2 792
订阅者
+2024 小时
+727 天
+18630 天
帖子存档
2 796
የትዳር ጥያቄዬን አልተቀበለችኝም በማለት ፍቅረኛውን የገደለው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ፡፡
በአርሲ ዞን ዴራ ወረዳ የተወለደው ናፍቆት ሙሉጌታ የ29 ዓመት ሲሆን ቤተልሄም ሃይሉ ከተባለች የ23 ዓመት ወጣት ጋር አብሮ አደግና የፍቅር ግንኙነት እንደነበረው የአዳማ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሙኑኬሽን ፅ/ቤት ሃላፊ ምክትል ኮማንደር ታምራት ጌታሁን ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ይሁን እና የነበራቸው ግንኙነት በስራ ምክንያት እሩቅ እንደነበረ ተጠቁሟል ። ቤተልሄም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች በቴክኒክ እና ሞያ የሴቶች የውበት ስልጠና ዘርፍ ሰልጥና በአዳማ ከተማ የሴቶች የውበት ሳሎን በመስራት እንደምትተዳደር ተገልጿል ።ናፍቆት ሙሉጌታም በስራ አጋጣሚ ወደ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ጉባ አባይ ግድብ የሄደ ሲሆን በፍቅር ግንኙነታቸው ላይ ናፍቆት ቶሎ ወደ ትዳር እንግባ የሚል ጥያቄ ሲያነሳ ዝግጁ አደለሁኝም ሰርቼ መለወጥ አለብኝ የሚል ምላሽ በማግኘቱ ምክንያት በመሀከላቸው አለመግባባት ይፈጠራል።
ናፍቆት የቤተልሄምን የትዳር ሽሽት ነገ ጥላኝ ለመሔድ ነው የሚል ጥርጣሬ በመያዝ ከጉባ አባይ ግድብ በስራ ምክንያት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ አዳማ በመምጣት ያገኛታል። አብረው ቆይተው ምሽት ላይ ወደ ትውልድ ቦታቸው ዴራ ለመሄድ ተስማምተው በህዝብ ትራንስፖርት ተሳፍረው በመጓዝ በመሃል ለመዝናናት አዋሽ መልካሣ ከተማ እንደወረዱ ም/ኮማንደር ታምራት ጌታሁን ገልጸዋል።
ለእረፍት በወረዱበት ሰዓት የትዳር ጥያቄዮን አልተቀበለችም በሚል ምክንያት በስለት ወግቶ ከገደላት በኋላ ወንዝ ውስጥ እንደጣላት ነው የተገለጸው። የዚህ አሳዛኝ የወንጀል ድርጊት በዚህ መንገድ ከተፈፀመ በኋላ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን በተገቢ ማስረጃዎች በማጠናከር ለአቃቢ ሕግ ያስተላልፋል።
አቃቢ ሕግም በከባድ የሰው መግደል ወንጀል ክስ ይመሠርታል። የተመሠረተውን የወንጀል ክስ የተመለከተው የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐምሌ ወር 2018 ዓም በዋለው ችሎት ተከሣሽ ናፍቆት ሙሉጌታ ሰው ለመግደል አቅዶና የወደፊት የትዳር አጋሩ ለመሆን በተዘጋጀች ልጅ ላይ የፈፀመው የግድያ ወንጀል ከባድ እጅግ ነውረኛ እና ዘግናኝ መሆኑን ጠቅሷል።
በዚህም መሰረት በሁለት የክስ ማቅለያዎች በ18 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ሲሉ ምክትል ኮማንደር ታምራት ጌታሁን ለብስራት ሬዲዮ ጨምረው ተናግረዋል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል
2 796
በዝዋይ ማረሚያ ቤት12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከተፈተኑ ከ23 ታራሚ ተማሪዎች 22 አለፉ፡፡
👉ከፍተኛው ውጤት 531 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል በ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 23 ታራሚዎች መካከል 22ቱ ከ300 በላይ ውጤት በማምጣት ማለፋቸውን ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን አስታውቋል።
የማዕከሉ ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ፍቅሬ አብዩ የማዕከሉ የትምህርት ሥራ በታራሚዎች ላይ አዎንታዊ ለውጥ ከማምጣቱ ባለፈ በትምህርት ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛልም ብለዋል።
በዚህ መሠረት በ2018 ዓ.ም. የ6ኛና የ8ኛ ክፍል ትምህርት የተከታተሉ ታራሚ ተማሪዎችን 100 በመቶ ማሳለፍ መቻሉን ዳይሬክተሩ አስታውሰው፤ በተመሳሳይም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 23 ታራሚዎች መካከል 22ቱ ከ300 በላይ ውጤት በማምጣት ማለፋቸው የማዕከሉ የትምህርት ሥራ ውጤታማነትን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከፈተናው ተሳታፊዎች መካከል 22 ተማሪዎች የተሳካ ውጤት ማምጣታቸው፣ ታራሚዎች በትምህርት እንዲበረታቱና ወደ ማኅበረሰቡ ሲመለሱ ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ ለማስቻል የሚደረገው የማረምና የማነጽ ሥራ አንዱ አካል መሆኑን ዳይሬክተሩ አመላክተዋል።
የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ታራሚዎች የእርምት ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ፣ የተለያዩ እውቀትና ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ እንዲሁም ከተፈቱ በኋላ በራሳቸውና በማኅበረሰባቸው ላይ ጠቃሚ ሚና እንዲጫወቱ የተለያዩ የማረምና የማነጽ ፕሮግራሞችን እያከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።
የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል በትምህርት ያስመዘገበው ውጤት፣ ታራሚዎችን በማረምና በማነጽ ሂደት ትምህርት ያለውን ወሳኝ ሚና የሚያሳይ ስኬት መሆኑንም ም/ኮማንደር ፍቅሬ አብዩ ተናግረዋል፡፡ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤትም ተጠቃሎ ሲታወቅ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡፡
ይሕ ውጤት የዝዋይ ማረሚያ ቤት ብቻ ሲሆን በአዲስ አበባ የሚገኙው የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ታራሚዎች ውጤት በቀጣይ እንደሚገለጽ ማረሚያ ቤቱ አስታውቋል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
