BiT SU Official Information Channel
Open in Telegram
➤➤➤ This channel has been created to provide students with timely and relevant information from the Student Union and management offices. bitstudentunion4@gmail.com
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
1 223
Subscribers
+424 hours
+1207 days
+15730 days
Posts Archive
🚨 አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ለኢንተርን ተማሪዎች በሙሉ! 🚨
የግቢውን የተማሪዎች ካፌ አገልግሎት በመጠቀም ላይ የምትገኙ የኢንተርን (Internship) ተማሪዎች ከዚህ ድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
ከዚህ በኋላ ጥብቅ ቁጥጥርና ፍተሻ የሚደረግ በመሆኑ፣ መመሪያውን ጥሳችሁ በሚገኘው ማንኛውም ተማሪ ላይ አስፈላጊው ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን በግልጽ እናሳውቃለን።
⚠️ ማሳሰቢያ፦ ካፌው የተፈቀደላቸው መደበኛ ተማሪዎች ብቻ እንዲጠቀሙበት ከወዲሁ እንድትተባበሩ እናሳስባለን።
📢 ለግቢያችን ተማሪዎች በሙሉ! 📢
በመንገድ መዘጋት (በትራንስፖርት ችግር) ምክንያት ጉዟችሁን አቋርጣችሁ ወደ ግቢ ለተመለሳችሁ ተማሪዎቻችን በሙሉ፤ ከነገ የቁርስ ሰዓት ጀምሮ የካፌ አገልግሎት መጠቀም የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን።
📅 የመጀመሪያው ምግብ ሰዓት፦ ከነገ ቁርስ ጀምሮ
📍 ቦታ። ማዘር ካፌ
መልካም ቆይታ!
አስቸኳይ ማስታወቂያ
ለባህር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) ተማሪዎች በሙሉ፤
በሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት ባጋጠመው የመንገድ መዘጋት ምክንያት፣ በግቢው ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎችን በሙሉ በድጋሚ በአዲስ መልክ በዶርም የመመደብ ስራ እየተሰራ ይገኛል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ሰዓት በግቢው ውስጥ የሚገኙትን ተማሪዎች ትክክለኛ ብዛት ማወቅ ባለመቻሉ፣ ሰሞኑን በምግብ አቅርቦት (በካፌ) ላይ እጥረት እየተፈጠረና ችግሮች እየተስተዋሉ ነው።
ስለሆነም፣ ይህንን ችግር በአስቸኳይ ለመቅረፍ እና የተማሪዎችን ትክክለኛ ቁጥር ለይቶ ተገቢውን የዶርም ምደባና የካፌ አገልግሎት በአግባቡ ለማቅረብ እንዲቻል፤ ከተመራቂ (Graduating Class) ተማሪዎች ውጭ ሆናችሁ በመንገድ መዘጋት ምክንያት ግቢ ውስጥ እየኖራችሁ የምትገኙ ተማሪዎች በሙሉ ተደዋውላችሁና መረጃውን ለሌሎችም አጋርታችሁ በአካል በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
የምዝገባ ቦታ፦ የተማሪዎች ህብረት ቢሮ ቁጥር 4
የምዝገባ ሰዓት፦ ከቀኑ 5:00 እስከ 6:00(Local Time)
⚠️ ማሳሰቢያ፦
ከተጠቀሰው ሰዓት ውጭ መጥቶ መመዝገብ የማይቻል መሆኑን እየገለጽን፤ በተባለው ጊዜ ቀርቦ ያልተመዘገበ ተማሪ የዶርምም ሆነ የካፌ አገልግሎት የማያገኝ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
የተማሪዎች ህብረት ፅ/ቤት
ስለ ካምፓስ የደህንነትና የጥበቃ ቁጥጥር የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት!
የባህር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) ተማሪዎች በሙሉ
አሁን ላይ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት የተማሪዎቻችንን እና የካምፓሳችንን ደህንነት ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ፣ ከዛሬ ጀምሮ በኢንስቲትዩታችን የጥበቃ ሰራተኞች አማካኝነት ጥብቅ የፍተሻ እና የቁጥጥር ስራዎች የሚከናወኑ መሆኑን እንገልጻለን።
በመሆኑም ተማሪዎቻችን የሚከተሉትን መመሪያዎች በጥብቅ እንድታከብሩ እናሳስባለን፦
1⃣የካምፓስ መታወቂያ (ID Card)፦ ማንኛውም ተማሪ ወደ ግቢ ሲገባም ሆነ በግቢው ውስጥ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ መደበኛ የዩኒቨርሲቲ መታወቂያው ሁልጊዜም ከእጁ መለየት የለበትም። መታወቂያ ያልያዘ ተማሪ ወደ ግቢ መግባት የማይችል መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን።
2⃣ከግቢ ውጪ ለሚንቀሳቀሱ፦ ከግቢ ውጪ ለተለያዩ ጉዳዮች የምትወጡ ተማሪዎች፣ በማንኛውም የከተማዋ አካባቢ ለሚደረጉ ድንገተኛ ቁጥጥሮች ዝግጁ ለመሆን መታወቂያችሁን በኪሳችሁ መያዝ ይኖርባችኋል።
3⃣የመግቢያ ሰዓት ገደብ፦ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት (2:00 PM) በኋላ ማንኛውም ተማሪ ከግቢ ውጪ ማምሸት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
⚠️ ወሳኝ ማሳሰቢያ፦ ይህ መመሪያ የተማሪዎቻችንን ሰላም ለማስከበር የወጣ በመሆኑ፣ ከተጠቀሰው የሰዓት ገደብ ውጪ አምሽቶ በሚገኝ እና መመሪያውን ጥሶ በሚንቀሳቀስ ተማሪ ላይ ለሚገጥመው ማንኛውም አይነት እንግልትም ሆነ የህግ ተጠያቂነት፣ ተማሪው ራሱ ሙሉ ኃላፊነቱን የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
"ደህንነታችሁ ለህብረታችን የቅድሚያ ቅድሚያ ነው!"
ከባህር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) የተማሪዎች ህብረት ፅህፈት ቤት
ከፈተናዎች ጀርባ ያሉ የዓላማ ፅናት ስዕሎች! 📸✨
ሰሞኑን በካምፓሳችን ግቢ ውስጥ ልዩ ድባብ ነበር። በየዲፓርትመንቱ የዓመታት ድካማቸውን፣ የሌሊት እንቅልፍ ማጣታቸውን እና ምርምራቸውን በታላቅ በራስ መተማመን ለዳኞች (Examiners) ሲያስረዱ የነበሩትን የተመራቂ ተማሪዎቻችንን የዲፌንስ (Thesis Defense) እውነተኛ የትግልና የስኬት ጊዜያት በምስል ከትበናል።
እነዚህ ፎቶዎች የአንድ ቀን ስኬት ብቻ ሳይሆኑ፣ የዓመታት የፅናት እና የውበት መገለጫዎች ናቸው። እንኳን ለዚህ ታላቅ ምዕራፍ በሰላም አደረሳችሁ! ህብረታችን በእናንተ ኩራት ይሰማዋል።
🎓 ቀጣዩ እና የመጨረሻው ምዕራፍ (Exit Exam)፦ ጀግኖች ተመራቂዎቻችን፤ የዲፌንስ ውብ ምዕራፍ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ለቀጣዩ ትልቅ ፈተና ትልቅ ስንቅ ነው። በመጪው ሰኔ ወር ለምትወስዱት የብሔራዊ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ከወዲሁ በርትታችሁ እንድትዘጋጁ እና ይሄንንም የመጨረሻ መስናክል በድል እንድትሻገሩ የላቀ ምኞታችንን እንገልጻለን። እናንተ የባህር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) ብርሃኖች ናችሁ፤ ይህንንም ፈተና እንደምታሸንፉት አንጠራጠርም!
"ድል ለእናንተ!"
ከባህር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) የተማሪዎች ህብረት ፅህፈት ቤት
#BiTGraduates2026፣ #ThesisDefense፣ #ExitExam፣ #BiTSU
📢 አስቸኳይ ማስታወቂያ ለBiT ተማሪዎች፤
ዛሬ ያጋጠመው የኢንተርኔት መቆራረጥ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (ELPA) በኩል ባጋጠመ የኃይል ማነስ ምክንያት ሰርቨራችን ስራ ማቆሙን እንገልጻለን።
ችግሩን ለመፍታት ከዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ከፍተኛ የጥገና ስራ ሲከናወን የቆየ ቢሆንም፣ በአሁኑ ሰዓት በአስቸኳይ መለወጥ ያለባት አንዲት እቃ በመኖሯ ምክንያት ስራው ሙሉ በሙሉ አልተጠናቀቀም።
በመሆኑም ነገ ጠዋት እቃዋ ተቀይራና ተስተካክላ ሲስተሙ ሙሉ በሙሉ ወደ መደበኛ ስራው እንደሚመለስ በትህትና እንገልጻለን። ላጋጠመው መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቅን፣ በትዕግስት እንድትጠባበቁን እንጠይቃለን።
እናመሰግናለን! 🙏
የBiT ተማሪዎች ህብረት
ካፌ አገልግሎት አቁሟል ተብላችሁ የተመለሳችሁ የ 3ኛ እና 4ኛ አመት ተማሪዎች ካፌ መታችሁ መመገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን።
Dear Graduating Class Student:
Congratulations for accomplishing almost all academic requirements and reach to this milestone. As you are on the verge of your graduation day, you might be busy with non academic routines and disregard preparing yourself for the national exit exam. With this, the institute want to remind you to give attention to this matter, and be successful on the national exam. Hence, please
1) study hard based on the blue spring, be selective and focus on the most relevant topics, ask your faculty for any help whenever needed,
2) actively use the Mobile App, we have loaded handreds of questions that directly help you for the exam,
3) communicate and collect information/data from students in other universities or graduated students,
4) help each other for common success
5) the institute arranged a Model Exit Exam on 26/09/2018 EC. Please attend this exam and evaluate your level of preparation.
Good Luck!
Alayu
የባህር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) ቤተሰቦች የዒድ አል-አድሐ (ዐረፋ) በዓልን በዚህ መልኩ በደመቀ ሁኔታ አክብረናል። 🕌✨ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የወንድማማችነት መገለጫ ሆኖ አልፏል። ለተማሪዎቻችን፣ ለመምህራንና ለሰራተኞች በሙሉ መልካም በዓል! ዒድ ሙባረክ! 🕋🎈 #BiT_Family #Arafa #Eid2026 #ባህርዳር
