2 560
Suscriptores
+1024 horas
+357 días
+13230 días
Archivo de publicaciones
2 560
በሚኒሶታ በሚገኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ከባድ የእሳት አደጋ ደረሰ::
ዛሬ ሰኞ ጁላይ 13 ቀን 2026 ዓ.ም (ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም) በሮዝማውንት ሚኒሶታ በሚገኘው የየሚኒሶታ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ በተነሳ ከባድ የእሳት አደጋ በህንጻው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በቁጥር 3285 144th St. W. ወደሚገኘው የቤተክርስቲያኑ ህንፃ የደረሱት በግምት ከጠዋቱ 4፡45 ላይ ነበር።
ከአደጋው የተነሳው ኃይለኛ እሳትና ጥቅጥቅ ያለ ጥቁር ጭስ በአቅራቢያው ካሉ የመኖሪያ መንደሮች እና ከሮዝማውንት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት (Rosemount Elementary School) በግልጽ ይታይ ነበር።
በህንፃው ላይ ከፍተኛ መዋቅራዊ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ በኃይለኛው ሙቀት ምክንያት የጣራው ትልቅ ክፍል ተደርምሷል። የእሳት አደጋ ተከላካዮች እሳቱን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ለሰዓታት መረባረብ አስፈልጓቸዋል።
አደጋው በደረሰበት ወቅት በህንፃው ውስጥ ምንም አይነት ሰው እንዳልነበረ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አረጋግጠዋል።
የእሳቱ መነሻ መንስኤ በውል አልታወቀም። የአካባቢው የህግ አስከባሪዎች እና የእሳት አደጋ ክፍሎች አደጋው ምን እንደቀሰቀሰው ለማወቅ ሙሉ ምርመራ ጀምረዋል።
በዚህ እጅግ አስቸጋሪ ወቅት ሃሳባችንና ጸሎታችን ከደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ምዕመናን፣ አገልግሎት አጋሮች እና አመራሮች ጋር ይሁን።
Via CBS News
ጉርሻ
2 560
የ69 ዓመታቸው አዛውንት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ገብተዋል።
በትምህርት ዓለም ውስጥ ዕድሜ ገደብ እንደሌለው በተግባር ያሳዩት የ69 ዓመቱ አዛውንት አባባ ወልደየስ አያና አሻቦ ዘንድሮ በሚሰጠው 4ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ላይ በመቀመጥ አዲስ ታሪክ አስመዝግበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ልዩ ስሟ ዳንጋራ ሳላጣ በተባለች ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አባባ ወልደየስ፣ ቀደም ሲል ማህበረሰባቸውን በቀበሌ አስተዳዳሪነት ከስድስት ዓመታት በላይ በታማኝነት ያገለገሉ የሀገር ሽማግሌ ናቸው።
በደርግ ዘመን በትውልድ አካባቢያቸው እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ ተምረው ቢያጠናቅቁም፣ በወቅቱ በነበረው የትምህርት አደረጃጀት፣ የአገዛዝ ሥርዓትና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአቅራቢያቸው አለመኖር ምክንያት ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደው ነበር።
ይሁን እንጂ ለትምህርት ያላቸው ፍቅርና ቁጭት ሳይቀንስ ከረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ በ2015 ዓ.ም ወደ ገበታ በመመለስ ከ9ኛ ክፍል ጀምረው በመማር ዛሬ ለዚህ ትልቅ ሀገር አቀፍ ፈተና ለመብቃት ችለዋል።
አባባ ወልደየስ የ6 ልጆች አባት ሲሆኑ፣ የቤተሰብ ኃላፊነትንና የማህበረሰብ አገልግሎትን ከትምህርት ጉዟቸው ጋር ጎን ለጎን አስማምተው ማስኬዳቸው ልዩ ያደርጋቸዋል።
ይበልጡኑ ደግሞ ከገዛ ልጆቻቸው ጋር በአንድ የመማሪያ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው መማራቸውና ለፈተናውም በጋራ መዘጋጀታቸው ልዩ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገራሉ።
እኩዮቻቸው ወደ ጡረታ በሚገቡበት ዕድሜ መጽሐፍ አንግበው ወደ ትምህርት ቤት የተመላለሱበት ዋና ዓላማ በመንግሥት ተቀጥሮ ለመሥራት ሳይሆን፣ አሁን የሚሰሩትን የግብርና ሥራ በዘመናዊ መንገድ ለማሻሻልና በተሻለ ሁኔታ ለማምረት የሚያስችላቸውን ሳይንሳዊ ዕውቀት ለማግኘት እንደሆነ ያስረዳሉ።
ይህ አስደናቂ ታሪክ “የተማረ ሰው የሥራ ዕድል ፈጣሪ እንጂ ተቀጣሪ ብቻ መሆን የለበትም” የሚለውን ዘመናዊ ትርክት በተግባር የሚያሳይ ነው።
በትጋትና በጽናት ከተጓዙ ዕድሜ ለማንኛውም ስኬት እንቅፋት ሊሆን እንደማይችል ለሚያነበውና ለወጣቱ ትውልድ ትልቅ መነሳሻ እንደሚሆን ይታመናል።
የዩኒቨርሲቲው ህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኝነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት እንዲሁም መላው የፈተና አስተባባሪ ግብረ-ሃይል ለአባባ ወልደየስ መልካም ምኞቱን እየገለጸ፣ ይህ ፈተና የረጅም ጊዜ ራዕያቸውን የሚያሳኩበት እንዲሆን ተመኝቷል።
Via ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ
2 560
በጂንካ ማረሚያ ተቋም የሚገኙ የህግ ታራሚዎች የ12ኛ ክፍል ፈተናን እንዳይወስዱ በመደረጋቸው ቅሬታ ፈጥሮባቸዋል ተባለ
በጂንካ ማረሚያ ተቋም የሚገኙ የህግ ታራሚዎች የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን እንዲወስዱ ወደ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተልከዉ እንደነበር ተቋሙ አስታውቋል ።
የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለዉ ነሬሬ ለብሰራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ለመዉሰድ 7 የህግ ታራሚዎች ወደ ጂንካ ዩኒቨርስቲ ተልከዉ በመጀመሪያው ቀን ፈተናዉን ከወሰዱ በኃላ ቀሪዎቹን ፈተናዎች ሳይፈተኑ መቅረታቸው ተገልጿል ።
ሀምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ፈተናዉን እንደሚወስዱ ቃል ተገብቶ የነበረ ቢሆንም ከትምህርት ሚኒስቴር ትዕዛዝ አልመጣልንም በሚል ምክንያት ፈተናዉን ሳይወስዱ መቅረታቸዉ ተገልጿል።ይህም በታራሚዎች ዘንድ ቅሬታ መፍጠሩን የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ገልጿል ። በመሆኑም የሚመለከተዉ አካል ርብርብ አድርጎ በዚህ ዓመት ፈተናዉን የሚወስዱበት ሁኔታ እንዲፈጠር ማረሚያ ተቋሙ ጥሪ አቅርቧል ።
ብስራት ሬዲዮ በቀጣይ የሚመለከተውን አካል አናግሮ በሌላ ዘገባ ምላሽ ይዞ የሚመለስ ይሆናል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
2 560
የሱዳን ፍርድ ቤት የአር ኤስ ኤፍ መሪን በሌሉበት የሞት ፍርድ በየነባቸው
የሱዳን ፀረ-ሽብርተኝነት ፍርድ ቤት የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (አር ኤስ ኤፍ) መሪ መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ፣ በስፋት ሄሜቲ በመባል የሚታወቁት፣ በቀድሞው የምዕራብ ዳርፉር ገዥ ካሚስ አብደላህ አባካር ግድያ ምክንያት እሁድ እለት በሌሉበት የሞት ፍርድ ፈርዶባቸዋል።በፖርት ሱዳን የሚገኘው የፀረ-ሽብርተኝነት እና የክልል ፍርድ ቤት በሌሉበት የአር ኤስ ኤፍ ምክትል መሪ እና የሄሜቲ ወንድም አብደል ራሂም ሃምዳን ዳጋሎን ጨምሮ እና ሌሎች 14 ተከሳሾች የሞት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ይህ ውሳኔ በኤፕሪል 2023 በሱዳን ጦር እና በፈጣን ድጋፍ ሰጪ ቡድኑ መካከል ግጭት ከተፈጠረ ወዲህ በአር ኤስ ኤፍ መሪዎች ላይ የተላለፈ የመጀመሪያው የፍርድ ቤት ውሳኔ ነው።ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹን በጦር ወንጀሎች፣ በሰብአዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች፣ የዘር ማጥፋት ፣ በሰዎች እና በንብረት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ጨምሮ በተለያዩ ክሶች ጥፋተኛ አድርጎባቸዋል።ሄሜቲን ወንጀሎቹን በማቀድ እና በመሳተፍ ተጠያቂ አድርጓቸዋል።
ከሌሎቹ ተከሳሾች መካከል አልጎኒ ሃምዳን ዳግሎ ሙሳ፣ ሌላው የሄሜቲ ወንድም አል-ቁኒ በመባል የሚታወቀው ሲሆን የምዕራብ ዳርፉር የአር ኤስ ኤፍ አዛዥ አብደል ራህማን ጁማ ይገኙበታል። በምዕራብ ዳርፉር ዋና ከተማ ኤል ጂንያና ውስጥ አርኤስኤፍ በሲቪሎች ላይ ጥቃት ፈጽሟል ሲል የሱዳን ጦር ከሷል። ጦሩ አክሎም ቡድኑ የዳርፉን ገዢ ገድሎ አስከሬኑን ቆርጦ እንደጣለ ከሷል፣ አር ኤስ ኤፍ በወቅቱ ክሱን አስተባብሏል።
የሱዳን ባለስልጣናት እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አርኤስኤፍን በኤል ጂንያና ውስጥ ሰፊ ጭካኔ ፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል፣ ይህም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን መግደል እና በሺዎች የሚቆጠሩ የማሳሊት ማህበረሰብ አባላትን ማፈናቀልን ያካትታል።
በስምዖን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
2 560
#ኢራን ለ #አሜሪካ ጥቃቶች በሰጠችው የአፀፋ ምላሽ በባሕረ ሰላጤው ሀገራት በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማት ላይ በርካታ ጥቃቶችን ሰነዘረች
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) በ #ኩዌት፣ በ #ባሕሬን፣ በ #ጆርዳን እና በ #ኦማን በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማት ላይ የተቀናጀ የሚሳይል እና የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃቶች ማድረሱን ገለጸ። ጥቃቶቹ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኙ የኢራን ወታደራዊ ሥፍራዎች ላይ በቅርቡ ለተሰነዘሩት የአሜሪካ ጥቃቶች የተሰጡ የአጸፋ ምላሾች መሆናቸውን አልጄዚራ እና ኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) በኩዌት የሚገኙትን ዓሊ አል ሳሌም እና አሕመድ አል-ጃበር የአየር ኃይል ካምፖችን ማጥቃቱን የገለጸ ሲሆን፥ ጥቃቱ የሚሳይል ሥርዓቶችን፣ የነዳጅ ማጠራቀሚያዎችን፣ የፓትሪዮት የአየር መከላከያ ባትሪዎችን፣ ራዳሮችን፣ ምሽጎችን እና መጋዘኖችን ኢላማ ያደረገ መሆኑን አስታውቋል። በተጨማሪም ጥቃቶቹ በባሕሬን የሚገኘውን ሼክ ኢሳ የአየር ኃይል ካምፕ እና በጁፌር የሚገኘውን የአሜሪካ አምስተኛ የጦር መርከብ ሰፈር እንዲሁም በጆርዳን የሚገኘውን ልዑል ሐሰን የአየር ኃይል ካምፕ እና በኦማን የሚገኙ ራዳሮችን መምታታቸውን ገልጿል።
ኩዌት የአየር መከላከያዋ «የአየር ላይ ኢላማዎችን» ማክሸፉን የገለጸች ሲሆን፥ ጆርዳን በበኩሏ በርካታ ሚሳይሎችን ማክሸፏንና ምንም ዓይነት ከባድ ጉዳት ወይም ከፍተኛ ውድመት አለመድረሱን አስታውቃለች።
ኢራን ጥቃቶቹ በባንደር አባስ፣ በቄሽም ደሴት፣ በሲሪክ፣ በጃስክ እና በሌሎች የባሕር ጠረፍ አካባቢዎች አቅራቢያ በሚገኙ ወታደራዊ እና የክትትል መሠረተ ልማቶች ላይ በቅርቡ አሜሪካ ለሰነዘረችው ጥቃት ምላሽ መሆናቸውን የገለጸች ሲሆን፥ ቴህራን ጥቃቶቹ በሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይም ጉዳት ማድረሳቸውን ተናግራለች።
ሮይተርስ እንደዘገበው የቅርብ ጊዜዎቹ ጥቃቶች በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ያለውን ፍጥጫ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባብሱ ሲሆን፥ ኢራን በባሕረ ሰላጤው በሚገኙ የአሜሪካ ተቋማት ላይ የሚሳይል እና የድሮን ጥቃቶችን በመሰንዘር የሆርሙዝ ወሽመጥን ለመዝጋት በድጋሜ ዝታለች። ሆኖም የአሜሪካ ባለሥልጣናት ምንም እንኳን ውጥረቱ ቢጠናከርም ስልታዊው የውኃ መስመር ለንግድ መርከቦች ክፍት እንደሆነ ቀጥሏል ብለዋል።
==================
2 560
የዓለም ባንክ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በኢትዮጵያ ለሚያከናውናቸው ድጋፎች የፖሊሲ ለውጦች አደረገ
የዓለም ባንክ ከ2027 እስከ 2036 ያለውን የ10 ዓመታት የአጋርነት ማዕቀፍ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥሉት 10ዓመታት ቅድሚያ ይሰጣቸው የነበሩ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ሙሉ በሙሉ ከዕቅዱ ውጪ ማድረጉን አስታወቀ፡፡
ሪፖርተር የተመለከተው የዓለም ባንክ አዲስ የስትራቴጂ ሰነድ ትኩረቱን በዋናነት በየዓመቱ ወደ ሥራው ዓለም ለሚቀላቀሉ ወደ ሁለት ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ አድርጓል፡፡
ግዙፍ በመንግሥት የሚመሩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን፣ ዋና ዋና የአስፋልት መንገዶችንና የቱሪዝም ዘርፍን በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሙሉ በሙሉ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ፕሮጀክቶች ዝርዝር ውጪ አድርጓቸዋል፡፡
👉የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ከዕቅዱ ውጪ እንዲሆኑ የተደረጉት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ባደረገችው ኢንቨስትመንት በቂ የማመንጨት አቅም ስላላት ሲሆን፣ የቱሪዝም ዘርፍ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለው የፀጥታና የመሠረተ ልማት ሁኔታ መሻሻል እስከሚታይበት ድረስ ከዝርዝሩ ውጪ እንዲሆን መደረጉን ጠቁሟል፡፡
የከተማ አውራ ጎዳናዎችን የመገንባት ዕቅድም ቀርቶ፣ በተመሳሳይ መልኩ የገጠር መንገዶችን ወደ ማስፋፋት እንዲዞር የተደረገ ሲሆን፣ ይህም አርሶአደሩ ምርቱን በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲያቀርብ ለማገዝ፣ የጉምሩክ አሠራርን ለማዘመንና የወጪ ንግድ ወጪን ለመቀነስ ያለመ አዲስ መዋቅራዊ አቅጣጫ መሆኑ ተመልክቷል።
👉ባንኩ በቀጣይ እቅዶቹ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ማስተካከል፣ የኃይል መቆራረጥን መቀነስና በሚሊዮኖች ለሚቆጠር ሕዝብ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን አስተማማኝ ማድረግ የሚሉት ይገኙበታል፡፡
