fa
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

رفتن به کانال در Telegram

Bashewam School Grade 1-8

نمایش بیشتر
2 781
مشترکین
+1524 ساعت
+287 روز
+8230 روز
آرشیو پست ها
photo content
+4

photo content

በፈተና ቦታ የተፈቀዱ እና የተከለከሉ ተፈታኞች እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ ብቻ ወደ ፈተና ማዕከላት ይዘው መሔድ እንደሚችሉ ተገልጿል ። ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት፣ ጆሮ ማዳመጫ፣ ዲጂታል ሰዓት እንዲሁም ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎችን ይዞ በፈተና ማዕከላት መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ መልካም ፈተና! @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library

የ6ኛ ክፍል የባሸዋም ት/ትቤት ተማሪዎች በሙሉ የክልላዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ፣ ሰዓት፣ፎርም እና አስፈላጊ የሚባሉ ዝግጅቶች: ያጠናቀቅን መሆኑን ይታወቃል፡ት/ት ቤታችሁ በተጨማሪም ለደህንነታችሁ በማሰብ ልዩ የትራንስፖርት ዝግጅት ያደረገ:ሲሆን ረቡዕ እና ሐሙስ ጠዋት ት/ትቤትልችሁ ምሳ ይዛችሁ በመምጣት:በጥንቃቄ ተቀምጦ :በሰርቪስ አድርሶ ምሳ መልሶ ት/ት ቤት:ከሰዓት መፈተኛ ቦታ መልሶ ስትጨርሱ ት/ት ቤታችሁ በማምጣት በጣም የሚገርም እንክብካቤ ለናንተ ያዘጋጀ ሲሆን ወላጆች ጠዋት 1:00 ሰ. ማምጣት እና ከሰዓት ፈተና ሲጨርሱ ወደቤት ከባሸዋም መረከብ ግዴታችሁ ይሆናል :ሰዓት የማያከብር ተማሪም ሆነ ወላጅ በፍፁም :አይስተናገድም።ባሸዋም ይለያል!#focuse#8ኛክፍሎች የተቀየረው መፈተኛ ካርድ ቅዳሜ እስከ5ሰዓት ብቻ ከ5-8ኛ ክፍል ር/መ/ር ቢሮ በመምጣት ፡የሚረከቡ ይሆናል::

የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች 1.የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ 2.በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ 3.ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ 4.ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ 5. በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ 6) ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ 7.ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ 8.መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ 9. ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ በተጨማሪም ተማሪዎች ምንም አይነት ጌጣጌጦች ማለትም የአንገት፡ የእጅ፡ የጆሮ የመሳሰሉት ጌጣጌጦች አጊጣችሁ ወደ ፈተና ቦታ አትሒዱ። ስልክ ይዛችሁ ወደ መፈተኛ ቦታ አትሒዱ ፡ ከትራንስፖርት ውጪ ወይም ከመጠን በላይ የሆነ ብር ወይም ገንዘብ ይዛችሁ አትሒዱ። መልካም ፈተና ለተማሪዎቻችን

6ኛ ክፍል ተማሪ ሆኖ መፈተኛ ካርድ (admision card)ያልወሰደ ተማሪ ነገ በ23/10/15 ጠዋት2:00 ሰዓት በባሸዋም ግቢ የሚሰጥ ሲሆን ፣በመቀጠል በብስራት ት/ቤት ግንዛቤ ይሰጣል።ፈተናቸው ረቡዕ 28 እናሐሙስ በ29/10/15 የሚሰጥ ይሆናል።

ውድ የ6ኛ እና8ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች :ክልላዊ ፈተና የሚፈተኑት 8ኛ ክፍሎች ሰኔ 26እና|27/10|15 :6ኛ ደግሞ 28እና29/10/15 መሆኑን ይታወቃል ሆኖም ሀሙስ በ22/10/15 ከጠዋቱ 2፡30 በት/ቤታቸው(ባሸዋም)ግንዛቤ የሚሰጥ እና የመፈተኛ ፈቃድ(admission card)ከክፍያ እና መሰል ጉዳዮች ነፃ መሆናቸው ተረጋግጦ ይሰጣቸዋል።ከዚህም በተጨማሪ ዓርብ በ23/10/15 በመፈተኛ ጣቢያቸው :በብስራት ት/ቤት ግንዛቤ የሚሰጣቸው መሆኑን እየገለፅን መቅረት :በፍፁም አይፈቀድም።

1.ሐሙስ ሰኔ 22/2015 ዓ.ም ለጣቢያ ሀላፊ ፣ለሱፐርቫይዘሮች፣ ለፈታኝ እና ጤና ባለሙያዎች በተመደቡበት  የፈተና ጣቢያ ኦረንቴሽን ይሰጣል 2.አርብ ሰኔ 23/2015 ዓ.ም ለ8ኛ እና 6ኛ ክፍል ተማሪዎች  በተመደቡበት የመፈተኛ ጣቢያ ኦረንቴሽን ይሰጣል 3.ከሰኔ 26-27/2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡፡ 4.ከሰኔ 28-30/2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡፡ ✅በመሆኑም ሁሉም የግል እና የመንግስት  ት/ቤቶች እና ወላጆች ተማሪዎች  ወደ  ተመደቡበት የፈተና ጣቢያ በተቀመጠው ፕሮግራም መሠረት ተገኝተው ፈተናቸውን በአግባቡ እንዲወስዱ እናሳስባለን