1 063
订阅者
无数据24 小时
-77 天
+230 天
帖子存档
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#ቴክኒክናሙያስልጠና
‹‹ዛሬ የሰለጠናችሁት ሙያና ክህሎት ነገ የምትፈልጉትን የወደፊት ህይወት ይገነባል ››
ሰላማዊት ወንደሰን ትባላለች በደሬዳዋ ከተማ ተወልዳ ነው ያደገችው፡፡ ወጣት ሰላማዊት የራሷን ህይወትና የቤተሰቧን የኑሮ ሁኔታ ለማስታከል እንዲረዳት የተለያዩ ትምህርቶችን በመደበኛው የትምህርት መስክ ተምራለች፡፡
ታድያ ይህች ወጣት በተማረችበት የትምህርት መስክ ስራን ለማግኘት እንደ ማንኛውም ወጣት ብዙ ተቸግራለች፡፡ነገር ግን የሚያጋጥማትን ችግር ወደጎን በመተው የራሷን ድርጅት ከፍታ ለመንቀሳቀስ አስባ ውደ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴክስታይል ጋርመንት ሌዘር እና ፋሽን ዲዛይን ትምህርት ክፍል በቆዳ ውጤቶች ላይ በአጫጭር ስልጠና ስልጠናን ወሰደች፡፡ በወሰደችው ስልጠና አሁን ላይ ከጓደኞቿ ጋር በጋራ በመሆን የራስዋን የቆዳ ውጤቶች ማምረቻ ድርጅት በኮሌጁ ባገኙት ድጋፍ ከፍተው እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች፡፡
ወጣት ሰላማዊት አሁን ላይ በኮሌጁ ባገኘችው ስልጠናና ድጋፍ የድርጅት ባለቤት ሆናለች እናንተም በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተከፈቱት የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች በረጃጅምና በአጫጭር ስልጠና በመመዝገብና ስልጠናዎችን በመውሰድ የነገ ህይወታችሁን ጥሩ እንዲሆን ወጣት ሰላማዊት ወንደሰን ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መስከረም 08/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
"እምርታ እና ማንሰራራት"
***
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃን አስመልክቶ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "እምርታ እና ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል ከቢሮው ሰራተኞች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ።
የፓናል ውይይቱን የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የመሩት ሲሆን ግድቡ በታሪክ ቅብብሎሽ በራሳችን ጥረት ጀምረን ያሳካነው ፕሮጀክት መሆኑን አንስተው ከጅማሬው አንስቶ እስከ ማጠናቀቅያው የነበሩ መሪዎች ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩም የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ሙሉጌታ ሀ/ማርያም ለዕለቱ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በጣም ደስተኛ እንዳደረጋቸውና ጀምረን መጨረስ የምንችል መሆኑን ለዓለም ያሳየንበት እንደሆነ ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 09/18 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቀዳሚ ምርጫ ወይስ አማራጭ?
በአለማችን እጅግ የረቀቁ ቴክኖሎጂዎች እና ግዙፍ የሆኑ ኩባንያዎች የተጠነሰሱት ክህሎት በታጠቁ ግለሰቦች መሆኑን ስንቶቻችን እንገነዘባለን?
የአለምን ኢኮኖሚ የሚዘውሩ የበለጸጉ ሀገራት እና የሀብት ማማ ላይ የተፈናጠጡ በርካታ የትላልቅ ኩባንያ ባለቤቶች መነሻቸው ሙያ/ ክህሎት ነው፡፡
ሀገራችንም ከዘርፉ ለመጠቀም ክህሎት የታጠቁ ዜጎች ለማፍራት በየአካባቢው በርካታ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች አቋቁማ እየሰራች ትገኛለች፡፡
ነገር ግን ጥቂት የማይባሉ የህብረተሰብ ክፍሎች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በመሰልጠን የሚገኙ ተቆጥረው የማያልቁ እድሎችን ሳይሆን በመደበኛ ትምህርት የሚገኝ ዲግሪ፣ ማስተርስ እና ፒ ኤች ዲ እንደ መልካም እድል የማየት አዝማሚያ ይስተዋላል፡፡
ነው ወይ? ብለን ስንጠይቅ ግን እውነታው፤ በፍጥነት እዕምሮ እና እጅን በማገናኘት ለሚታዩ አካባቢያዊ ችግሮች ተጨባጭ መፍትሄ ለመስጠት፣ በገበያ በእጅጉ ተፈላጊ ለመሆን፣ በፍጥነት ወደ ግል ቢዝነስ ለመግባት፣ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች ለመጀመር እና ያሰቡትን ለመተግበር ክህሎት መታጠቅ አይነተኛ መፍትሄ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
ይህንን እውነታ ለመረዳት እሩቅ መሄድ ሳያስፈልግ በአለማችን ታዋቂ እና ግዙፍ ኩባንያዎች መስራችና ባለቤት የሆኑ ግለሰቦች ታሪክ በአጭሩ ማየት ብቻ በቂ ይሆናል፡፡
በአለማችን በአውቶሞቲቭ ኢንደስትሪ እጅግ ግዙፍ የሆኑት የአማሪካው የፎርድ ሞተር ካምፓኒ እና የጃፓኑ ሆንዳ ሞተር ካምፓኒ መስራቾች መነሻቸው በማሽን የነበራቸው ክህሎት(skills) ነው፡፡
በቴክኖሎጂ ደግሞ የአሜሪካው አፕል መስራቾች ስቴቭ ጆብስ እና ስቴቭ ኦዝኒያክ በነበራቸው የኤሌክትሮኒክ ክህሎት እጅግ ታዋቂ የሆነውን አፕል ለአለም አበርክተዋል፡፡
በተመሳሳይ የአሜሪካው ሚካኤል ዴል ኮምፕዩተሮችን ፈትቶ የመገጣጠም ክህሎቱ ወደ የዴል ኮምፕዩተር መስራችነት አሸጋግሮታል፡፡
እነዚህ ለአብነት እናንሳ እንጂ የአለምን ኢኮኖሚ የሚዘውሩ በማኑፋክቸሪንግ እና ኢንጅነሪንግ፣ በፋሽን እና ክሬቲፍ ኢንደስትሪ እና በግንባታ ስራ የተሰማሩ ኩባንያዎች እና በአይቲ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች መነሻቸው የቴክኒክና ሙያ(ክህሎት) ነው፡፡
እነዚህን የአለማችን ነባራዊ ሀቆች መነሻ ስናደርግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቀዳሚ ምርጫ እንጂ አማራጭ እንዳልሆነ እንረዳለን፡፡
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በክህሎት የላቁ ለፈጠራ የቀረቡ ዜጎችን በማሰባሰብ ቶሎ ከህልማቸው የሚያገናኙ የቴክኖሎጂ፣ የኢኖቬሽንና ፈጠራ ማዕከል በመሆን እያገለገሉ ይገኛል፡፡
ይህንን ሀገራዊ ተልዕኮአቸው ለመወጣት በሀገራችን የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት እንደየ አካባቢያዊ ጸጋቸው በተሰማሩበት ስልጠና በመደበኛ እና በአጫጭር ስልጠና ሰልጣኞችን ተቀብለው ለማሰልጠን ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል፡፡
በአቅራቢያዎ ወደ ሚገኝ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በመሄድ የክህሎት ባለቤት ይሁኑ!
መስከረም 7/2018 ዓ.ም ፤
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሴት ሠራተኞች ለአዲስ አመት ያሰባሰቡትን ጥሬ ገንዘብ ለአሰገደች የአረጋውያን መጦሪያ ማዕከል በአካል በመገኘት ድጋፍ አደረጉ፤
ለዚህም ድጋፍ በማዕከሉ የተገኙት ሠራተኞች የማዕከሉን ሁኔታ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ማዕከሉ እየሰጠ የሚገኘውን አገልግሎት አድንቀው ከተደረገው ድጋፍ በተጨማሪ ቀጣይነት ባለው መልኩ የተለያዩ የገንዘብና የአይነት ድጋፎችን እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡
አሰገደች የአረጋውያን መጦሪያ በድሬዳዋ ከተማ በ1980 ዎቹ የተቋቋመ የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው። ድርጅቱ የተጠነሰሰው በወ/ሮ አሰገደች መኖሪያ ቤት ሲሆን ይህ ጅማሮ የመንግስት እና የበጎ አድራጊ ግለሰቦች ጥረት ታክሎበት አሁን ያለበትን የአገልግሎት ማዕከል መመስረት ችሏል፤ በአሁኑ ወቅት ማዕከሉ ውስጥ ለሚገኙ አዛውንቶች የምግብ፣ የመጠልያ፣ የጤና፣ እና የንፅህና ግልጋሎቶች ይሰጣል። ከዚህ በተጨማሪም ከመጠለያ ውጪ ላሉ በርካታ አዛውንቶች የገንዘብ ድጋፍ ያደረጋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 6/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+2
‹‹ሀገራችን ኢትዮጵያን የሚረከቡ በእውቀትና በክህሎት የዳበሩ ትውልዶችን ለማፍራት የትምህርት ስልጠና ዘርፉ ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል››
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ2018 ዓ.ም የትመህርት ዘመን የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በዛሬው እለት በኮሌጁ ለሚገኙ ዝቅተኛ ደሞዝ ላላቸው ሰራተኞች ድጋፍ አደረገ።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መስከረም 05/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#|ዜና የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD አማካኝነት ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክት የህንጻ ግንባታ ስምምነት ህንጻውን ከሚገነባው ሀገር በቀል ህንጻ ተቋራጭ ጋር በዛሬው እለት ተፈራረመ፡፡
በኮሌጃችን ውስጥ ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክት ፕሮጀክቱን ከሚያጸድቁ አካላቶች ከGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD No Objection ከዚህ ቀደም መገኘቱ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለት የኮሌጁ ዲንና ም/ዲን፣ SIFA ፕሮጀክት የኢትዮጵያ አስተባባሪ፣ህንጻውን ለመገንባት ጨረታውን ያሸነፈው ኮንትራክተር እንዲሁም የEASTRIP ፕሮጀክት አስተባባሪና ኣባላት እና የ ICT ትምህርት ክፍል ተጠሪ በተገኙበት በይፋ ከተቋራጩ ጋር ኮሌጁ የተፈራረመ ሲሆን፣
በፊርማ ስርአቱ ላይ የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት ይህ ፕሮጀክት በኮሌጁ ተግባራዊ እንዲደረግ የተለያዩ ውጣ ውረዶችን አልፎ ለዚህ የፊርማ ስርአት በመገኘታችን የተሰማኝን ደስታ ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ ፕሮጀክቱ በኮሌጃችን ተግባራዊ መሆኑ የአካባቢውን ብሎም የቀጠናውን ወጣቶች በICT የዳበረና እውቀት ያለው ትውልድ ለመገንባት ያስችለናል፡፡ ከዚህም አልፎ ከተማችንን ስማርት እንድትሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረክታል ያሉ ሲሆን አያይዘውም በተቀመጠው ጊዜ መሰረት ህንጻው ተገንብቶ ለአገልግሎት የሚውል ይሆናል ብዋል፡፡
ይህ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲውል ከOctober 8/2025 እስከ December 2/2026 የ14 ወራት ጊዜ የተሰጠው ሲሆን በDecember 2/2026 ህንጻው ተመርቆ ለአገልግሎት የሚውል ይሆናል፡፡ ህንጻው በውስጡም የተለያዩ Smart Classroom፣ Design Studio ፣ዘመናዊ Computer Lab፣ Research Room የተለያዩ Conference Room፣ Digital Library እንዲሁም በርካታ ማስተማሪያ ክፍሎችና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ክፍሎችን በውጡ የያዘ እንደሆነ በፊርማ ስርአቱ ላይ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መስከረም 5/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የኮሌጅ አመራርና ሰራተኞች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድቡን ምርቃት ምክኒያት በማድረግ በድሬዳዋ አሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴስ ትምህርት ቤት የተዘጋጀ የፎቶግራፍ አውደርዕይ ጉብኝት አካሄዱ።
በፎቶ አውደርዕይ ጉብኝቱ አመራሩ እና ሰራተኛው የሀገር ምልክት የሆነው ግድቡ ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው ያለውን ሂደት የተመለከቱ ሲሆን በዚህም ሀገራዊ አንድነትንና የጋራ ዕሴትን በመገንባቱ ረገድ መሰል ዝግጅቶች ሚናቸው ላቅ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 5/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና 8 ነጥብ 4 በመቶ ተማሪዎች አለፉ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተናን ከተፈተኑት 8 ነጥብ 4 በመቶ ተማሪዎች አልፈዋል አሉ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)።
የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት በዛሬው ዕለት ይፋ ተደርጓል።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንዳሉት፤ ዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከተፈተኑት መካከል 8 ነጥብ 4 በመቶ ተማሪዎች ከ50 በመቶ በላይ በማምጣት አልፈዋል።
በዚህም በአጠቃላይ ዘንድሮ 48 ሺህ 920 ተማሪዎች ማለፋቸውን ጠቁመዋል።
ባለፈው ዓመት አማካይ ውጤት 29 ነጥብ 7 እንደነበር አስታውሰው÷ ዘንድሮ 31 ነጥብ 67 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል ነው ያሉት።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
