ch
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

前往频道在 Telegram
1 063
订阅者
无数据24 小时
-77
+230
帖子存档
#Dire Dawa Polytechnic College #የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ #Address entered the main asphalt road 150 meters from the Dire Dawa Administration Police Headquarters. #አድራሻችን ከድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ባለው ዋናው አስፓልት ላይ 150 ሜትር ገባ ብሎ

እንኳን ለ2018 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ!! አዲሱ አመት ኢትዮጵያ ውጥኖቿን ወደ ስኬት እንዲሁም የጀመረችውን ተስፋን ወደ ሚጨበጥ ውጤት መቀየሯን የምትቀጥልበት ዓመት ይሆናል!! በ2018 ፍቅ
+1
እንኳን ለ2018 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ!! አዲሱ አመት ኢትዮጵያ ውጥኖቿን ወደ ስኬት እንዲሁም የጀመረችውን ተስፋን ወደ ሚጨበጥ ውጤት መቀየሯን የምትቀጥልበት ዓመት ይሆናል!! በ2018 ፍቅራችን በዝቶ፣ ሰላማችን ጎልብቶ፣ ህልማችን እውን የሚሆንበት አዲስ ዓመት እንደሚሆንልንም አልጠራጠርም። በእርግጠኝነት 2018 የኢትዮጵያውያን ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበጥ ብርሃን የማረጋገጥ ጉዞ ተጠናክሮ የሚቀጥልበት  ዓመት ነው!!! በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ!!! የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው

"እምርታና ማንሰራራት“ በሚል መሪ ሀሳብ ከሚከበሩ የጳጉሜ ቀናቶች አንዱ የሆነው ጳጉሜ 5 የነገው ቀን " ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ " በሚል መሪ ሃሳብ በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር በታላቅ ድምቀት ተከብሯል ።      በዚሁ መርሀ-ግብር ላይም በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር በድሬዳዋ አስተዳደር ዲጂታል ድሬን እውን በማድረግ ተቀዳሚ ድርሻችንን ለማበርከት በዲጂታል ቴክኖሎጂው መስክ በትኩረት በመንቀሳቀስ ተስፋን የሚያጭሩ የተለያዩ ፈጠራዎችንና ችግር ፈቺ አፖችን ማልማት መቻሉን ተናግረው ሌሎች በርካታ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎችን በትኩረት በማከናወን ላይ እንደሚገኙም ነው ክቡር ከንቲባው በዕለቱ ያስታወቁት ።      ጷግሜ 5 የነገው ቀንን ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር የለሙ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም ደግሞ በፈጠራ ስራዎች የበለፀጉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በስፋት እንደሚተዋወቁ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ለፕሮግራሙ መሳካትም ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።      በዕለቱም በቴክኖሎጂ የበለፀጉ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች ከድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፤ ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሁም ከኢንተርፕራይዞች ቀርበው ተጎብኝተዋል ።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ ለሆኑ ሠራተኞቹ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር በዛሬው እለት አካሄደ። በማዕድ ማጋራት መርሀ-ግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው "በቅድሚያ ይህን መርሃ-ግብር በምናካሂድበት እለት የዘመናት የኢትዮጵያውያን ህልም የሆነው የታላቁ የህዳሴ ግድባችን ተጠናቆ የሚመረቅበት በመሆኑ መርሃ-ግብሩን እጅግ ልዩ ያደርገዋል" ያሉ ሲሆን አክለውም "የታላቁ የህዳሴ ግድባችን በዛ ሁሉ ተጋድሎ ውስጥ አልፎ ዛሬ ለምረቃ መብቃቱ እኛ ኢትዮጵያውያን ተጋግዘን በአንድነት ከሰራን ሁሉን መለወጥና ማንሰራራት እንደምንችል ማሳያ ነውም ብለዋል:: በተጨማሪም የዚህ ታሪካዊ ቀን አንድ አካል በመሆናችንም ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን በማለት ደስታቸው አጋርተዋል:: በማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብሩ ላይ ከኮሌጁ ዲን በተጨማሪ የኮሌጁ ም/ል ዲኖች የተገኙ ሲሆን ለሠራተኞቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈው ከኮሌጁ የማኔጅመንት አባላት ጋር በመሆን የተዘጋጀውን መአድ አጋርተዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጷጉሜ 4 " የማሰራራት ቀን"

“በህብረት ሆነን የህዳሲ ግድብን እውን እንዳደረግነው በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ውሰጥም የሚጠበቅብንን በመስራት የሃገራችንን የህዳሴ ጉዞ ማስቀጠል ይኖርብናል፡፡” የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ #ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ 2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም እና የ 2018 በጀት አመት እቅድ ኮሌጁ የአመራሮችና እና አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞች በተገኙበት የውይይት እና የግምገማ መድረክ በዛሬው እለት አካሄደ ። በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉትና ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲስ አመትና ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ምርቃት ቀን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን፤ አያይዘውም በተጠናቀቀው በጀት አመት ከትምህርትና ስልጠና፣በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት፣ ለኮሌጁ በገቢ እራሱን ለመቻል አንጻር አንዲሁም በአጫጭር ስልጠና እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር መልካም ትስስርን በመፍጠር አንጻር በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን እና ስራዎቹም ፍሬ ያፈሩበት አመት ነበር ያሉ ሲሆን አቶ ሰለሃዲን አያይዘውም ኮሌጁ የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት እንዲሁም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የሚፈልቁበት ተቋም እንዲሆን የተለያዩ ስራዎች በቀጣይ የሚሰሩ ይሆናል ብለዋል፡፡ በማንሰራራት ቀን ላይ ሆነን በህብረት ታላቁን የህዳሴ ግድብ እውን እነዳደረግነው በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ውስጥም የሚጠበቅብንን ስራዎች በመስራት የራሱን ዳግማዊ አድዋን መፍጠር የሚችል ትውልድ በመፍጠር የሃገራችንን የብልጽግና ጉዞ ማስቀጠል ይኖርብናል ሲሉ ብለቱ ገልጸዋል፡፡ በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ የው/ተ/ት/ስልጠና ም/ዲን የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ እንደደገለጹት በከተማና በገጠር የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በሚሰጡ አገልግሎቶች ተጠቃሚ ከማድረግ ጋር ተያይዞ በትምህርና ስልጠና እንዲሁም የማህበረሰቡን ችግር ከመፍታት አንጻር በቀጣይ አመት በትጋት የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት፣ለኮሌጁ ተጨማሪ ገቢን ከማስገኘት አንጻር አንዲሁም በአጫጭር ስልጠና እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር መልካም ትስስርን በመፍጠርና ተተኪ መለዋወጫ ምርቶችን ከማምረት እና ገጽታ ግንባታ ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የአካባቢውን ማህበረሰብ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በተለያዩ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዱሆኑ በስፋት የማሻሻል ስራዎች እንደሚሰራ የገለጹት ደግሞ የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ናቸው፡፡ በእለቱም በበጀት አመቱ የተሰሩ እንዲሁም ደግሞ በ 2018 በጀት አመት ለመስራት የታቀዱ ስራዎች በአቶ ዘየደ ተክሌ እንዲሁም የEASTRIP እና SIFA ፕሮጀክቶች ላይ በአቶ መሳይ ጥላሁን የቀረበ ሲሆን በአፈጻጸሙላይና በእቅዱ ላይ ሰፊ ውይይትም ተደርጓል ። ስለ ኮሌጁ ትኩስ መረጃ ለማግኘት Facebook: facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/diredawapolytechniccollege YouTube: youtube.com/diredawapolytechniccollege የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጷጉሜ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከመንግስትና ከግል ኮሌጆች እንዲሁም ከዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጋር የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ በጋራ ለመስራትና ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራረሙ። ከሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የተፈራረሙ የግል ኮሌጆች የሚከተሉት ናቸው፦ ✍️ አዲስ አበባ ቢዝነስና  ሜዲካል  ኮሌጅ ✍️ ኦልብራይት ኢንተርናሽናል  ኮሌጅ ✍️ ሉሲ ኮሌጅ ✍️ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ✍️ ሲቲ ጤናና  ቢዝነስ ኮሌጅ    በዚህም በአስተዳደሩ የሚገኙ ከላይ የተዘረዘሩት ኮሌጆች ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ማለትም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ጋር በክላስተር የተደለደሉ ሲሆን ከዚህ ቀደም በተፈጠረው የጋራ ግንዛቤ መሠረት ወደ ስራ የሚገቡ መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ  የ2018 አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ አነስተኛ ደሞዝ ላላቸው የተቋሙ ሰራተኞች የትምህርት ቁሳቁስ እና የፍጆታ ዕቃ መግዣ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ። በድጋፍ ማድረግ መርሃግብሩ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለፁት ቢሮው ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በዚህ ክረምት 120 ለሚሆኑ የአስተዳደሩ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉና የአቀመ ደካሞችን ቤት እያደሰ እንደሚገኝ አስታውሰው ይህ ለቢሮው ሰራተኞች የተደረገውም ድጋፍ ተቋማዊ ጤናማ መስተጋብርን የሚያጎለብት በመሆኑ መሰል ተግባራትን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል። የቢሮ ኃላፊው ለ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያውያን አዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞታቸውንና መልክታቸውን አስተላልፈዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የነገው ቀን! ዿግሜ 5/2017 ዓ.ም ለብሩህ ነገ ዘመኑ በሚፈቅደው ጎዳና መራመድ ከፍ ሲልም የጎዳናው መሀንዲስ መሆን ያስፈልጋል። ዲጂታል ኢትዮዽያን እውን ማድረግ እድገቷን ማፋጠን፣ ግቧን በሰፊው
የነገው ቀን! ዿግሜ 5/2017 ዓ.ም ለብሩህ ነገ ዘመኑ በሚፈቅደው ጎዳና መራመድ ከፍ ሲልም የጎዳናው መሀንዲስ መሆን ያስፈልጋል። ዲጂታል ኢትዮዽያን እውን ማድረግ እድገቷን ማፋጠን፣ ግቧን በሰፊው መወጠን ነው። ይህ ታሪክ መሰራት የለመደ ትውልድ በዚህ ረገድም ታላቅ ድል ያስመዘግባል። ዲጂታል ድሬ የዲጂታል ኢትዮዽያ አካል ሆኖ ህልምን እውን ያደርጋል። የድሬዳዋ አስተዳደር