2 467
Suscriptores
+824 horas
+357 días
+8530 días
Archivo de publicaciones
2 469
በሙዝ ንግድ የምትተዳደር አንዲት እናት መንገድ ላይ ያገኘችውን ገንዘብ ወደ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ አስረከበች።
የታማኝነት እና የቅንነት ተምሳሌት — ከዶዮገና ከተማ!
ድህነት ማለት የገንዘብ ማጣት እንጂ የማንነት እና የሞራል መውደቅ አይደለም!"
ዛሬ ሁላችንም ልንማርባት የሚገባን፣ በቅንነቷ እና በጽናትዋ ሁላችንንም ያስተማረች ድንቅ እናትን ልናስተዋውቃችሁ ወደድን።
ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በከምባታ ዞን ዶዮገና ከተማ ውስጥ የምትኖር፣ በሙዝ ንግድ የምትተዳደር አንዲት ታጋይ እናት መንገድ ላይ ወድቆ የነበረ ገንዘብ (ብር) ታገኛለች።
ኑሮዋን ሙዝ በመሸጥ ሌት ተቀን የምትለፋ እናት ብትሆንም፣ "የሰውን አልፈልግም፤ ባለቤቱ እየተጨነቀ ይሆናል" በማለት ያገኘችውን ገንዘብ ሳታንገራግር በቀጥታ ወደ ዶዮገና ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት በመውሰድ በታማኝነት አስመዝግባለች።
ይህች እናት በዚህ በፈተና በበዛበት ዘመን፣ እውነተኛ ሀብት የሰው ልጅ ማንነት እና ህሊና መሆኑን በተግባር አሳይታለች። የላቧን እንጂ የሰውን የማትመኝ፣ ለልጆቿም ሆነ ለሀገር ትልቅ ተምሳሌት የሆነች ድንቅ የኢትዮጵያ እናት!
ገንዘቡ የጠፋባችሁ ወይም ባለቤቱን የምታውቁ ሰው፣ ትክክለኛ እና ህጋዊ መረጃ ይዛችሁ በዶዮገና ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በመቅረብ ገንዘባችሁን መረከብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
እባካችሁ ይህ መልዕክት ለባለቤቱ እንዲደርስ #Share በማድረግ ተባበሩን!
ፈጣሪ ይህችን እናት በጤና፣ በበረከት እና በኪሷ ሞልቶ ይባርካት! ታማኝነት መቼም ቢሆን አይረክስም።
#ዶዮገና #ከምባታ #ታማኝነት #ኢትዮጵያዊነት
Via ዶዮገና ከተማ ፖሊስ ጣቢያ
2 469
ወገንተኛ እገዳ ሰላም ማምጣት ኣይችልም- ህወሓት‼️
ትግራይ ህዝብዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ
አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ያላት የሰላም አቋም እና የፕሪቶርያ ዘላቂ የተኩስ ማቆም ስምምነት እንዲፈረም የነበራት መሪ ተዋናይነት እና ለትግራይ ህዝብ ሰላም እንዲያገኝ ያሳየቺው ተነሳነት እንደሚያደንቅ ያመለከተው የህወሓት መግለጫ፤ በፌደራል መንግስት ተደጋግሞ የተጣሰው የፕሪቶርያው ስምምነት ሳይታይ ህወሓት ላይ የጉዞ እገዳ ማኖሩ ፍትሓዊነት የጎደለውና ኣሳሳቢ መሆኑን በአቋም መግለጫው አመላክቷል፡፡
ጥፋተኛው አካል ሳይጠየቅ በህወሓት ላይ ብቻ ያነጣጠረ እገዳ ፍትሓዊነት የጎደለው መሆኑን ያመለከተው መግለጫው ፤በእብደዚህ ዓይነት ኣድላዊ አቋም ሰላም ማስፈን እንደማይቻል አመልክቷል፡፡
እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ሕዳር 2 ቀን 2022 የተፈረመው የፕሪቶርያው ዘላቂ የተኩስ ማቆም ስምምት፤ በሁለቱም ተፈራራሚ አካላት እንዲፈፀሙ በግልፅ ከተቀመጡ ነጥቦች መካከል፤ ህገመንግስታዊ ስርዓት ወደ ነበረበት መመለስ፣ የተፈናቀሉና የተሰደዱ ወገኖች ወደቦታቸው መመለስ፣ ከመከላከያ ሰራዊት ውጭ የሆኑ ታጣቂዎች ከትግራይ ግዛቶች ማስወጣት፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱና የህወሓት ሕጋዊ እውቅና እንዲሁም ፖለቲካዊ ቁመና መመለስ መሆኑ ያስታወሰው መግለጫው፤ እነሲህ ስምምነቶች በፌደራል መንግስት ምክንያት ያልተተገበሩ መሆናቸውን ያስረዳል፡፡
የትግራይ ህዝብ ሰላም ወዳድና ተሎ ወደቄዬው እንዲመለስ እዲሁም የመልሶ ግንባታ ስራዎች ተሰርቶለት ወደ መደበኛ ህይወቱ እንዲመለስ ያለው ፍላጎት ተግባራዊ እንዲሆን የፕሪቶርያ ስምምነት ተግባራዊነት በጉጉት ሲጠባበቅ መቆየቱን የመለከተ መግለጫው፤ ስምምነቱ ከመተግበር ይልቅ በትግራይ ህዝብ ዘንድ ኢ-ተገማቲእና አለመተማመን እንዲሰፍን ምክንያት ሆኖ መቆየቱ በፅሑፉ ተመላክቷል፡፡
ስምምነቱ ሶስት ዓመታት ያሳለፈ ቢሆንም፤ ወሳኝ የስምመነት ነጥቦቹ ሳይተገበሩ መቆየታቸውን ያመለከተው መግለጫው፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተጋሩ ወደ ቂያቸው መመለስ እንዳልቻሉ፣ የተጠያቂነት ሂደት እንዳልተቋቋመና የኢትዮጵያ መንግስት በቅርብ ከተካሄደው ሃገራዊ ምርጫ ውጪ እንድትሆን መደረጉን ኣመላክቷል፡፡
የሰራተኞች ደመወዝ፣ ነዳጅ፣ የባንክ አገልግሎት እና ሰብአዊ እርዳታዎችን የመሳሰሉ መሰረታዊ አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ምንግስተ በኩል እገዳ ተደርጎባቸው እንደሚገኝ እንዲሁም በመጠሊያዎች የሚገኙ ወገኖች በከፋ የኖሮ ሁኔታ ይገኛሉ ያለው መግለጫው፤ በረሃብ መሞትና መከላከል በሚቻሉ በታዎች እየተጠቁ መሆኑ ያስረዳል፡፡
የትግራይን ህዝብ አስርቦ ለማጥፋት በፖሊሲ ደረጃ እየሰራ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት አረሜናዊ ተግባር ሆኖ እየቀጠለ እንደሚገኝ ያስረዳው የህወሓት መግለጫ፣ የትግራይ ህዝብ ስቃይ ከህወሓት ጋር አያይዞ መገለፅ ተገቢነት የጎደለው መሆኑን አስረድቷል፡፡
በየመጠልያው የሚገኙ የምዕራብ ትግራይ ተፈናዮች ወደ ቦታቸው እንዳይመለሱ ዋነኛ ተጠያቂ ለማወቅ፤ መሰረታዊ አገልግሎቶች፣ እንደሁም በፕሪቶርያ ስምምነቶች የተቀመጡ የሰብኣዊ አገልግሎት ጉዳዮች እንዳይፈፀሙ በፖሊሲ ደረጃ ከልከሎ የሚገኘው የኢትዮጵያ መንግስት ማወቅ በቂ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው፤ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ዳሰሳ በማከናወን እውነታው መረዳት እንደሚቻል ያስረዳክል፡፡
የፌደራል መንግስት ወሳኝ የሚባሉ የፕሪቶርያው ዘላቂ ተኩስ ማቆም ስምምነቶች እንዳይፈፀሙ አንቆ መያዙን ለመረዳት የሚያወጣቸው የተለያዩ ደብዳቤዎችና በመሬት ላይ የሚታዩ ተግባሮቹ መመልከት በቂ ማስረጃዎች መሆናቸው ያመለከተው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ግለጫ፤ በትግራይ ህዝብ ላይ የተጣሉ ክልከላዎች አጠቃላይ ህዝቡ ከመጉዳታቸው በተጨማሪ በወታደራዊ ማስፈራራትና በተደጋጋሚ በፈፀማቸው የድሮን ድብደባዎች እንዲሁም ትግራይን ለማድቀቅ በተከተለው የፖለቲካ ተነጽሎ የትግራይ ህዝብ በፌደራል ስርዓቱ ያለ ውክልና እንዲቀር ማድረጉን አስረድቷል፡፡
ስምምነቱ እንዳይተገበር ሙሉ በሙሉ የዘጋ አከል አቅልሎ በማየት፤ ችግሩ ባልፈጠረ ተደራዳሪ ላይ ተጠያቂ በማድረግ የሰላም ሂደት ለመተግበር ያለው ዕድል አናሳ መሆኑ ያመለከተው መግለጫው፤ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ የሚችለው ገለልተኛ፣ መርህን በመጠበቀና የጋራ ተጠያቂነት ሲኖር መሆኑን አስረድቷል፡፡
የትግራይ ህዝብ ሰላም ወዳድ በመሆኑ፤ ህወሓት በሰላም ጉዳይ ያለው አቋም የፀና በመሆኑ ያብራራው መግለጨው፤ የፕሪቶርያው ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዲተገበር የፌደራል መንግስት ለስምምነቱ ተገዥ በመሆን የሰራተኞች ደመወዝ፣ የባንክ አገልግሎት፣ የነዳጅ አቅርቦት እና የሰብኣዊ ጉዳይ ተደራሽነት ማረጋገጥ ኣለበት ብሏል፡፡
በትግራይ ህገመንግስታዊ ግዛት የሚገኙ ወራሪዎች ሙሉ በሙሉ በማስወጣት፣ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደቄያቸው ለመመለስ የሚያስችል የጊዜ ሰሌዳ ማኖር እንዲሁም የህወሓት ህጋዊነት ለመመለስ የፕሪቶርያው ስምምነት መተግበር ይኖርበታል ያለው የህወሓት መግለጫ፤ በትግራይ ህዝብ ስቃይና መከራ የተሳተፉ አካላት ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የፌደራል መንግስት ቁርጠኝነት መታየት ይኖርበታል ብሏል፡፡
#አዩዘሀበሻ
=====================
2 469
ታክስ ከፋዮች ከደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት ጋር ተስማሚ የኤሌክትሮኒክ ሽያጭ መመዝገቢያ እንዲኖራቸው የሚያስገድድ መመርያ ወጣ
የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ሕጉ መሠረት የሒሳብ መዝገብ የሚይዙ ታክስ ከፋዮች፣ ራሱ ካበለፀገው የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት ጋር ተስማሚ የኤሌክትሮኒክ ሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት እንዲጠቀሙ የሚያዝ መመርያ ተግባራዊ አደረገ።
ገቢዎች ሚኒስቴር የራሳቸውን የሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት አበልፅገው ወይም ከአልሚዎች ገዝተው በማስፈቀድ ለሚጠቀሙ ታክስ ከፋዮች ዕውቅና እንዲያገኙ፣ የክትትልና ቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋትና አሠራራቸውን በሕግ ለመወሰን የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ አስተዳደር ሥርዓት መመርያ ቁጥር 1142/2018ን ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩ ተገልጿል፡፡
የኤሌክትሮኒክ ሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት ስለመጠቀም በሚደነግገው የመመርያው አንቀጽ 19፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ካዘጋጀው የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት ጋር ተስማሚ የኤሌክትሮኒክ ሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት፣ የሒሳብ መዝገብ በሚይዙ ሁሉም ታክስ ከፋዮች ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡
የኤሌክትሮኒክ ሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት፣ ታክስ ከፋዮች ሽያጫቸውን ለመመዝገብና የሽያጭ መረጃዎችን በቀጥታ በኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ ሥርዓት ለማስተላለፍና ለመመዝገብ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ማንኛውም ታክስ ከፋይ በፈቃደኝነት ከኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት ጋር ተስማሚ የኤሌክትሮኒክ ሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት መጠቀም እንደሚችልም ተደንግጓል፡፡
ሆኖም በርካታ ደረሰኞችን የሚያመነጩና አሠራራቸው ለኦዲትና ለክትትል አመቺ የሆኑ ባንኮች፣ የሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያዎች፣ የዲጂታል ከፍያ አሳላጮች፣ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎች፣ ለሸማች ወይም ለግል አገልግሎት በሚውሉ ግብይቶችና አገልግሎቶች ላይ ከኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት ጋር በቀጥታ መገናኘት ሳያስፈልጋቸው፣ ደረሰኝ የሚሰጡበትን አሠራር ሚኒስቴሩ በልዩ ሁኔታ ሊፈቅድ ይችላል ተብሏል፡፡
አጠቃላይ የሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት ፈቃድ አሰጣጥ ሁኔታን በሚመለከት በተደነገገው የመመርያው ከፍል፣ የሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓቱ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የሶፍትዌር ደኅንነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ሊያቀርብ እንደሚገባ ተደንግጓል፡፡
በተጨማሪም በኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓቱ ውስጥ የተተገበሩ የማንነት ማረጋገጫ፣ የግንኙነት መመስጠሪያና ሌሎች የደኅንነት አሠራሮችን መተግበሩና በዲጂታል ፊርማ የተረጋገጠ ግንኙነትና የመረጃ መላላክን ማስቻሉ ሊረጋገጥ እንደሚገባ ተመላከቷል፡፡
Via : ሪፖርተር
2 469
በአሜሪካ የቪዛ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል የተባሉ የህወሃት አመራሮችና መኮንኖች ዝርዝር ይፋ ተደረገ
የአሜሪካ መንግስት ማዕቀብ ጥሎባቸዋል የተባሉና ቁጥራቸው 203 የሚደርስ የሲቪል አመራሮች፣ የጦር ጄነራሎችና ከፍተኛ መኮንኖች ስም ዝርዝር ይፋ መደረጉን ተያያዥ መረጃዎች ጠቁመዋል።
በቀረበው ይፋዊ መረጃ ላይ ከተጠቀሱት 203 ግለሰቦች መካከል በመጀመሪያው ዙር ስማቸው በግልጽ የወጣው የ64ቱ አመራሮችና መኮንኖች ሙሉ ዝርዝር :-
1. ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መዓሾ
2. ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር
3. አቶ ጌታቸው አሰፋ
4. ሌተና ጄነራል ፍስሃ ኪዳኑ
5. ብርጋዴር ጄነራል ሃይለስላሴ ግርማይ
6. ብርጋዴር ጄነራል ምግበይ ኃይሌ
7. ሜጀር ጄነራል ማሾ በየነ
8. ሜጀር ጄነራል ዮሐንስ ገብረጊዮርጊስ (ጆን መዲድ)
9. አቶ ዓለም ገብረዋህድ
10. አቶ ተወልደ ገብረትንሳኤ (ዕምበብ)
11. ወ/ሮ ኪሮስ ሐጎስ
12. አቶ አማኑኤል አሰፋ
13. አቶ ተክላይ ገብረመድህን
14. ብርጋዴር ጄነራል ወልደጊዮርጊስ ተክላይ
15. ብርጋዴር ጄነራል አብርሃ ተስፋይ
16. ብርጋዴር ጄነራል ህንጻ ገብረጊዮርጊስ
17. ብርጋዴር ጄነራል ዘነበ ክፍሌ
18. ሜጀር ጄነራል ብርሃነ ነጋሽ
19. ዶ/ር ፍስሃ ኃፍተጽዮን
20. ወ/ሮ ልያ ካሳ
21. አቶ ሲሳይ ግርማይ
22. አቶ ወልደሃብርሃ ገብረጻድቅ
23. ኮሎኔል ካህሳይ መኮንን
24. ኮሎኔል ትንሳኤ ብርሃነ
25. ኮሎኔል ሐጎስ ገብረ
26. ኮሎኔል ታደሰ ገብረማርያም (ወዲ ያዞል)
27. ዶ/ር ሰሎሞን ኪዳነ
28. ፕሮፌሰር ክንፈ አብርሃ
29. ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ
30. ዶ/ር አብርሃም ተከስተ
31. ዶ/ር ምህረት በየነ
32. አቶ ጸጋይ ተካ (ማርክስ)
33. ብርጋዴር ጄነራል ፍስሃ በየነ (ወርቂ ዓይኑ)
34. ኮሎኔል ንጉስ አበጀ
35. አቶ ከላሊ ሐጋዚ
36. አቶ ኪዳነ አመነ
37. አቶ ዶሪ አስገዶም
38. ዶ/ር ረዳኢ በርሀ (ሥራ አስፈጻሚ)
39. ዶ/ር ኪሮስ ጉዕሽ
40. ወ/ሮ ፍረወይኒ ገረዝጊሄር
41. ዶ/ር ጸጋይ በሪሁ
42. ዶ/ር አብርሃም ሐጎስ
43. ዶ/ር ጸጋይ ብርሃነ
44. ወ/ሮ ዘነበች ፍስሃ
45. ወ/ሮ ኤልሳ ተስፋይ
46. አቶ እያሱ ተስፋይ
47. አቶ ባህኢለን ወላይ
48. ወ/ሮ ብርክቲ ገብረመድህን
49. አቶ ዓለምብርሃን ሃሪፈዮ
50. አቶ ተክኣ ገብረየሱስ
51. አቶ ረዳኢ ገብረእግዚአብሔር
52. አቶ ካልኣዩ ገብረሂወት
53. ዶ/ር ተክላይ ተስፋይ
54. አቶ ሃይላይ አረጋዊ
55. ፈናን አብርሃ
56. አቶ ትኩእ ኃይሉ
57. አቶ አማኑኤል ገረዝጊሄር
58. አቶ ዝናቡ ገብረመድህን
59. አቶ ገዛኢ ዳኘው
60. አቶ ገብረመድህን ዮሐንስ
61. አቶ አጽብሃ አረጋዊ
62. ጸሃይ አያሌው
63. አቶ ክብሮም ፍስሃየ
64. ኮሎኔል ገብረ ገብረጻድቃን ይገኙበታል ተብሏል።
#ዋሱመሐመድ
2 469
ትራምፕ የጣሊያኗ ጠቅላይ ሚኒስትር አብረን ፎቶ ለመነሳት ለምናኛለች አሉ
የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒዮ ታጃኒ ወደ አሜሪካ ሊያደርጉት የነበረውን ጉዞ የሰረዙ ሲሆን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጣሊያን ቲቪ እንደተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ከእኔ ጋር ፎቶ ለመነሳት "ለምናኛለች" ማለታቸውን ተከትሎ ነው።
ሜሎኒ በሰጠችው አስተያየት ሙሉ በሙሉ "የፈጠራ" ንግግር ስትል አስተባብላለች። የሁለቱ መሪዎች ከፍተኛ ውዝግብ የተጀመረው ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነት ለመግጠም ከወሰኑ በኃላ የነበራቸው የጠበቀ ግንኙነት መሻከሩን አመላካች ሆኗል።
ትራምፕ እና ሜሎኒ በዚህ ሳምንት በምስራቃዊ ፈረንሳይ ኤቪያን-ሌ-ባይንስ በተካሄደው የቡድን ሰባት ስብሰባ ላይ የቅርብ ውይይት ሲያደርጉ የታዩ ሲሆን የጣሊያኗ መሪ በኋላ ግንኙነታቸው እንዳልተለወጠ እና "ምንም አይነት ነቀፋ እንደሌለበት" ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ትራምፕ ከጣሊያኑ ላ7 የቴሌቭዥን ጣቢያ ጋር በስልክ ባደረጉት ቃለ ምልልስ “ከእርሷ ጋር ፎቶ እንዳነሳ ለምናኛለች፤ አዘንኩላት” ሲሉ ከሰዋል። ሁለቱ መሪዎች ኤቪያን ላይ ብዙ ጊዜ አንድ ላይ ታይተው ነበር፣በተጨማሪም በትንሽ ሶፋ ላይ ሲጨዋወቱ ትራምፕ ሲያወሩ ሜሎኒ ፈገግ ስትል ትታያለች።
በስምኦን ደረጄ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
