The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
前往频道在 Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
显示更多3 291
订阅者
+224 小时
+127 天
+10030 天
帖子存档
ለቃሉ እና ቁዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ለ31 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ተሰጥቷል
* * * * * *
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አዶላ ገናሌ ሲኖዶስ በተካሄደ የቀሳውስት ምደባ ሥነ-ሥርዓት የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃልና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ ለ31 አገልጋዮች በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የቅስና ሃላፊነት ተሰጥቷል።
የቤተ ክርስቲያኒቱም የወንጌል እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማር ለእጩ ቀሳውስቱና ለምዕመናን የማበረታቻ ቃል አስተላልፈዋል።
በስፍራውም ምዕመናን፣ የእጩ ቀሳውስት ቤተሰቦች፣ የሲኖዶሱ አገልጋዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ለእጩ ቀሳውስቱም እጅ በመጫን ስአገልግሎታቸው ሥኬት ተፀልዮላቸዋል።
በአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ እየተካሄደ ስላለው ሰፊ የወንጌል አገልግሎት እና ወደ ማሳው አገልግሎት ስለተጨመሩ ቀሳውስት የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።
ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
አዶላ ወዩ፣ ምስራቅ ጉጂ
_ _ _ _ _ _
Wendmagen Youth H Office:
Tajaajila Sagalee Waaqayyoo fi Dhoksaalee Qulqulluutiif Tajaajiltootni 31 Lubummaan Muudaman.
* * * * * *
Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itoophiyaa, Sinoodoosii Adoolaa Gannaaleetti sagantaa eebbaa fi rammaddii lubootaatiin, tajaajila Sagalee Waaqayyoo fi Dhoksaalee Qulqulluutiif tajaajiltoota 31'f Pirezidaantii Waldattii kan ta'an Luba Dr. Yoonaas Yiggazuutiin itti gaafatamni lubummaa kennameera.
Daarektara Qajeelcha Tajaajila Wangeelaa fi Ti'ooloojii Waldattii kan ta'an Lubni Dr. Lalisaa Daani'eel Sagalee Waaqayyoo barsiisuudhaan, luboota kaadhimamtootaaf gorsa kennaniiru.
Sagantaa kanarratti, amantootni, maatiin luboota kaadhimamtootaa, tajaajiltootni sinoodoosichaa fi keessummootni waamichi godhameef adda addaa argamaniiru. Luboota ramaddiin keennameefis harka irra kaa'uun kadhannaan godhameera.
Sinoodoosii Adoolaa Gannaaleetti hojii Wangeelaa bal'aa hojjatamaa jiruuf, tajaajila Wangeelaatiif tajaajiltoota dabalamaa jiranuuf Waaqayyoof galanni haa ta'u!
Adoolessa 20, 2017
Adoolaa Woyyuu, Gujii Bahaa
የኢትዮጵያን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የአለም አቀፍ ሚስዮን ማህበር ዳይሬተር ቄስ ጥላዬ ዳባ እና እሳቸው የመሩት የሚስዮን ላኪ የስራ ዘርፎች ልዑክ በሰሜን ኬንያ የአገልግሎት ጉብኝት አደረገ
* * * * * *
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የአለማቀፍ ሚሲዮን ማህበር የመስክ አግልግሎትን ይበልጥ ዉጤታማ ለማድረግና ሚሲዮናዊያንን ለማበረታታት ብሎም ከታለመለት አንጻር ለመገምገም ላኪ የስራ ዘርፎችን በማስተባበር የመስክ ጉብኝት በሰሜን ኬንያ አድርጎ ተመልሶአል። ይህ ልምድ እያደገ የመጣዉን ይህን አገልግሎት የሚያጠናክር ሲሆን በቀጣይነት መደረግ ስላለበት ስልት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ የጋራ ግንዛቤ ወስደናል።
የሚስዮን አገልግሎቱም ጉብኝቱን ተከትሎ ዳይሬክተሩ ባጋሩት መልዕክት "ሚሲዮናዊያን የሚኖሩትን ማየት በጌታ የዳኑ ምእመናንን በእንባ የታጀብ ምስጋና መስማት፣ ወንጌል በአንድ ከበሽታ በተፈወሰ ሰዉ ምክንያት አካባቢዉን ሲያጥለቀልቅ እና ቤተክርስቲያን በየቦታዉ ተተክሎ ከማየት የበለጠ ደስታ ምን አለ?" ብለዋል።
ልዑኩም አራት ቀናትን ያስቆጠረ ጉዞ በማድረግ ከምዕመናን ጋር የማምለክ፤ ከሚስዮናውያን ጋር ማዕድ የመካፈል፣ የመፀለይ እና ቀጣይ አገልግሎቶችን አስመልክቶ የመምከር ዕድል አግኝተዋል።
በቤተ ክርስቲያኑቱ የአለም አቀፍ ሚስዮን ማህበር በኩል በወንጌል እየተደረሱ ስለሚገኙ በአፍሪካ፣ በኤስያ፣ በላቲን አሜሪካና በመካከለኛ ሩቅ ምራቅ ስላሉ ማህበረሰቦች የሚስዮኑ ባለቤት እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። አገልግሎቱም በተቀረው የአለማችን ክፍል እንዲሰፋ ሁላችንም ስለ አገልግሉቱ እንፀልይ፤ አገልግሎቱንም እንደግፍ።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ8 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት የተሰጠች ሲሆን የሰርትፊኬት የሥነ መለኮት ትምህርታቸውን ያጠናጠናቀቁ 12 አገልጋዮችን በማስመረቅ ወደ አገልግሎት አሰማርታለች።
በምዕረብ ግቤ ሲኖዶስ የቃሉንና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዩናስ ይገዙ ለ8 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ተሰጥቷል። ፕሬዚዳንቱም በመልዕክታነው እጩ ቀሳውስቱ ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁና በቤተ ክርስቲያኒቱ ለማገልገል ብቁ መሆናቸው የተረጋገጠ መሆኑን በመጥቀስ ነገር ግን እራሳቸውን ለማሳደግና ለምዕመኑ መልካም እረኞች ለመሆን ሁል ጊዜ የሚተጉና የሚማሩ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በተመሳሳይ መርሃ ግብር በሲኖዶሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ በሰርቲፊኬት ፕሮግራም የሥነ መለኮት እና የአገልግሎት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 12 አገልጋዮች ተመርቀው ወደ አገልግሎት ተሰማርተዋል። በትምህት ቆይታቸውም ጥሩ ውጤት ላመጡ ተመራቂ ተማሪዎች የማበረታቻ ሥጦታ ተበርክቷል።
የቤተ ክርስቲያኒቱም የሚስዮንና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማር ለእጩ ቀሳውስቱ እና ለተመራቂ ተማሪዎቹ የማበረታቻ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመርሃ ግብሩም የተገኙ የቀድሞ ቀሳውስት እና የሲኖዶሱ መሪዎች ለአገልዩቹ እጅ በመጫን ፀልየዋል።
በዕለቱም ለበርካታ አመታት በቤተ ክርስቲያኒቱ ከማህበረ ምዕመናን አንስቶ በተለያዩ ደረጃዎች ያገለገሉት የቄስ በየነ ኩብሩ "የመሪ ጥሪና ሚና" በሚል ርዕስ የተፃፈው መጽሐፍ ተመርቋል።
ለምዕመናን ጥበቃና ለቤቱ አገልግሎት አገልጋዮችን የሰጠን ጌታ የተመሰገነ ይሁን!
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
