en
Feedback
BiT SU Official Information Channel

BiT SU Official Information Channel

Open in Telegram

➤➤➤ This channel has been created to provide students with timely and relevant information from the Student Union and management offices. bitstudentunion4@gmail.com

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
1 224
Subscribers
+1224 hours
+1367 days
+15230 days
Posts Archive
6 ቀናት ብቻ! 🎓 ምረቃው በጣም ቀርቧል!
6 ቀናት ብቻ! 🎓 ምረቃው በጣም ቀርቧል!

​🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄ ማስታወቂያ ​ውድ የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎቻችን በሙሉ፤ ​በመጀመሪያ ለአገር አቀፍ መውጫ ፈተና (Exit Exam) መልካም እድል እንመኛለን። ​ነገር ግን፣ ሰሞኑን በየዶርማችሁ የልብስ፣ የጫማ፣ የስልክ፣ የላፕቶፕ እና የሌሎች ውድ ዕቃዎች ስርቆት እየተበራከተ መምጣቱን ተገንዝበናል። በመሆኑም በድካም ያፈራችሁትና ለምረቃችሁ ያዘጋጃችሁት ንብረት እንዳይባክን ከፍተኛ ጥንቃቄ እንድታደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን። ​ሊደረጉ የሚገቡ ቅድመ-ጥንቃቄዎች፦ 1⃣​በርና መስኮት መቆለፍ፦ ከዶርም ለአጭር ጊዜም ቢሆን ስትወጡ (ለጥናት፣ ለምግብ ወይም ለሽንት ቤት) በራችሁንና መስኮታችሁን በጥንቃቄ መቆለፋችሁን አረጋግጡ። 2⃣​ንብረትን በቦታው ማስቀመጥ፦ ላፕቶፕ፣ ስልክ እና ሌሎች ውድ ዕቃዎችን በግልጽ ከሚታይ ቦታ ላይ ከማስቀመጥ ይልቅ በቁምሳጥን (Lockers) ውስጥ ቆልፎ ማስቀመጥ። 3⃣​የጋራ ጥበቃ፦ በዶርም ውስጥ ያሉ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ከመውጣታችሁ በፊት የዶርም ጓደኛችሁ መኖሩን ወይም መቆለፉን ተከታተሉ። ​አጠራጣሪ ነገሮችን መጠቆም፦ በዶርም አካባቢ የሚንቀሳቀሱ አጠራጣሪ ሰዎችን ወይም ያልተለመዱ ሁኔታዎችን ሲያዩ ወዲያውኑ ለካምፓሱ ጥበቃ ወይም ለተማሪዎች ህብረት ጥቆማ ያድርጉ። ​💡 ያስተውሉ፦ ጥንቃቄ ማድረጋችን ለምረቃችን ያዘጋጀነውን ደስታና ሰላም ይጠብቅልናል። ​የBiT ተማሪዎች ህብረት

BiT_Graduate_CV_Template_2026.docx0.31 KB

NDB 2&3

ሉሲ ህንፃ ዶርም ቁጥር 104

​🌸 ለተመራቂ ሴት ተማሪዎች ብቻ የተዘጋጀ ልዩ የቅዳሜ ጠዋት መርሃ-ግብር! 🌸 ​ምርቃት ደርሷል... ከምርቃት በኋላ ስላለው ማህበራዊ እና የስራ ህይወት፣ ስላጋጠሙ ተግዳሮቶች እና እድሎች በግልፅ
​🌸 ለተመራቂ ሴት ተማሪዎች ብቻ የተዘጋጀ ልዩ የቅዳሜ ጠዋት መርሃ-ግብር! 🌸 ​ምርቃት ደርሷል... ከምርቃት በኋላ ስላለው ማህበራዊ እና የስራ ህይወት፣ ስላጋጠሙ ተግዳሮቶች እና እድሎች በግልፅ ለመወያየት የሚያስችል ልዩ ፕሮግራም ተዘጋጅቶላችኋል። ​🎉 ልዩ የPijama Night (የፒጃማ ምሽት) ፕሮግራም 🎉 (ምንም እንኳን ስሙ የፒጃማ ምሽት ቢሆንም፣ ፕሮግራማችን የሚካሄደው በቅዳሜ ጠዋት ነው!) ​ይህ ፕሮግራም የተዘጋጀው ለእናንተ ለተመራቂ ሴት ተማሪዎች ብቻ ሲሆን፣ ምቹ በሆነ ልብስ ተዘጋጅታችሁ በመምጣት፣ ዘና ባለ መንፈስ በስልጠና እና ውይይት የምናሳልፍበት ነው። እናንተ የምታነሷቸው ማንኛውም አይነት ሀሳቦች እና ጥያቄዎች ላይ በግልፅ እንወያያለን። ​የፕሮግራሙ ይዘት፡ ​👥 የውይይት መድረክ እና የስልጠና ክፍለ ጊዜ ​🤝 ከምርቃት በኋላ ስለሚኖር የስራ እና ማህበራዊ ህይወት ​🤔 እራሳችሁ ተማሪዎች በሚያነሷቸው ማንኛውም ሀሳቦች ላይ ውይይት ​ተሳታፊዎች፡ ተመራቂ ሴት ተማሪዎች ብቻ አዘጋጆች፡ የፀረ-ሱስ ክበብ እና የሴቶች እና ማህበራት አካቶ ትግበራ አስተባባሪ ​📆 መቼ፡ ቅዳሜ (ነገ) ⏰ ሰዓት፡ ጠዋት 3:00 (ልክ በሰዓቱ ይጀምራል!) 📍 ቦታ፡ ፒጃማ ናይት ቢሮ ​ኑ፣ ዘና ባለ ስሜት ስለ ነገው ህይወታችሁ በግልፅ እንወያይ! የሁላችሁም መገኘት ለፕሮግራሙ ድምቀት ነው! ✨

📢 Important Notice from the Students’ Union We understand the concerns raised regarding the power interruptions that occurred during yesterday’s examination and the potential impact they may have had on your exam performance. In response, we have held an urgent discussion with the relevant university officials. Based on the agreement and coordination reached: ⚡ Full preparations have been completed to ensure that the backup generator is activated automatically whenever there is a power outage, preventing any interruption to the electricity supply during examinations. Therefore, we kindly encourage all students to focus fully on their examinations without any concern and to take their exams with confidence and peace of mind. The Students’ Union remains committed to working continuously to create a conducive environment for all students. 🍀 We wish you all a calm, successful, and productive examination period! 🍀 BiT Students’ Union

🚨 Important Notice from the Students’ Union! 🚨 It has come to our attention that during today’s examination session, some disruptions occurred because our Automotive Engineering students arrived late to their examination room. Therefore, we kindly request all students who will be taking upcoming examinations to arrive at the examination venue well before the scheduled starting time. Doing so will help avoid unnecessary stress and ensure that you can take your exams in a calm, organized, and confident manner. 👍 Being on time is the first step toward success! 🎯 We sincerely wish all of you the very best and great success in your examinations. 🌟 Good Luck with Your Exams! 🌟

🚨 Reminder for All Students This is a final reminder for students who have already taken their yearbook photos. Photo selection must be completed by Sunday. Students from departments that have already taken the Exit Exam are requested to complete their photo selection tomorrow. ⚠️ If you do not select your preferred photo before the deadline, one of the photos taken during your session will be selected and used in the yearbook. Students who have not yet submitted their Last Words are required to do so by tomorrow. Late submissions may not be included in the yearbook. Please complete these requirements on time to avoid any issues. 📍 Photo Muler 🏢 Merkato Building, 2nd Floor 🏢 Merkato Building, 3rd Floor 🏨 Water Front Hotel, Ground Floor

This is an updated Exit Exam Schedule for Day 7 (Friday). Please share this schedule with all of our graduating students waiting for their exit exam. Students may use the following direction indicator (Room Labeling) to locate their exam room. B-42 (Computer/Korea Building) Room-1: Programming Lab Room-2: Networking Lab Room-3: Database Lab Room-4: Korea Lab Room-5: FMIE Project Lab Room-6: FCFE Project Lab Room-7: Audiovisual Lab KeHaS Building Room-8: Project Lab Room-9: Multimedia Lab Room-10: Design Project Lab Block-10 Room-11: CAD-CAM Ghion Building: Room-12: Software Testing Lab Room-13: Advanced Programming Lab Room-14: Hardware Lab Room-15: Software Lab Room-16: Microprocessor and Interfacing Lab The Academic Program Office wishes all candidates a peaceful and successful exam. Note: 1) Only non-programmable calculators are allowed for Engineering Programs 2) Faculties should provide their students with A4 paper for rough calculations.

Exit Exam Schedule for tomorrow, Friday https://t.me/c/1803768150/1439

YOU ALL ARE INVITED!!
YOU ALL ARE INVITED!!

https://play.google.com/store/apps/details?id=com.portal_mobile.app 🌍 Attention Bahir Dar University Students! You are now eligible to become an Official International Member of True Culture University (TCU). 📲 Please download and install the TCU app. If you encounter any difficulties during the installation process, feel free to contact me or send me a DM for assistance. ✨ As an official member, you'll have the opportunity to connect and collaborate with international chapters in the United States, Brazil, Kenya, Mexico and all over the World. 🚨 This is your opportunity to become an official member of True Culture University and join a global community of young leaders and changemakers. Don't miss out—take the first step and become part of something bigger! For any questions or support, my inbox is always open.

📢 NOTICE TO COMPUTER SCIENCE AND IT_BED GRADUATING STUDENTS Dear Graduating Students, This is to inform all Computer Science and IT_BED students who will be taking the Exit Examination tomorrow (Thursday) that the room placement list has been posted on the notice board located at the Students' Main Gate of the Institute. Please check your assigned examination room in advance and make the necessary preparations before the exam. The BiT Student Union wishes all graduating students the very best in their examinations. Good Luck and Success to Our Graduates! BiT Student Union

ውድ እና የተወደዳችሁ የኒውትሪሽን (Nutrition) እና የሌሎችም ዘርፎች የብቃት ማረጋገጫ (Exit Exam) ተፈታኝ ተማሪዎቻችን ​በመጀመሪያ ዛሬ የፈተና ሂደቱን በይፋ የጀመራችሁ እና የመጀመሪያውን ከበድ ያለ ፈተና በጽናት ለተጋፈጣችሁ የኒውትሪሽን ተማሪዎቻችን በሙሉ፣ የታየው ፈተና መጠነኛ ፈታኝ ቢሆንም፣ እስከ ዛሬ ያሳለፋችሁትን የላብ እና የጥናት ዋጋ እንደማያሳጣው ሙሉ እምነት አለን። የመጀመሪያው ቀን ሁልጊዜም አዲስ እና የአቅጣጫ መለኪያ በመሆኑ ጫናው ከበድ ማለቱ ተፈጥሯዊ ነው፤ ነገር ግን ዋናው ነገር እናንተ የገጠማችሁን ፈተና በቁርጠኝነት ማለፋችሁ ነው። ​ዛሬን በድል ተሻግራችኋል፤ አሁን ትኩረታችሁን ሙሉ በሙሉ ወደ ቀጣዩ ውጤታማ ጉዞ ማድረጉ ላይ እንዲሆን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ​ነገ እና በሚቀጥሉት ቀናት ለምትፈተኑ ውድ ተፈታኞቻችን፡ 1⃣​የመጀመሪያው ቀን መረጃዎች እና የፈተናው ክብደት ስጋት ሊፈጥርባችሁ አይገባም! ይልቁኑ ይሄ ለእናንተ የተሻለ ዝግጁነትን እና የአዕምሮ ጥንካሬን የምታገኙበት አጋጣሚ ነው። 2⃣​በትጋታችሁ እመኑ፡ ላለፉት ዓመታት በዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁ የቀሰማችሁት እውቀት እና ያደረጋችሁት ዝግጅት ማንኛውንም ፈተና ለማለፍ በቂ ነው። ​ተረጋጉ እና በራስ መተማመናችሁን ሰንቁ፡ ፈተናን ግማሽ በግማሽ የሚያሸንፈው እውቀት ብቻ ሳይሆን የተረጋጋ የነፍስ እና የአዕምሮ ዝግጁነት ነው። ​የትናንት ፈተና የነገ ስኬታችሁ መነሻ ነው፡ የዛሬው ተሞክሮ ነገ ይበልጥ ጠንክራችሁ እንድትገቡ እና ጥያቄዎችን በብልሃት እንድትመልሱ ስልት የሚሰጣችሁ መሆን አለበት። ​ፈተናዎች የእናንተን እውነተኛ አቅም ለመለካት እንጂ እናንተን ለማስቆም የመጡ አይደሉም! ​የተማሪዎች ህብረት ፅህፈት ቤት ሁልጊዜም ከጎናችሁ ይቆማል። ይህንን የመጨረሻ ምዕራፍ በደመቀ ስኬት አጠናቃችሁ፣ ለራሳችሁ፣ ለቤተሰባችሁ እና ለሀገራችን ኩራት እንደምትሆኑ ሙሉ እምነታችን ነው። ​መልካም የፈተና ጊዜ! ስኬት ለሁላችሁም! ​የባህር ዳር ኢንስቲቱት ቴክኖሎጂ ተማሪዎች ህብረት ፅህፈት ቤት ሰኔ 2018 ዓ.ም

የነን ካፌው ብር ገብቷል ስለ ትግስታችሁ ከልብ እናመሰግ ናለን !!!