስላችኋል… አንዱ ቢዝነስ ከፍቷል…፤ አንዱ ተጋብቷል…፤ ሌላው አለምን ይዞራል…፤ ሁሉም ደስተኛ፣ ውጤታማ፣ የተሳካላቸው ይመስሏችኋል አይደል…⁉️ እናንተ ግን እዛው ቆማችሁ ራሳችሁን “ገና ጊዜ አለኝ…” እደርስባቸዋለሁ ብለህ ለማሳመን ትሞክራለህ። ግን ይህን አቆም ውስጣችሁ አይቀበልም… ውስጣችሁ አልፎባችኋል የሚል ጩሀት ያስተጋባል .....። 👉ወንድሞቼ… 👉እህትቼ... ችግሩ ከእናንተ አይደለህም። 🌷..ችግሩ ያለው ራሳችሁን ከሌሎች ጋር በማወዳደራችሁ የሚፈጠር #ተውሳክ ነው። ⭕️ሁሌም እንደምነግራችሁ‼️ ....Social media ላይ የሚታየው ሙሉ ህይወት አይደለም… ➽#ሰዎች_የሚያሳዩዋችሁ ድሎቻቸውን....ስኬታቸውን ብቻ ነው…። #እንባቸውን፣ #ውድቀታቸውን፣ #እዳቸውን፣ #ጭንቀታቸውን አያሳዋችሁም። ⭕️ለምሳሌ...‼️ ➥በ❷❸ አመቱ ድርጅት የከፈተውን ወጣት ታያለህ…ከ➏ ወር በኋላ መክሰሩን ግን አታይም። ➥በ➋➎ አመቷ አለምን ስትዞር ታያታለሽ… በእዳ እንደምትኖር ግን አታውቂም። ➥በ➋❼ አመታቸው በደማቅ ሰርግ የተጋቡትን ጥንዶች ታያላችሁ… እርስ በእርስ ቀስ ብለው ያለ ጭቅጭቅ መነጋገር እንደማይችሉ ግን አታዩም። 🛑ወዳጄ… አንተ ዘግይተህ አይደለህም። ህይወት ውድድር አይደለችምና ነው። ➥20ዎቹና 30ዎቹ “ሁሉን ነገር መጨረሻ” ሳይሆን ሁሉን ነገር የመጀመሪያ ፣ የመሞከሪያ ፣ የመውደቅ፣ የመነሳት ዘመን ናቸው። 20ዎቹን አልፈህ .... 👉በ30ዎቹ መጨረሻ ስራህን ልታገኝ ትችላለህ… 👉በ40ዎቹ ደሞ ራስህን ልታገኝ ራስህን ልታውቅ ትችላለህ… 👉በ50ዎቹ ፍቅር ውስጥ ልታገባ ትችላለህ… .....እመነኝ አሏህ ሲፈቅድ እንጂ በእኛ በሰው ልጆች እቅድና ፕላን ምንም “ትክክለኛ የህይወት ሰዓት” የሚባል የለም። ላንዱ ቀድሞ የተሳካለት ላንዱ በእስተርጅናው ሊሳካለት ይችላል። .....ጀግናዬ ከተባረከኮ ....ማምሻም እድሜ ነው....የማታ እንጀራ ይስጠኝ የሚባለው ፀሎት የሚፀለየው ለዚህ ነው። ስለሆነም…‼️ ➥ዛሬ ከሌሎች ህይወት ይልቅ የራስህን ጉዞ አክብር። ቀስ ብለህ ብትሄድም እየተራመድክ ነው። ውድቀትህ መጨረሻህ አይደለም…። የዛሬ ውድቀትህ ለነገ ስኬትህ ምክንያት ነው። ✅ወላሒ አንተ የማትረባ ሰው አይደለህም…። አንተ በሂደት ላይ ያለህ ጠንካራ ብርቱ ጀግና ሰው ነህ!! ፈጣሪ ሀሳብህን በሙሉ ያሳካልህ፣አግኝቶ ከማጣት ይሰውርህ...ብዬ ዱዐዕ አደርግልሀለሁ በዱዐዕ አንረሳሳ እሽ። «መልካም ዒድ ለሁላችን ይሁንልን» t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

በኢማራት የሚቀርበው የደዕዋ ፕሮግራም በዚህ የቴሌግራም ቻናል የሚተላለፍ ይሆናል፣ ኢንሻአላህ - የቴሌግራም ቻናል :- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

ልባም ሴት ትናቷን ለትምህርት ዛሬዋን ለስራ ፣ነገዋን ለተስፋ፣ትጠቀማለች ፡፡ https://t.me/+o7ZrQFQjILVhNDVk
ልባም ሴት ትናቷን ለትምህርት ዛሬዋን ለስራ ፣ነገዋን ለተስፋ፣ትጠቀማለች ፡፡ https://t.me/+o7ZrQFQjILVhNDVk