2 783
订阅者
+624 小时
+317 天
+8630 天
帖子存档
በተጨማሪም :ሁሉንም ከ5 ወደ6 እና ከ7 ወደ 8 የሚዘዋወሩ ተማሪዎች ለብሔራዊ ፈተና ይረዳቸው ዘንድ:ልዩ የክረምት ት|ት የሚሰጥ ሲሆን ከሰኞ 10|11|15 ጀምሮ ለ 45 ቀናት የሚሰጥ ይሆናል ።በዘንድሮ ዓመት የብሄራዊ ፈተና የወሰዳችሁ የ 6እና 8 ክፍል ተማሪዎች:ውጤት እስኪመጣ :በ መጠባበቂያ(waiting list)ተመዝግባችሁ የምትቆዩ ይሆናል።
ለባሸዋም ትምህርት ቤት ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ፡
ቅዳሜ እለት ከጠዋቱ 2:00 -- 6:30 ምዝገባ የምንመዘግብ ስለሆነ ፡ ያልተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሰዓቱ መጥታችሁ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን።
ቅዳሜ ቀን እስከ 6:30 ምዝገባ አለ።
Repost from Ethiopian Digital Library
በፈተና ቦታ የተፈቀዱ እና የተከለከሉ
ተፈታኞች እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ ብቻ ወደ ፈተና ማዕከላት ይዘው መሔድ እንደሚችሉ ተገልጿል ።
ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት፣ ጆሮ ማዳመጫ፣ ዲጂታል ሰዓት እንዲሁም ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎችን ይዞ በፈተና ማዕከላት መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
መልካም ፈተና!
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
የ6ኛ ክፍል የባሸዋም ት/ትቤት ተማሪዎች በሙሉ የክልላዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ፣ ሰዓት፣ፎርም እና አስፈላጊ የሚባሉ ዝግጅቶች: ያጠናቀቅን መሆኑን ይታወቃል፡ት/ት ቤታችሁ በተጨማሪም ለደህንነታችሁ በማሰብ ልዩ የትራንስፖርት ዝግጅት ያደረገ:ሲሆን ረቡዕ እና ሐሙስ ጠዋት ት/ትቤትልችሁ ምሳ ይዛችሁ በመምጣት:በጥንቃቄ ተቀምጦ :በሰርቪስ አድርሶ ምሳ መልሶ ት/ት ቤት:ከሰዓት መፈተኛ ቦታ መልሶ ስትጨርሱ ት/ት ቤታችሁ በማምጣት በጣም የሚገርም እንክብካቤ ለናንተ ያዘጋጀ ሲሆን ወላጆች ጠዋት 1:00 ሰ. ማምጣት እና ከሰዓት ፈተና ሲጨርሱ ወደቤት ከባሸዋም መረከብ ግዴታችሁ ይሆናል :ሰዓት የማያከብር ተማሪም ሆነ ወላጅ በፍፁም :አይስተናገድም።ባሸዋም ይለያል!#focuse#8ኛክፍሎች የተቀየረው መፈተኛ ካርድ ቅዳሜ እስከ5ሰዓት ብቻ ከ5-8ኛ ክፍል ር/መ/ር ቢሮ በመምጣት ፡የሚረከቡ ይሆናል::
የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች
1.የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ውስጥ
ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
2.በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
3.ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
4.ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
5. በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
6) ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
7.ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
8.መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
9. ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
በተጨማሪም ተማሪዎች ምንም አይነት ጌጣጌጦች ማለትም የአንገት፡ የእጅ፡ የጆሮ የመሳሰሉት ጌጣጌጦች አጊጣችሁ ወደ ፈተና ቦታ አትሒዱ።
ስልክ ይዛችሁ ወደ መፈተኛ ቦታ አትሒዱ
፡
ከትራንስፖርት ውጪ ወይም ከመጠን በላይ የሆነ ብር ወይም ገንዘብ ይዛችሁ አትሒዱ።
መልካም ፈተና ለተማሪዎቻችን
6ኛ ክፍል ተማሪ ሆኖ መፈተኛ ካርድ (admision card)ያልወሰደ ተማሪ ነገ በ23/10/15 ጠዋት2:00 ሰዓት በባሸዋም ግቢ የሚሰጥ ሲሆን ፣በመቀጠል በብስራት ት/ቤት ግንዛቤ ይሰጣል።ፈተናቸው ረቡዕ 28 እናሐሙስ በ29/10/15 የሚሰጥ ይሆናል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
