The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Відкрити в Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Показати більше3 501
Підписники
+124 години
+77 днів
+10830 днів
Архів дописів
✨🎶 የሙዚቃ ሰርቲፊኬት መርሐ ግብር የማታ ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን።
ሁለንተናዊ የልጆችና ታዳጊዎች አገልግሎት ስልጠና በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ሀዋሳ ከተማ ተሰጠ
'ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ታዳጊዎቻችን' በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በሲኖዶሱ ማዕከል ሀዋሳ ከተማ ተሰጥቷል። ስልጠናው የተሰጠው ከሲኖዶሱ ጋር በመተባበር በዋናው ጽ/ቤት የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ በኩል ሲሆን: ከሲኖዶሱ ሰበኮች እና ማ/ምዕመናናት የተወጣጡ መሪዎች እና የልጆችና ወጣቶች አገልጋዮች ተሳትፈዋል::
ከስልጠናው ጎን ለጎን ለልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት የሚጠቅሙ: ታቅዶ እየተሰራበት ላለው ቤተ መጻህፍትን በእያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን የማስጀመር ራዕይ የሚረዱ የልጆች መጽሐፍ ቅዱሶች: የወጣቶች ማስተማርያ መጽሐፍቶች: ለአገልጋዮች እና ምዕመናን: ለደቀመዛሙርትነት እና ለሌሎች ለቤተክርስቲያን ስነ መለኮታዊ አስተምህሮ የሚረዱ የተለያዩ መጽሐፍቶች በመምሪያው በኩል በድጋፍ መልክ ተሰጥቷቸዋል::
ስልጠናውን የሰጡት የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ ኡዴሣ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት: Rafiki Foundation እና Lutheran Heritage Foundation እና ሌሎችንም በማመስገን : መጽሐፍቶቹን ለቤተክርስቲያኒቱ ማ/ምዕመናናት: ሴሚናሪዎች: መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጆች እና ት/ቤቶች ከተባባሪ ድርጅቶች ጋር በመሆን ድጋፍ የማድረጉ ስራ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በተጨማሪም ቤተክርስቲያኒቱ ባስቀመጠችው አቅጣጫ መሰረት ሲኖዶሱ የልጆች አገልግሎትን በመምሪያ ደረጃ በማደራጀት ቀዳሚ መሆኑን በማንሳት: ስለ ምሳሌያዊ ተግባራቸው አመስግነው ሌሎች ሲኖዶሶችም ይሄን መልካም ልምድ ወስደው በልጆች አገልግሎት ላይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በስልጠናው መክፈቻ የተገኙ የሲኖዶሱ ፕረዚዳንት ቄስ ኢያሱ ጠግቾ ስልጠናው የልጆች እና ታዳጊዎችን አገልግሎትን ጊዜው በሚፈልግ መልኩ ለማሳደግ አስፈላጊ እና ወቅቱን ያገናዘበ መሆኑን ገልጸው: ሰልጣኞች በወሰዱት ስልጠና መሰረት ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው መልዕክት አስተላልፈዋል::
በተቀሩት የቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶችም ተመሳሳይ ስልጠና ከሲኖዶሶች ጋር በመተባበር የሚቀጥል ይሆናል::
===
📷 : Biniam, Alamura Congregation , Hawassa
EECMY Children Ministry - MY Sunday School #Hawassa
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምስራች ድምጽ መገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል ፕሮግራም የፎቶ ምልከታ።
የጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የስልጠና ማዕከል አስተዳደርና ሰራተኞች የጌታችን እና የመዳኒታችን ኢየሱስ ክስትቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በታላቅ ድምቀት አከበሩ።
በአከባበሩም የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ፣ የኢትዮጵያዊ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሀፊ ቄስ ዶ/ር ደረጀ ጀምበሩ እና የቤተ ክርስቲያኒቱ የክብር ፕሬዚዳንት ቄስ ኢተፋ ጎበና ተገኝተው መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
የበዓሉ አከባበር አያይዘው የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና አባቶች በታላቅ ትህትና እና መሰጠት ቤተ ክርስቲያናችንን እና መላውን ወንጌል አማኞችን በተቋሙ ከእሁድ እስከ እሁድ እያስተናገዱ የሚገኙ የተቋሙ ሰራተኞችን እንዲባርኩ በማሰብ መሆኑን የማዕከሉ የአስተዳደር ሀላፊ የሆኑት ቄስ ሀረገወይን ገልጸዋል።
የማዕከሉም የሰራተኞች ኳየር በዕለቱ ያገለገለ ሲሆን የማዕከሉን የላይብረሪ አገልግሎት ለማጠናከር የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች መምሪያ የመንፈሳዊ መጽሐፍት ድጋፍ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዋናው ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል ዋዜማን በጋራ አክብረዋል።
ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም
ፎቶ - ህሊና ታደሰ
