1 076
订阅者
+224 小时
+37 天
+230 天
帖子存档
በድሬደዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለአንድ ማዕከል አመራሮች እና ባለሞያዎች ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
ስልጠናው በዘርፉ የእሳቤ ዘረመል (DNA)፤ የቤተሰብና የማህበረሰብ ንግድ፤ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች መመሪያ፤ የጥሪት ማፍሪያ መመሪያ እና የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ አተኩሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍና ኢንተርፕራይዝ ልማት ላይ አትኩሮ የአስተዳደሩን የማክሮ ኢኮኖሚው ትልቁ የትኩረት አቅጣጫ የሆነውን ሥራ አጥነትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ የሚያስችል ተልዕኮ የተወሰደበት ሆኗል፡፡
ይህም ተልዕኮውን ለማሳካትም የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎቻችን ከኢኮኖሚ ልማቱ ጋር በማስተሳሰር የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት የአስተዳደሩ የወረዳ አንድ ማዕከላትን አቅም በመገንባት ተግባራዊ እንቅስቃሴውን ከፍ ባለ መነቃቃትና ተነሳሽነት ለመፈጸም አቅጣጫ የተቀመጠበት ሲሆን በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ በአስተዳደሩ የሚካሄዱ የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎች በአጠቃላይ ዕለታዊ ችግሮችን ከማቃለል ባሻገር ሀብት መፍጠርና ማካበት እንዲሁም ጥሪት ማፍራት ላይ የሚያተኩሩ በዋናነትም ክህሎት መር መሆኑ ተመላክቷል፡፡
እንደ አስተዳደር ያለውን ፀጋ አልምቶ መጠቀም እንዲቻል የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎቻችን የየአካባቢውን ፀጋ የለዩ እና በሂደቱ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች በሙሉ የእሴት ሰንሰለትን መሰረት ያደረጉ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና ለሥራ ፈጣሪዎች ምቹ የሆነ ስነ ምህዳር ለማመቻቸት ከባለድርሻ፣ አስፈፃሚ እና አጋር አካላት ጋር የተጀመሩ ስራዎችም ተስፋ የሚሰጡ መሆናቸውና ከዚህ አንፃር የተለያዩ አካላትም ለሥራ ፈጠራ እየሰጡ ያለው ትኩረት እየተሻሻለ መምጣቱ ይህም ስነ-ምህዳሩን ለማስፋት የተጀመረው ጥረት ተስፋ ሰጪ መሆኑንና የተፈጠረውን እድል ዜጎችን ተጠቃሚ በሚያደርግ አግባብ መጠቀም እንደሚገባ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ አስገንዝበዋል፤
በስልጠናው ማጠናቀቂያም የማደግ አለኝታ ያላቸው ኢንተርፕራይዞች በማክሮ ኢኮኖሚው እድገት ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ የሚያግዙ የሥልጠና፣ የብድር፣ የገበያ ትስስርና መሰል መንግስታዊ ድገፎችን እንዲያገኙ ተገቢው ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑና ከሥራ ፈጠራ ባሻገር የአስተዳደሩን ነዋሪ ችግር ሊፈቱ የሚችሉ፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎቻችን የሚያፋጥኑና በተለይ እንደ ሀገር ተኪ ምርቶች ላይ አቅም ለመፍጠር የሚያስችል ውጤት ለማስመዝገብ ስልጠናውን ወደ ተግባር መቀየር እንደሚገባ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ አሳስበዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 5/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ጠቃሚ አገር በቀል እውቀቶች፣ ክህሎቶችና ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችል መድረክ ለአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራንና ለባለድርሻ አካላት አዘጋጀ።
በግንዛቤ ማስጨበጫና በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆኑ አገር በቀል እውቀቶችንና ክህሎቶች ለሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት ያላቸው ፋይዳ ቀላል አለመሆኑ በዚህም በትምህርት ቤቶች ውስጥ ተማሪዎች እያዳበሩ የሚያድጉበት አመቺ ሁኔታ ማመቻቸት እንደሚገባ ከመድረኩ ተነስቷል፡፡
በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተመላከተው መሰረት አገር በቀል እውቀቶችና ክህሎቶችን ማልማት ትኩረት መሰጠቱ ትልቅ አቅም መሆኑም የቢሮው ም/ኃላፊ እና የኤጀንሲው ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል።
ኃላፊዋ አክለውም በአስተዳደሩ የሚገኙ አገርበቀል እውቀቶችንና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ስርዓተ ትምህርት ለማስገባት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስታውሰው ይህን የማህበረሰብ ሀብት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገርና ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ የመምህራን ሚና ላቅ ያለ እነደሆነ አስረድተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 5/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
የድሬዳዋ አስተዳደር በሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የኮሌጆችን አቅም ለማሳደግና የአሰልጣኝ መምህራንን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስራዎችን በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የማኑፋክቸሪንግ ትምህርት ክፍል እና የአውቶሞቲቭ ትምህርት ክፍል የውስጥ የሚገኙ በተለያየ ምክንያት የተበላሹ ሶስት ማሽኖች በማኑፋክቸሪንግ ትምህርት በኩል CNC lathe machine እና
CNC milling machine የተጠገኑ እና ወደ ስራ የገቡ ሲሆን በቀጣይ የSpot welding machine ፣ Circular sheet metal cutter ፣ Surface grinding machine ተሰርተውና ተጠግነው ወደ ስራ እንዲገቡ በእቅድ የተያዙ ሲሆን፤ በአውቶሞቲቭ ትምህርት ክፍል ደግሞ የመኪና ማጠቢያ ማሽን እንዲሁም የተሸከርካሪ አመታዊ መመርምሪያ ማሽን (ቦሎ ማሽን) ጥገና ተደርጓል፡፡
የማሰልጠኛ ማሽኖቹ ጥገና በአሰልጣኝ መምህራኑ መካከል የልምድና የእውቀት ሽግግር አንዳቸው ለሌላቸው በማድረግ አሰልጣኝ መምህራኑ የክህሎት አቅማቸውን በአንድ በኩል ሲያሳድጉ ከዚሁ ጎን ለጎን ማሽኖቹን ጠግነው ለትምህርትና ስልጠናው ዝግጁ በማድረግ ጥቅም ላይ እንዲውሉ አድርገዋል ያሉት የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ሲሆኑ
ለ15 ቀናት በተከናወነው የጥገና ስራ በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ዘንድ ያለውን የክህሎት ክፍተት መሙላት መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ይህ ተግባር በኮሌጁ በሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
#ዜና | በቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ የሚሰጡ የሞያ ስልጠናዎች በሀገር ውጥ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ማእከል ማድረግ እንዳለበት ተገለፀ።
#Diretv አማርኛ ታህሳስ 3/2017
የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ጋር የምክክር መድረክ አካሔደ።
እንደ ሀገር አቀፍ ያለውን የስራ እጥ ችግርን ለመቅረፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በዚህ የቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች ደሞ ያላቸው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም።
ይሁን እንጂ የሞያ ኮሌጆች የሚሰጡት ስልጠና ክህሎትን ከስራ ቅጥር ጋር ያገናኘ ባለመሆኑ ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች የሚወጡ ሰልጣኞች በስራ እጦት ሲቸገሩ ይስተዋላል። የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት በሚቻልባቸው የስልጠናና የትምህርት መስኮች ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ የሚሰጡ የሞያ ስልጠናዎች በሀገር ውጥ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ማእከል ማድረግ እንዳለበት የገለፁትና የኢንዱስትሪዎች ፍላጎት ተለይቶ ስራ እጥነትን መቅረፍ ያስችላል፣ ለዚህም ኢንዱስትሪዎች በራሳቸው የሚሰጡትን ስልጠና በማቆም ለኮሌጆች ሀላፊነቱን መስጠት አለባቸው ሲሉ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ ተናግረዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በአስተዳደሩ ባሉ ሁለት የሞያ ኮሌጆች የሚያሰለጥኑት ኢንዱስትሪ መር ስልጠናዎች ውጤት እያመጡ በመሆኑ ኢንዱስትሪዎች ከኮሌጆች ጋር በፈቃደኝነት ተቀራርበው መስራት አለባቸው ሲሉ ገልፀዋል።
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ Education and Skills for Employ Ability ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት ኮሌጁ የኢንዱስትሪዎች ፍላጎትን በማጤን ከውጪ የሚመጡ ባለሞያዎችን በመተካት የኮሌጁ ምሁራንን በማብቃት ምሁራን ብቁ የሆኑ ሰልጣኞችን በማውጣት የተሻለ አፈፃፀም ማምጣት ያስችለናል ሲሉ ገልፀውልናል።
በመድረኩ የተገኙት ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተወጣጡና ባለድርሻ አካላት ውይይት አካሒደዋል።
ይህ Education and Skills for Employ Ability ፕሮጀክት ከአለም ባንክ በተገኘ 6.7 ሚሊየን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የ5አመት የስልጠና መርሀግብር መሆኑ ታውቋል።
©️ ድሬቲቪ
#ዜና | ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተዉጣጡ ከ30 በላይ የሴት ኢንተርፕራይዞች ከ360 በላይ ፍየሎች ድጋፍ ተበረከተ።
#Diretv አማርኛ ታህሳስ 3/2017
ድጋፉን የሰጠው የድሬደዋ የስራና ክህሎት ቢሮ ሲሆን ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (snv) በተገኘ የገዘብ ድጋፍ ነው።
የድሬደዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ድጋፉን በተበረከተበት ወቅት እንዳሉት ይህ ድጋፍ ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተዉጣጡ ከ30 በላይ የሴት ኢንተርፕራይዞች የተሰጠ ሲሆን ሁሉም በቤተሰብ ደረጃ በማህበር የተደራጁ ናቸው ብለዋል።
አቶ ሮቤል አክለውም ይህ ድጋፍ እንደሀገር ለተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ራስን በምግብ ከመቻል አንጻር ብሎም ከተረጅነት ለመላቀቅ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልጸው ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ በተደረገ የዶሮዎች ድጋፍ ኢንተር ፕራይዞቹ ከራሳቸው ፍጆታ አልፈው ዶሮ እና እንቁላል ለገበያ በማቅረብ የዋጋ ንረትን በማረጋጋት በኩል አበረታች ውጤት እያሳዩ ነው ብለዋል።
በተያያዘ ዜና የድሬደዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ለአንድ ማዕከል አመራሮች እና ባለሞያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።
የቢሮው ሀላፊ ስልጠናውን ባስጀመሩበት ወቅት ስልጠናው በ4 ዋናዋና ነጥቦች ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል እነዚህም የተቋም ግንባታ፣ተግባር ወይም ክህሎት መር የስራ እድል ጠራ፣ የስልጠና ዘርፎች እና የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳዮች ናቸው።
ሀላፊው በወቅቱ ቢሮው በጀመራቸው አዳዲስ እሳቤዎች ላይ አቅም በመገንባት የእሴት ሰንሰለት በጠበቀ መልኩ የስራ እድል መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል። ስልጠናዉም በነገው እለት እንደሚጠናቀቅ ከመርሀ ግብሩ ለማወቅ ተችሏል።
©️ ድሬቲቪ
ጠቃሚ አገር በቀል እውቀት፣ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ ተካሄደ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ጠቃሚ አገር በቀል እውቀት፣ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ምንነትና መረጃ አሰባሰብ ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችል መድረክ ለወረዳ አንድ ማዕከላትና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት አዘጋጀ።
በግንዛቤ ማስጨበጫና በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆኑ አገርበቀል እውቀቶችንና ክህሎቶችን በመለየትእያዳበሩ የሚያድጉበት አመቺ ሁኔታ ማመቻቸት ላይ በተለይ በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተመላከተው መሰረት ለአገርበቀል እውቀቶችንና ክህሎቶችን ማልማት ትኩረት መሰጠቱ ትልቅ አቅም መሆኑም ተገልጿል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 3/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ጋር በመተባበር የኩባንያ ውስጥ ስልጠና ለማጠናከር የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠ፡፡
ይህም ስልጠና በ2017 ዓ.ም የኩባንያ ውስጥ ስልጠና ለመስጠት በአስተዳደሩ ከሚገኙ ለትብብር ስልጠና መስጫነት ከተመረጡ ኩባንያዎች በ4 የሙያ ዘርፎች ማለትም በማኑፋክቸሪንግ፣ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ፣ በሆቴልና ቱሪዝም እንዲሁም በአውቶሞቲቭ ሙያዎች ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በተውጣጡ አሰልጣኞች የኩባንያዎቹን ሰራተኞች ያለባቸውን የክህሎት ክፍተት በመለየት ስልጠና ለመስጠት ያስችል ዘንድ ከ4ቱ ዘርፎች ለተውጣጡ አሰልጣኝ መምህራንና ስልጠና አስተባባሪዎች የአሰልጣች ስልጠናው መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡
የስልጠናው ዋና አላማ የኩባንያ ሰራተኞችን በማብቃት፤ የቴክኖሎጂ ክፈተቶችን በመሙላት ምርትና ምረታማነትን ማሳደግ ሲሆን በተጨማሪም የአሰልጣኝ መምህራንን አቅም በማሳደግ በትብብር ስልጠና ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የጥራት ችግሮችን ከወዲሁ ለመፍታት ማስቻል ነው ሲሉ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ጀማል አደን ገልጸዋል ፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ADRA ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በፕሮጀክቱ አፈፃፀም ላይ በየጊዜው የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ከባለድርሻ እካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
በመድረኩ የመጀመርያ ዙር ተመራቂ ሰልጣኞችን በማደራጀት ሂደት ውስጥ ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች ለመለየት እና የመፍትሄ አቅጣጫ ለማስቀመጥ በአስተዳደሩ ከከተማና ከገጠር የተወጣጡ አራት ክላስተሮች በተገኙበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል::
በእለቱ ባለድርሻ አካላቱን ያወያዩት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊና የኤጀንሲው ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጥፋ ለተሳታፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት ዘርፉ አዲስ ከመሆኑ አኳያ ብዙ ያልተነኩ የስራ ዕድሎችን መፍጠር የሚያስችል በመሆኑ እንዲሁም በእስተዳደሩ በሚገኙ ገጠር ወረዳዎች ውስጥ ከተወሰኑት በቀር የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ እለመደረጉን እስታውሰው ይህን ሁሉ አጋጣሚ በእጃችን ይዘን ሰልጣኞቹን ለማደራጀትና ወደ ስራ ለማስገባት ምክንያት ምንደረድር ከሆን ችግሩ ያለው እኛው ጋር ነውም ብለዋል::
በዘርፉ የገጠሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ሰፋ ያለ ውይይትም የመጀመርያ ዙር ሰልጣኞች በገጠርም ሆነ በከተማው በአፋጣኝ ወደ ስራ የሚገቡበት ሁኔታ ምችችት እንዲደረግና ለዚህም ጉዳዩን በባለቤትነት የያዙት ባለድርሻ አካላት ተቀዳሚ ተግባራቸው አድርገው ሊወስዱትና ጉዳዩንም ከዳር ሊያደርሱት እንደሚገባ ተገልፇል::
በተጨማሪም ሰልጣኞች የወሰዱት የሙያ ክህሎት ወደ ሀብት እንዲለወጥ እንዲሁም ያሰለጠንናቸው ወጣቶች ወደ ስራ መሰማራታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ዘርፉ ላይ ያለውን የሀብት ብክነት እንደሚታደግ የተገለፀ ሲሆን ሁሉም የባለድርሻ አካላት በመረባረብ የስልጠናውን ውጤት ማሳየት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል::
በመጨረሻም ለሁለተኛ ዙር ስልጠና በተደረገው የሰልጣኝ የምልመላ ሂደት ላይ እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮች በመድረኩ በዝርዝር ተነስተው ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በገጠሩ ያሉ ወጣቶችን በምልመላው መስፈርት መሰረት ተመልምለው ለክላስተር ሀላፊዋች ወደ ስልጠናው እንዲገቡ ጠንከር ያለ መልእክትም ተላልፏል።
በመድረኩ ማገባደጃም በአስተዳደሩ ከሚገኙ የከተማ እና የገጠር አራት ክላስተሮች የተወጣጡ የአንድ ማዕከል ባለሞያዎች እና ሀላፊዎች የጋራ ውይይት አካሂደዋል::
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 29/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ ዓመት በተቋሙ ለሚጀመረው የEASE ፕሮጀክት SIP Validation እና የፕሮጀክት ማስጀመርያ መድረክ አካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የስልጠና መርሀ-ግብር SIP(Strategic Investment Plan) ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በእለቱ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም ይህን የEASE ፕሮጀክት ትግበራ ላይ ሲውል የከተማና የገጠር ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ መሆን እንደሚገባው ተናግረው አያይዘውም መሰል ፕሮጀክቶች በአግባቡ ካልተመሩ እና በትክክል ለተቀመጠላቸው አላማ ማይውሉ ከሆነ ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው እንደሚያመዝን ጠቅሰው ኮሌጁ ከሌሎች ትምህርት በመውሰድ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት እቅድ መሰረት እንዲመራና የሚፈለገውን ግብ እንዲመታ አደራ ብለዋል::
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ እሰፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም ይህ ፕሮጀክት የኮሌጁ የፈንድ ራይዚንግ ክፍል የመጀመርያ ስራ የሆነው የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀክት መሆኑን አስታውሰው በብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ታልፎና ብዙ ኮሚትመንት ተጨምሮበት ዛሬ ለደረስንበት ደረጃ መብቃቱን ጠቅሰው በነበረው ሂደት ላይም ቀላል ማይባሉ እድካሚና እሰልቺ መንገዶች ታልፈው እዚህ እንደደረሰ በመግለፅ ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ትልቁን ሚና ለተወጡት የፕሮጀክት አስተባባሪዎች ትልቅ ምስጋና አቅርበዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ 5 አመታት ውስጥ አንድ የራሱን አሻራ አሳርፎ የሚያልፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀው ዛሬ ይህ ፕሮጀክት ለሰራተኛው ሲቀርብም በተቻለ መጠን የሰራተኛውን ተሳትፎና የሁሉንም ሰው ርብርብ እንደሚጠይቅ ግንዛቤ ለመፍጠር ሲሆን የፕሮጀክት ውጤታማነት የሚለካውም በሁሉም የጋራ ተሳትፎ መሆኑንም አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል::
በመድረኩ የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀርት ሰነድ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለተቋሙ ሰራተኛ የቀረበ ሲሆን በዚህም ይህ ፕሮጀክት ከምን ተነስቶ እንደተጀመረና አላማውስ ምንድነው ከሚለው ጀምሮ የፕሮጀክቱን ዋና ሰነድ በዝርዝር አቅርበዋል::
በመጨረሻም የፕሮጀክቱን SIP(Strategic Investment Plan) እንዲሁም ከፕሮጀክቱ የሚጠበቁ ውጤቶችን በተመለከት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ በሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን አጠቃላይ በመድረኩ በቀረቡ ሰነዶች ላይ ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጎበታል::
ፕሮጀክቱ በዋናነት የስራ እድል ትስስርን ይፈጥራል የተባለ ሲሆን ይህም በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካቶችን የሞያ ክህሎትን በማሰልጠን ከገበያው ጋር የሚያስተሳስር መሆኑም ተገልፇል።
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 28/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
