ch
Feedback
Orthodox⛪anthems ❤️‍🩹

Orthodox⛪anthems ❤️‍🩹

前往频道在 Telegram

ሃይማኖታዊ ወሬዎች, ምስሎች, ግጥሞች, ስዕሎች እና መዝሙሮች ብቻ Just impressing our soul by anthems❤️‍🩹🎶

显示更多
1 417
订阅者
+424 小时
+227 夊
+2530 夊

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服。
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+43
在1个频道中
五月 '26
+56
在1个频道中
Get PRO
四月 '26
+49
在3个频道中
Get PRO
三月 '26
+12
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+26
在1个频道中
Get PRO
一月 '26
+16
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+30
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+35
在1个频道中
Get PRO
十月 '25
+24
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+32
在1个频道中
Get PRO
八月 '25
+39
在5个频道中
Get PRO
䏃㜈 '25
+46
在5个频道中
Get PRO
六月 '25
+69
在3个频道中
Get PRO
五月 '25
+39
在3个频道中
Get PRO
四月 '25
+40
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+55
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+65
在3个频道中
Get PRO
一月 '25
+148
在7个频道中
Get PRO
十二月 '24
+162
在3个频道中
Get PRO
十一月 '24
+130
在3个频道中
Get PRO
十月 '24
+149
在4个频道中
Get PRO
九月 '24
+150
在2个频道中
Get PRO
八月 '24
+241
在10个频道中
Get PRO
䏃㜈 '24
+80
在5个频道中
Get PRO
六月 '24
+66
在1个频道中
Get PRO
五月 '24
+64
在7个频道中
Get PRO
四月 '24
+43
在2个频道中
Get PRO
三月 '24
+65
在2个频道中
Get PRO
二月 '24
+59
在9个频道中
Get PRO
一月 '24
+372
在10个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
15 六月+1
14 六月+6
13 六月+4
12 六月+3
11 六月+3
10 六月+2
09 六月+5
08 六月+5
07 六月+4
06 六月+2
05 六月+1
04 六月+2
03 六月+1
02 六月+3
01 六月+1
频道帖子
የማትገመት ሰው ሁን... ቤተሰቦችህ ጠዋት ተኝቷል ብለው ሲያስቡ ቤተክርስትያን ሄደህ ጸበል ተጠምቀህ ተመለስ

2
​በአርሲ ምድር በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለው ስልታዊ እና አረመኔያዊ ግድያ መቆም አልቻለም። ትናንትም፣ ዛሬም የንጹሃን ደም እንደ ጎርፍ እየፈሰሰ ነው፤ ታረዱ፣ ተሰደዱ፣ ማረፊያ
​በአርሲ ምድር በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለው ስልታዊ እና አረመኔያዊ ግድያ መቆም አልቻለም። ትናንትም፣ ዛሬም የንጹሃን ደም እንደ ጎርፍ እየፈሰሰ ነው፤ ታረዱ፣ ተሰደዱ፣ ማረፊያ አጡ። ​ይሁንና ከእነዚህ ወገኖቻችን እልቂት እኩል እያስደነገጠ ያለው የእኛ "የዝምታ ዋጋ" ነው። ​ዛሬ በአርሲ ያሉ ወንድም እህቶቻችን ዋጋ እየከፈሉ ያሉት በማንነታቸውና በእምነታቸው ብቻ ሳይሆን በእኛም ድንዛዜ ጭምር ነው። የአንድ ንጹህ ሰው ህይወት ሲቀጠፍ "ለኔ አልደረሰም" ብሎ በቸልታ ማለፍ፣ ነገ ተራው ወደ እኛ ቤት ሲመጣ የሚጮኽልን ሰው ማጣትን ያስከትላል። ​ሀዘናችን በ የፖለቲካ ትርክትና ፍርሃት ከቆለፈው አንደበታችን በላይ የንጹሃን ነፍስ አትበልጥም? ለገዳዮች ግድያውን እንዲቀጥሉበት ትልቁን የሞራል ስንቅ እየሰጣቸው ያለው የእኛ ግብረ-አልባነት እና ግድየለሽነት ነው። ​ ወገን በገዛ ሀገሩ፣ በገዛ ቀዬው ሲታረድ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ከገዳዮቹ እኩል የታሪክ ተጠያቂ ያደርገናል። ​የኦርቶዶክሳውያን ደም ማንም መጫወቻ ሊያደርገው የሚነሳበት ሜዳ መሆን የለበትም። መንግስትም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት የዜጎችን በህይወት የመኖር መብት የማስከበር ቀዳሚ ግዴታቸውን እንዲወጡ ድምጻችንን በአንድነት ልናሰማ ይገባል። ​ዛሬ ለአርሲ ካልጮህን፣ ነገ ለራሳችን የምናለቅስበት አንደበት እንኳ አይኖረንም። ዝምታችን ይበቃል፤ ፍትህ በአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን ለሚታረዱ ንጹሃን!
327
3
没有文字...
403
4
ስሙት❤️‍🩹
ስሙት❤️‍🩹
483
5
没有文字...
399
6
አንድ ቀን ሰዉ እንሆናለን🥺💔
355
7
አንድ ቀን ሰው እሆናለሁ .mp3
271
8
ክፍል ሁለት ፈቃደ እግዚአብሔር 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 የእግዚአብሔርን_ፈቃድ_የምናውቀው_እንዴት_ነው? እግዚአብሔር ፈቃዱን ለእኛ መግለጥ ፍላጎቱ ነው። ሥነ ፍጥረትን የፈጠረው፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን የሰጠው፣ በኋላም የባሕርይ ልጁን በሥጋ የላከው ፈቃዱን በግልጥ እንድናውቅ እንዲሁም በዚያ መሠረት እንድንመራና እንድንኖር ጽኑ ፍላጎቱና ፈቃዱ ስለሆነ ነው። ሐዋርያው “እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምስጢር አስታውቆናልና” ያለው ለዚህ ነው። /ኤፌ.፩፥፱/የእግዚአብሔርን ፈቃድ የምናውቅባቸው ዋና ዋና መንገዶች 1,✅መጽሐፍ ቅዱስ፦ እግዚአብሔር ፈቃዱ ምን እንደሆነ በቅዱሳት መጻሕፍት በተለያየ መንገድና ሁኔታ በግልጽ አስተምሮናል። ቅዱሳት መጻሕፍት የተሰጡበት ዋና ዓላማ ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት መኖር እንዳለብን? ለመዳን ምን ማድረግ እንዳለብን? እግዚአብሔር የሚወድደውና የሚጠላው ምን እንደሆነ? በአጠቃላይ የግዚአብሔር ፈቃድና ለሰው ልጆች ያለው ዓላማ ምን መሆኑን ለእኛ ለመንገርና ለማሳወቅ ነው። ይኽን በተመለከተ ቅዱሳት መጻሕፍት ብዙ ይናገራሉ። ነቢዩ ዳዊት “እግዚአብሔር ይነግሮሙ ለሕዝቡ በመጽሐፍ ወለመላእክቲሁኒ እለ ተወልዱ በውስቴታ፤ እግዚአብሔር ለሕዝቡ፥ በውስጧም ለተወለዱት አለቆቿ በመጽሐፍ ይነግራቸዋል” ይላል። /መዝ.፹፮፥፮/ እንዲሁም “ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ፣ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው” ይላል። /መዝ.፻፲፰፥፻፭/ የእግዚአብሔር ትእዛዝ አእምሯችንንና ልቡናችንን ፈቃዱን ለማወቅ ብሩህ የሚያደርግ ስለ መሆኑ ሲናገር ደግሞ፤ “ትእዛዙ ለእግዚአብሔር ብሩህ ወያበርህ አዕይንተ - የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል” ይላል። /መዝ.፲፰፥፰/ ቅዱስ ጳውሎስም ደቀ መዝሙሩን ጢሞቴዎስን “ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳት መጻሕፍትን አውቀሃል፤” በማለት ዋናውና መሠረታዊ የሆነው የእግዚአብሔር ፈቃድ ማለትም የእኛ መዳን በቅዱሳት መጻሕፍት አማካኝነት የተሰጠና የተገለጠ መሆኑን ተናግሯል። /፪ ጢሞ.፫፥፲፭/ ✅ስለሆነም የእግዚአብሔር ፈቃዱ ምን እንደ ሆነና እንዳልሆነ በቅዱሳት መጻሕፍት በግልጽ የተነገረ ነው። “የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንዴት አድርጌ ላውቅ እችላለሁ? ከየትስ አገኘዋለሁ? የሚል ጭንቀት ሊኖር አይገባም፤ በቅዱሳት መጻሕፍት በዓዋጅ የተነገረ ነውና። ለዚህ ደግሞ የእግዚአብሔር እስትንፋስ የሆኑትን የቅዱሳት መጻሕፍትን ቃል መብላትና በውስጣቸው ባለው በትምህርታቸው መጥገብ ግድ ይላል። ለነቢዩ ለሕዝቅኤል እንዲህ ተብሎ እንደ ተነገረ፦ “እርሱም፦ የሰው ልጅ ሆይ፥ ያገኘኸውን ብላ፣ ይህን መጽሐፍ ብላ፥ ሄደህም ለእስራኤል ቤት ተናገር አለኝ። አፌንም ከፈትሁ፣ መጽሐፉንም አጎረሰኝ። እርሱም፦ የሰው ልጅ ሆይ፥ አፍህ ይብላ፥ በምሰጥህም በዚህ መጽሐፍ ሆድህን ሙላ አለኝ። እኔም በላሁት፥ በአፌም ውስጥ እንደ ማር ጣፈጠ።” /ሕዝ.፫፥፩-፫/ ✅ቅዱሳት መጻሕፍትን ያልተማረ ሰው ፈቃደ እግዚአብሔርን ለማወቅ በእጅጉ ይቸገራል። በአኗኗራችን፣ በአነጋገራችን፣ በምርጫዎቻችን፣ ወዘተ የምናያቸው ምስቅልቅሎችና ከፈቃደ እግዚአብሔር ጋር የማይስማሙ ድርጊቶቻችን አብዛኛዎቹ በቅዱሳት መጻሕፍት የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ጠንቅቆ ካለመረዳት የሚመነጩ ናቸው። ስለዚህ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማወቅ ቅዱሳት መጻሕፍትን መማርና ለተማርነውም መታዘዝና ታማኝ መሆን ይገባል። በትንሹ ስንታመን፣ ላወቅነው ቃለ እግዚአብሔር አክብሮት ስንሰጥና በሕይወታችን መተግበር ስንጀምር ሌላውንም በቸርነቱ እየገለጠልንና እየረዳን ይሄዳል። ፈቃዱን ለማድረግ የሚጥርን ሰው እግዚአብሔር የበለጠውን የጥበቡን በር እየከፈተለት ይሄዳል። ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ፈቃዱን ሊያደርግ የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ ይህ ትምህርት ከእግዚአብሔር ቢሆን ወይም እኔ ከራሴ የምናገር ብሆን ያውቃል” ያለው ለዚህ ነው። /ዮሐ.፯፥፲፯/ ✅መጽሐፍ ቅዱሳዊውን እውነታ አዲስ በሚገጥሙ የተለያዩ ሁኔታዎች ላይ መተግበር መጽሐፍ ቅዱስ አጠቃላይ አቅጣጫ የሚያሳይና ዋና ዋና የሆኑ መሠረታዊ ጉዳዮችን የሚነግረን ነው እንጂ በእያንዳንዱ ዝርዝርና ተራ ጉዳይ ውስጥ ገብቶ እኛ በአእምሯችን እያብሰለሰልነው ያለውን ጉዳይ ሁሉ በቀጥታ “እንዲህ አድርግ” ወይም “አታድርግ” እያለ የሚነግረን አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ሀገራት “ሕገ መንግሥት” እንደሚሉት ያለ ነው። የሀገራት ሕገ መንግሥት የዚያን ሀገር ሕዝብ በተመለከተ አጠቃላይ መሠረቱን የሚጥልና ወሰኑንና ዳርቻውን የሚወስን ነው። ስለ እያንዳንዱ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊ፣ ፍትሐ ብሔራዊ፣ ወንጀል ነክ፣ ወዘተ ጉዳይ ገብቶ አንቀጽ የሚያትት አይደለም። ነገር ግን በዚያ በሕገ መንግሥቱ መሠረትነት የተለያዩ የማስፈጸሚያ ሕጎችና መመሪያዎች በረጃ በደረጃ በየዓይነቱ ይወጣሉ። ✅መጽሐፍ ቅዱስንም በዚህ ዓይነትሁኔታ ልናየው እንችላለን። ስለ መዳናችንና ዘለዓለማዊ ሕይወትን ለማግኘት ምን ማድረግ እንዳለብን በቅዱሳት መጻሕፍት በግልጽ ተነግሮናል። ከዚያ ውጭ ስላሉ ሌሎች ጉዳዮች ግን አጠቃላይ አቅጣጫና መመሪያ በመስጠት ዳሩንና ድንበሩን ያሳየናል እንጂ ዝርዝር ነገር ላይነግረን ይችላል። ለምሳሌም እያንዳንዱ ሰው በምን ዓይነት የሥራ መስክ መሰማራት እንዳለበት፣ ማንን ማግባት እንዳለበት፣ ምን ዓይነት ቤት እንደሚሠራ፣ ወዘተ አይነግረውም። ስለዚህም የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል በሚገባ በመማርና በማስተዋል መጽሐፍ ቅዱስ ላይ በግልጥ ያልተነገሩ ወይም በግልጽ ያልተናገረባቸው ጉዳዮች ሲገጥሙን ቃሉን በሚገባ የተረዳን ከሆነ ጥሩ መሠረትና መነሻ እናገኛለን። አጠቃላዩን የቅዱስ መጽሐፍ አቅጣጫና መመሪያ በዚያ በገጠመን ዝርዝር ጉዳይ ላይ በመተግበርና ከቃሉ አንጻር በመመዘን ምን ማድረግ እንደሚኖርብንና እንደማይኖርብን ፍንጭ እናገኛለን። ክፍል ሦስት ይቀጥላል,,,,,,,,,,, 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ❤ ✞_✞_✞ ❤ ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት              👇👇👇👇👇👇         👉@sewargegn27 👈             ☝️☝️☝️☝️☝️☝️ 💐አደራችሁን የእግዚአብሔር ቃል እንዲስፋፋ ቻናሉን ለየትኛውም የተዋሕዶ ልጆች እንዲቀላቀሉ join በማስደረግ ያበረታቱን፤አሁኑኑ join ያስደርጉ!!! https://t.me/yehiwotbirhan27
391
9
ፈቃደ እግዚአብሔር ክፍል-1 🌹🌹🌹🌹🌹🌹 #የእግዚአብሔር_ፈቃድ🦋➻➻🦋✅የእግዚአብሔር ፈቃድ (ፈቃደ እግዚአብሔር) ምንድን ነው?የእግዚአብሔር ፈቃድ ስንል እግዚአብሔር ወድዶና ፈቅዶ እንዲሆን የሚያደርገውን ነገርና እንዲሆንየሚፈቅደውን (የማይከለክለውን) ነገር ያመለክታል።የእግዚአብሔር ፈቃድ የእግዚአብሔር ባሕርይ የሚገለጥበት አንዱ መንገድ ነው። ለምሳሌ እግዚአብሔር ቸር ነው፣ መሐሪ ነው፣ ደግ ነው፣ ... ፈቃዱም እንዲሁ ነው፤ እርሱ ወድዶና ፈቅዶ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እነዚህ የባሕርያቱ መገለጫዎች፦ ቸርነት፣ ደግነት፣ ምሕረት ወዘተ አሉ።እንዲሁም የእግዚአብሔርን አሠራር የሚመራውና ክሂሉን የሚወስነው ፈቃዱ ነው። እግዚአብሔር የሚያደርገው ነገር ማድረግ የሚችለውን ሁሉ ሳይሆን ፈቃዱ የሆነውን ብቻ (ከባሕርዩ ጋር የሚስማማውን ብቻ) ነው የሚፈጽመው። ለምሳሌ እግዚአብሔር ዓለምን ማጥፋትና እንዳልተፈጠረ ማድረግ ይችላል። ነገር ግን ማድረግ ስለሚችል ብቻ (ይህን ለማድረግ ክሂል ስላለው ብቻ) አያደርገውም፤ ፈቃዱ ማጥፋት አይደለምና። ስለሆነም ማንኛውንም ጉዳይ እግዚአብሔር ማድረግ ስለሚችል ብቻ ያደርገዋል ማለት ስህተት ነው። እርሱ የሚያደርገው ከቅድስናውና ከባሕርዩ ጋር ተስማሚ በሆነ መንገድ ነው። ይኽ ደግሞ ፈቃደ እግዚአብሔር የምንለው ነው። የእግዚአብሔር ፈቃድ እጅግ ትልቅና ረቂቅ ነው። መጽሐፍም እንዲህ ይላል፦“የጥበቡን ምስጢር ቢገልጥልህ! ማስተዋሉ ብዙ ነውና። . የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ልትመረምር ትችላለህን? ወይስ ሁሉን የሚችል አምላክ ፈጽመህ ልትመረምር ትችላለህን? ከሰማይ ይልቅ ከፍ ይላል፤ ምን ልታደርግ ትችላለህ? ከሲኦልም ይልቅ ይጠልቃል፤ ምን ልታውቅ ትችላለህ? ርዝመቱ ከምድር ይልቅ ይረዝማል፥ ካባሕርም ይልቅ ይሰፋል። እርሱ ቢያልፍ፥ ቢዘጋም፥ ጉባኤንም ቢሰበስብ፥የሚከለክለው ማን ነው?” ኢዮ.፲፩፥፮-፲ ክፍል ሁለት ይቀጥላል,,,,,,,,,,
475
10
语音消息
487
11
https://youtu.be/-ZJ9DtjHU9s?si=i22DlaHQ-SM5q6Ps
694
12
"ማግባት ለሚሹ” የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡ ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡ አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡ እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡ እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡ እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡ የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡ - ዲያቆን ሔኖክ ጣሰው
728
13
没有文字...
0
14
አለማዊ channel ያላችሁ forward አርጉልኝ
0
15
ፕሮቴስታንት እና ሙስሊም ወንድም እና እህቶች ስለ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የማወቅ ፍላጎት ያላችሁ ወይም ደሞ ወደዚ ሕይወት መቅረብ የምትፈልጉ እንዲሁም ኦርቶዶክስ ሆናችሁ ጥያቄዎች ያልተመለሰላቹ @yematbelawef dm ፃፉልኝ የማቀውን ለማስተማር ዝግጁ ነኝ
0
16
The words make my feel right 🤌🥹
The words make my feel right 🤌🥹
0
17
የት ጠፋቹ እሺ😭
0
18
没有文字...
0
19
Vc ገብተን እንተዋወቅ እንዴ guys ?
0
20
没有文字...
0