ch
Feedback
Ethiopian Business Network

Ethiopian Business Network

前往频道在 Telegram

የኢትዮጵያ ብቸኛ የስራ ፈጠራ መድረክ! ማንኛውንም ፕሮጀክት፣ ሃሳብ ለህዝብ በማድረስ አዳዲስ ድርጅቶችን ለማቋቋም የነፃ እገዛ እናደርጋለን! ያነጋግሩን!

显示更多
4 483
订阅者
-124 小时
-217
-5930
帖子存档
አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ሆኖ እንዲቀጥል ሃሳብ ቀረበ‼ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሀገር ግንባታ አጀንዳ ላይ በተደረገ ውይይት 📌አማርኛ፣ 📌ኦሮምኛ፣ 📌ትግርኛ፣ 📌አፋርኛ እና 📌ሶማሊኛ የፌዴራል
አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ሆኖ እንዲቀጥል ሃሳብ ቀረበ‼ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሀገር ግንባታ አጀንዳ ላይ በተደረገ ውይይት 📌አማርኛ፣ 📌ኦሮምኛ፣ 📌ትግርኛ፣ 📌አፋርኛ እና 📌ሶማሊኛ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ ምክረ ሀሳብ ቀረበ። በምክክሩ አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ሆኖ እንዲቀጥል የሚል ሀሳብ የተነሳ ሲሆን፣ 📌እንግሊዝኛ፣ 📌አረብኛ፣ 📌ፈረንሳይኛ እና 📌ቻይንኛን የመሳሰሉ የውጭ ቋንቋዎች በስርዓተ ትምህርት እንዲካተቱ ወይም የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ የቀረበው ሀሳብ "የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን ያጠፋል" በሚል አከራካሪ ሆኗል። የቀረቡት ምክረ ሀሳቦች በ4 ሺህ ተሳታፊዎች ተመክሮባቸው የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥባቸው መሆኑ ተገልጿል።

Job Title: ምግብ ሰሪ Job Type: On-site - Permanent (Full-time) Work Location: Addis Ababa, Ethiopia Salary/Compensation: Monthly Deadline: August 6th, 2026 Description: የስራ ማስታወቂያ፦ ለምግብ ሰሪ(chef) በአራት ኪሎ አካባቢ የሚገኝ ካፌያችን የተለያዩ የካፌ ምግቦችን ማዘጋጀት የሚችል ሼፍ መቅጠር ይፈልጋል። ተፈላጊ ችሎታዎች እና መስፈርቶች፦ • በሼፍነት ሙያ ቢያንስ 1 ዓመት የተረጋገጠ የስራ ልምድ ያለው/ላት። ዋና ዋና ኃላፊነቶች (የሚዘጋጁ ምግቦች ዝርዝር)፦የጾ ... [view details below] ______________ Private Client 3 Jobs PostedOn-site - Permanent From: afriworket.com | @freelanceethbot | @freelance_ethio | @afriworkamharic

መረጃ‼️ 59 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድ ክፍል ቤት ውስጥ እንደሚኖር የፌደራል ስታትስቲክስ አገልግሎት ከአውሮፓዊያኑ 2024 እስከ 2025 ያካሄደው ጥናት አመለከተ። የመኖሪያ ቤቶች መጨናነቅ
መረጃ‼️ 59 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድ ክፍል ቤት ውስጥ እንደሚኖር የፌደራል ስታትስቲክስ አገልግሎት ከአውሮፓዊያኑ 2024 እስከ 2025 ያካሄደው ጥናት አመለከተ። የመኖሪያ ቤቶች መጨናነቅ በተለይ በከተሞች አካባቢ እንዲባባስ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገው ያልተቋረጠ ፍልሠት መኾኑን ዋዜማ ከጥናቱ ላይ ተመልክታለች። በተጠቀሠው ጊዜ ውስጥ በጥናቱ 31 በመቶ የሴቶች እና 24 በመቶ የወንዶች ፍልሠት ተመዝግቧል። የተሻለ የሥራ ዕድል፣ ትምህርትና የመሠረተ ልማት አቅርቦትን ፍለጋ የሚደረገው ፍልሠት፣ በከተሞች ላይ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠሩ በባለ ሁለት ክፍል ቤቶች የሚኖሩ ዜጎች ድርሻ 31 በመቶ መድረሱን ሪፖርቱ ያትቷል።

የስራ ማስታወቂያ ---------//--------- 👉 የስራ መደቡ መጠሪያ :- ጉዳይ አስፈፃሚ 👉 የስራ ቦታ:-  አዲስ አበባ 👉 ብዛት :- አንድ 👉 የቅጥር ሁኔታ :- በጊዜያዊነት 👉 ደመወዝ :- በስምምነት 👉 ፃታ :- ማንኛውም (ሴት ብትሆን ይመረጣል) ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች    ከታች የተያያዘው የቴሌግራም Username ላይ 👇👇👇👇 @Danimakh መታወቂያችሁን ብቻ በመላክ ማመልከት ትችላላችሁ!

ኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ባለሀብቶችንና ኢንቨስተሮችን ለመሳብ ባዘጋጀችውና “ጎልደን ቪዛ” (Golden Visa) በተሰኘው የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ፈቃድ ፕሮግራም ላይ የ10 ሚሊዮን አሜሪካን ዶላር የኢንቨ
ኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ባለሀብቶችንና ኢንቨስተሮችን ለመሳብ ባዘጋጀችውና “ጎልደን ቪዛ” (Golden Visa) በተሰኘው የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ፈቃድ ፕሮግራም ላይ የ10 ሚሊዮን አሜሪካን ዶላር የኢንቨስትመንት ቅድመ-ሁኔታ ማስቀመጧ ይፋ ሆኗል። ይህ አዲስ መመሪያ ከፍተኛ የውጭ ሀገር ካፒታልን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባትና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ ያለመ ቢሆንም፣ የተቀመጠው የገንዘብ መጠን ከሌሎች የአፍሪካና የዓለም ሀገራት ተመሳሳይ ፕሮግራሞች ጋር ሲነጻጸር እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በኢኮኖሚ ባለሙያዎችና በባለሀብቶች ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል። በዚህ ፕሮግራም መሰረት የተዋቀረውን የ10 ሚሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት መስፈርት የሚያሟሉ የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ ውስጥ የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ፈቃድና ልዩ ልዩ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን የማግኘት መብት የሚሰጣቸው ሲሆን፣ መንግስት እርምጃው ሀገሪቱ በቅርቡ የጀመረችውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የኢንቨስትመንት ምህዳር ማደስ ጥረት የሚያግዝ መሆኑን እምነቱን ጥሏል። ይሁን እንጂ በርካታ ተችዎች እንደሚሉት፣ ይህን ያህል ከፍተኛ የገንዘብ መጠን እንደ ቅድመ-ሁኔታ ማስቀመጥ በተለይም ከአፍሪካና ታዳጊ ሀገራት የሚመጡ ባለሀብቶችን ተሳትፎ ሊገድብ ይችላል በሚል ስጋት እየተነሳበት የሚገኝ ሲሆን፣ የፖሊሲው አፈፃፀም እና በኢንቨስትመንት ፍሰቱ ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ ወደፊት የሚታይ ይሆናል።

በቅርቡ በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ ጎዳናዎች ላይ አንድ ታዋቂ ዩቲዩበር (YouTuber) ሰዎችን እያስቆመ በሚያደርገው ተንቀሳቃሽ ቃለመጠይቅ ላይ፣ አቀራረቧ ፈረንጅ የሚመስል ነገር ግን በዜግነቷ ኢትዮጵያዊት የሆነች ወጣት የሰጠችው ምላሽ ማህበራዊ ሚዲያውን በከፍተኛ ሁኔታ እያነጋገረ ይገኛል። "ቪኪ" (Viki) በሚል ስም ራሷን ያስተዋወቀችውና ወደ አሜሪካ ከመጣች ገና ሁለት ዓመታት ብቻ እንደሆናት የገለጸችው ይህች ወጣት፣ ጋዜጠኛው በኒውዮርክ ከተማ ለመኖር በወር ምን ያህል ወጪ እንደምታወጣ ላቀረበላት ጥያቄ የሰጠችው ምላሽ እጅግ አስደንጋጭ ነበር። በየወሩ ከ35 ሺህ እስከ 40 ሺህ ዶላር ወጪ እንደምታደርግ የተናገረች ሲሆን፣ ይህንን ያህል ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የምታገኝበትን የስራ መስክ ስትጠየቅ ግን "ምንም አይነት ስራ የለኝም" ስትል ምላሽ ሰጥታለች። ይህ በየወሩ የምታወጣው 40 ሺህ ዶላር አሁን ባለው የኢኮኖሚ እውነታ ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲቀየር ከ6.4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት በመሆኑ፣ ያለምንም የስራ ገቢ ይህንን ያህል የቅንጦት ሕይወት እንዴት ልትኖር እንደቻለች በጠያቂውም ሆነ በተመልካቹ ዘንድ ትልቅ ጥያቄና መደናገጥን ፈጥሯል። ይሁን እንጂ ከጉዳዩ በስተጀርባ ያለው እውነት ሲመረመር፣ ይህች ወጣት በኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር ውስጥ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት የባለስልጣኑ የአቶ ዘሱ ወልደጊዮርጊስ ልጅ መሆኗ ተነግሯል። ይህ መረጃ ይፋ መሆኑን ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ድምፅ እያሰሙ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ህዝብ የእለት ጉርሱን ለመሸፈንና የኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም ሌሊት ከቀን እየደከመ፣ በግዴታም ይሁን በፈቃደኝነት የሚከፍለው ግብርና ታክስ ለሀገር ልማትና ለህዝብ አገልግሎት መዋል ሲገባው፣ የከፍተኛ ባለስልጣናት ልጆች በውጭ ሀገር ያለ ምንም ስራ በንጹሃን ዜጎች ገንዘብ እንዲህ ባለ የቅንጦትና የአምሮት ሕይወት እንዲኖሩበት መደረጉ እጅግ አሳዛኝና አሳሳቢ ክስተት ነው። እንዲህ አይነቶቹ ምናልባትም በሙስና እና በህዝብ ሀብት ያለአግባብ መበልጸግ ላይ የሚነሱ ጥርጣሬዎች በተቋማት ላይ ያለውን የህዝብ እምነት ሙሉ በሙሉ የሚሸረሽሩ በመሆናቸው፣ የሚመለከታቸው የህግ አካላት በባለስልጣናቱና በቤተሰቦቻቸው የሀብት ምንጭ ላይ ጥብቅና ግልጽ የሆነ ማጣራት ሊያደርጉ እንደሚገባ የብዙዎች ድምጽ እየሆነ ነው።

አስቸኳይ የጥንቃቄ መልእክት! Trust፣ Google TV እና Known የተባሉ ጉዳት አምጪ የአንድሮይድ መተግበሪያዎች በማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት እንደ Google Chrome፣ Telegram እና WhatsApp ባሉ መድረኮች ላይ በስፋት እየተሰራጩ ነው። በስልክዎ ላይ ከተጫኑ፣ እርስዎ ሳያውቁ ገንዘብ ሊያዘዋውሩብዎ እና ሌላም ጉዳት ሊያደርሱብዎ ይችላሉ። በመሆኑም፣ መተግበሪያዎችን ወደ ስልክዎ ለማውረድ፣ እንደ Play Store ወይም App Store ያሉ የታመኑ ምንጮችን ይጠቀሙ። ነገር ግን፣ በGoogle Chrome፣ በTelegram ወይም በWhatsApp አማካይነት የሚላኩ መተግበሪያዎችን ወደ ስልክዎ አያውርዱ፤ በእነሱ በኩል የሚላኩ አጠራጣሪ ማስፈንጠሪያዎችንም ሳያረጋግጡ አይክፈቱ። በተጨማሪም፣ በሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎ ላይ የባዮሜትሪክ (Biometrics) እና የፒን (PIN) የደኅንነት ማረጋገጫዎችን አጣምረው ይጠቀሙ። አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥምዎ፣ በ951 በነጻ ደውለው ድጋፍ ሊያገኙ ይችላሉ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!

ኢትዮጵያ የ4 ቢሊዮን ዶላሩን የኩርሙክ ወርቅ ማውጫ ግዢ አጸደቀች የኢትዮጵያ መንግስት የቻይናው ዚጂን ጎልድ ኢንተርናሽናል የካናዳውን አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በ4 ቢሊዮን ዶላር ለመግዛት ያደረገውን
ኢትዮጵያ የ4 ቢሊዮን ዶላሩን የኩርሙክ ወርቅ ማውጫ ግዢ አጸደቀች የኢትዮጵያ መንግስት የቻይናው ዚጂን ጎልድ ኢንተርናሽናል የካናዳውን አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በ4 ቢሊዮን ዶላር ለመግዛት ያደረገውን ስምምነት በይፋ ማጽደቁን ካፒታል ከምንጮቹ ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል። በአሶሳ ዞን ኩርሙክ ወረዳ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት፣ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ትልቁ ዘመናዊ የወርቅ ማውጫ ይሆናል። በ620 ሚሊዮን ዶላር ወጪ እየተገነባ ያለው ማዕድኑ፣ በዓመት ወደ 290 ሺህ አውንስ ወርቅ የማምረት አቅም አለው። የኩባንያው የባለቤትነት መብት ቢቀየርም፣ ነባሩ የህግ እና የውል ማዕቀፍ እንደማይቀየር ተገልጿል። ዝርዝሩን ያንብቡ https://capitalethiopia.com/2026/07/12/ethiopia-clears-zijin-golds-usd-4-billion-acquisition-of-allied-gold/

ጎተራ ኮንዶሚኒየም አካባቢ የሚገኝ ወረዳ ላይ የምትሰሩ ሀላፊዎች ደግሞ ምን አይነት ብል'ግና ጀመራችሁ..? እንደዚህ ይደረጋል ግን..? 🤦‍♂️ መንግስት ያዋዋለው የ 2 አመት የኮንዶሚኒየም ኪራይ
ጎተራ ኮንዶሚኒየም አካባቢ የሚገኝ ወረዳ ላይ የምትሰሩ ሀላፊዎች ደግሞ ምን አይነት ብል'ግና ጀመራችሁ..? እንደዚህ ይደረጋል ግን..? 🤦‍♂️ መንግስት ያዋዋለው የ 2 አመት የኮንዶሚኒየም ኪራይ ውል ሳያልቅ የቤት ተከራይን ኪራይ ካልጨመሩ የሚሉ አከራዮች እናንተ ጋር እየመጡና ሳንቲም እያስነከሷችሁ ተከራዮችን በጉልበት የምታስወጡትን ነገር መንግስት ያውቀዋል ወይስ የዛ አካባቢ የወረዳ ሀላፊዎች የራሳችሁን መንግስት መስርታችኋል..? ተከራዩ ውል እያለው በሰላም እየኖረ እያለ ከአከራዮች ጋር ተመሳጥራችሁና አሳቻ ሰአት ጠብቃችሁ የተከራይን ቤት ሰብሮ መግባትና እቃውን በ Isuzu መጫን ምን የሚሉት ጉልበ'ተኝነት ነው..? ይሄ ነገር ደግሞ አንድ ቤት ላይ ብቻ አይደለም የሆነው በርካታ ቤቶች ላይ ነው እየሆነ ያለው። የዛ አካባቢ ወረዳ ሀላፊዎች ምንድነው እንደዚህ ውጥ-ርጥር ያደረጋችሁ..? የወረዳ ሀላፊዎች ገንዘብ ከቀመሳችሁ ምንም ነገር ታደርጋላችሁ እሱን እኮ እናውቃለን። ነገር ግን ተከራይ በሌለበት የሰው ቤት ሰብሮ መግባትና እቃውን መጫን በጣም ሰቅ-ጣጭ የሆነ ሌብ'ነት ነው። ይህ በተከራይ ንብረት ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው ልጅ የሰብአዊ መብት እና ክብር ላይ እየተፈፀመ ያለ ግልፅ ጥ'ቃት ነው። ያለ ምንም የፍርድ ቤት ትእዛዝ በወረዳ ሹመኞች አለቅነት ብቻ የሰው ቤት ሰብሮ መግባትና ማፈናቀል ምን የሚሉት ውንብድና ነው..? 🤦‍♂️

"የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ድሮ በነበረው ዋጋ ለማስረከብ እንቸገራለን"ከንቲባ አዳነች አቤቤ ​ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ተረካቢዎች ወቅቱን ያገናዘበና ምክንያታዊ የሆነ ዋጋ መክፈል ግድ እንደሚላቸው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ እንደተናገሩት፥ ቤቶቹን የዛሬ 20 ዓመት በነበረው የዋጋ ተመን ማስተላለፍ የማይቻል ቢሆንም፣ አሁንም ዋጋው ተመጣጣኝ (Affordable) እንዲሆን ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ​ለቤቶቹ የሚሰሩት እንደ መንገድ፣ ፍሳሽ፣ ውሃ እና መብራት ያሉ መሰረተ ልማቶች ሙሉ በሙሉ በከተማው በጀት የሚሸፈኑ ሲሆን፣ መሬትም በነጻ የሚቀርብ በመሆኑ እስካሁን ለተጠቃሚዎች የተላለፉት ቤቶች እስከ 67 በመቶ የሚደርስ የመንግስት ድጎማ የተደረገባቸው ናቸው። ​በሌላ በኩል፣ የመኖሪያ ቤት ልማቱ በከተማ አስተዳደሩ ላይ ከፍተኛ የዕዳ ሸክም መፍጠሩን ከንቲባዋ አስታውቀዋል። ቀድሞ የተገነቡ ቤቶች ዕዳ ሳይከፈል በመቆየቱ፣ ከተማው ከወለድ ጋር 99 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የውርስ ዕዳ እንደነበረበትና ካለፈው ጊዜ ጀምሮ 62 ቢሊዮን ብር መክፈል እንደተቻለ ገልጸዋል። ​በአሁኑ ወቅት ከተማው አሁንም 37 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ዕዳ ያለበት ሲሆን፣ ይህንን ዕዳ በመክፈል ከመንግስት በጀት በተጨማሪ ሌሎች የፋይናንስ አማራጮችን በማፈላለግ ቤቶቹን በብዛት ለመገንባት እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆትን ለሚያጋልጡ ዜጎች ከሚጣለው ቅጣት የ25 በመቶ የገንዘብ ኮሚሽን ክፍያ ሊሰጥ ነው (አዲስ ሪፖርተር ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም)-በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋለው
የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆትን ለሚያጋልጡ ዜጎች ከሚጣለው ቅጣት የ25 በመቶ የገንዘብ ኮሚሽን ክፍያ ሊሰጥ ነው (አዲስ ሪፖርተር ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም)-በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋለውን የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት ለመግታትና በመሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰውን ውድመት ለመከላከል የተቀናጀ የቁጥጥር ሥርዓት እየተዘረጋ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል። የተቋሙ የሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ይሔይስ ስዩም እንደገለጹት፣ የኃይል ስርቆቱ በዋናነት የሚፈጸመው የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች በትክክል እንዳይቆጥሩ በማድረግ ወይም መስመር ወደ ቆጣሪ ከመግባቱ በፊት በቀጥታ በመጥለፍ ወደ መኖሪያ ቤቶችና ወደ ኢንዱስትሪ ማሽኖች በመውሰድ ነው። ይህንን ሕገ-ወጥ ድርጊት በዘላቂነት ለመከላከልም ኅብረተሰቡ ጥቆማ የሚሰጥበት የተደራጀ መመሪያና አሠራር ተቀርጾ ወደ ሥራ ተገብቷል። በአዲሱ መመሪያ መሠረት የኃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን ለሚያጋልጡ ጠቋሚዎች፣ በጥፋተኞቹ ላይ ከሚጣለው ጠቅላላ የገንዘብ ቅጣት ውስጥ የ25 በመቶ የኮሚሽን ክፍያ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። ለአብነትም አንድ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በፈጸመው የቴክኒክ ስርቆት ምክንያት 1 ሚሊዮን ብር ቢቀጣ፣ ጥቆማውን ያቀረበው ግለሰብ የ250 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ በሕጋዊ አሠራር ወዲያውኑ ያገኛል። ባለፈው የ2017 በጀት ዓመት በተደረገ ከፍተኛ ክትትልና የቁጥጥር ሥራ፣ ከኃይል ስርቆትና ከተለያዩ መጋጠሚያዎች ከባከነ ኃይል 259 ሚሊዮን ብር ማስመለስ መቻሉን አቶ ይሔይስ ጠቁመዋል። የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መሠረተ ልማት የጋራ ሀብት በመሆኑ፣ ኅብረተሰቡ የኃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን በምስጢር በማጋለጥና ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ተቋሙ ጥሪ አቅርቧል።

በአዲሱ የታክስ አዋጅ ላይ የተቀመጠዉ የትርፍ ድርሻ (ዲቪደንድ) ታክስ ምጣኔ ከ10 ወደ 15 ፐርሰንት ከፍ እንዲል ተደርጓል። ይህ ውሳኔ የተላለፈው ከአለም አቀፍ አሰራሮች እና ሀገሪቱ ከሌሎች ሀገራት ጋር ከፈረመቻቸው "ድርብ ታክስን የማስቀረት ስምምነቶች" ጋር ህጋዊ ተጣጣሚነትን ለመፍጠር መሆኑ ተገልጿል። ከገንዘብ ሚኒስትር የመጡት አቶ ሙላይ ወልዱ፤ የመንግሥት እና በግሉ ዘርፍ የጋራ የምክክር መድረክ ላይ እንደገለፁት ​እስካሁን የነበረው የ10 ፐርሰንት ታክስ ሀገሪቱ ከሌሎች ሀገራት ጋር በምትደራደረው የ15 ፐርሰንት ስምምነት መሰረት ታክስ ለመሰብሰብ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። ለመሆኑ ከንግዱ ማህበረሰብ ይህ የትርፍ ድርሻ በተመለከተ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ አቶ ሙላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ​#TaxReformEthiopia #DividendTax #TaxPolicy #Ethiopia #EconomicReform #Capitalnewspaper

ለአልጋ 5% ታክስ ተጣለ‼️ በአዲስ አበባ ከተማ በሆቴሎች እና ተመሳሳይ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ላይ የ5 በመቶ ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ተጣለ። ⚫️ በአዲሱ ደንብ ድንጋጌ መሰረት ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም የመኝታ ክፍሎቹን ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሆቴሎች፣ በሪዞርቶች፣ በሞቴሎች እና በሌሎች መሰል የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ አዲስ የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ የሚጥል ደንብ አወጣ። "የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ደንብ ቁጥር 204/2018" በሚል የወጣው ይህ ደንብ፣ የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግና መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በደንቡ አንቀጽ 6 መሠረት፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ተጠቃሚ ለክፍል አገልግሎት ከሚከፍለው ዋጋ ላይ 5 በመቶ (5%) የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ እንዲከፍል ይደረጋል። ይህ የታክስ ተመን የሚሰላው የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ሳይታከልበት ባለው መደበኛ የክፍል ዋጋ ላይ ተመስርቶ መሆኑ ተደንግጓል። ይህ አዲስ የታክስ ሕግ በከተማዋ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ ሁሉንም የመኝታ አገልግሎት ሰጪዎችን የሚያካትት ሲሆን፣ እነዚህም፦ • ከ1 እስከ 7 ኮከብ ደረጃ ያላቸው ሆቴሎች እና ኮከብ የሌላቸው ሆቴሎች፣ • ሪዞርቶች፣ ሎጆች እና ሞቴሎች፣ • የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች (Guest Houses) እና ፔንሲዮኖችን ያጠቃልላል። አገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ በየወሩ ወይም በየሦስት ወሩ (እንደ ግብር ከፋይ ደረጃቸው) የሰበሰቡትን ታክስ ለከተማው ገቢዎች ቢሮ ሪፖርት የማድረግና ገቢ የማድረግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል። ደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች  በየወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ የሚያደርጉ ሲሆን ደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ደግሞ በየሦስት ወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ ያደርጋሉ። ደንቡን በማይተገብሩ፣ ሪፖርት በሚያዘገዩ ወይም የገቢ መረጃ በሚደብቁ ተቋማት ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና ቅጣት እንደሚጣል ተመልክቷል። ለማሳያም ሪፖርት ያዘገየ ተቋም ካለበት ዕዳ ላይ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችልና የታክስ መረጃ መደበቅ ደግሞ በወንጀል እንደሚያስጠይቅ ተደንግጓል። እንደ ደንቡ ድንጋጌ፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ የመመዝገብ ግዴታ ያለበት ሲሆን፣ በሚመዘገብበት ወቅትም የተቋሙን የክፍሎች ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል። ይህ የታክስ አከፋፈል ሂደት ከተቋማቱ የንግድ ፈቃድ እድሳት ጋርም በቀጥታ የተያያዘ ነው። የከተማዋ የቱሪዝም ኮሚሽን የሆቴሎችን የሙያ ብቃት ፈቃድ የሚያድሰው ተቋማቱ ታክሱን በአግባቡ መክፈላቸውን የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ከገቢዎች ቢሮ ሲያቀርቡ ብቻ መሆኑ በደንቡ ላይ በግልጽ ተቀምጧል። የታክስ አሰባሰቡን ግልጽነት ለማረጋገጥም፣ ተቋማቱ በሚሰጡት የሽያጭ ደረሰኝ ላይ "የማዘጋጃ ቤታዊ መኝታ አገልግሎት ታክስ" የሚለው ሐረግ በግልጽ እንዲሰፍር ታዟል። የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ የሌለባቸው ግብር የሚከፍሉ ተቋማት ደግሞ ከሚሰጡት አገልግሎት 70 በመቶው ላይ የ5 በመቶ ታክስ ታስቦ እንዲከፍሉ ይደረጋል። በተጨማሪም ተቋማቱ የሰበሰቡትን የታክስ ገቢ በየወሩ ጠቅልለው ሪፖርት ከማድረጋቸው ባለፈ፣ ሰብስበው ባጠናቀቁ በ30 ቀናት ውስጥ ለዚሁ ተብሎ ወደተከፈተ የባንክ ሒሳብ ገቢ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም በታክስ አሰባሰብና በአሠራር ሂደት ላይ ቅሬታ ካላቸው በየደረጃው ለሚገኝ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ የማቅረብ መብት አላቸው። ኮሚቴው ቅሬታውን ተቀብሎ በ15 የሥራ ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ያለበት ሲሆን፣ በውሳኔው ቅር የተሰኘ ወገን ውሳኔው በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ለከተማ አስተዳደሩ የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል። ማንኛውም የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከመኝታ አገልግሎት የተገኘን ገቢ ወቅቱን ጠብቆ ሪፖርት አለማሳወቅ ለዘገየበት በየወሩ 5 ከመቶ ከክፍያው ከ50 ከመቶ ያልበለጠ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል። በተጨማሪም የታክስ ገቢውን በወቅቱ ገቢ ያላደረገ ተቋም በወቅታዊ የባንክ ብድር ወለድ ተመን መሠረት ወለድና በወለዱ ላይ ተጨማሪ 15 በመቶ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል። አዲስ አበባ የቱሪስት መዳረሻነቷ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ፣ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለከተማዋ የልማት ስራዎች ለማዋል ታስቦ የወጣ መሆኑን የመግቢያው ክፍል ያስረዳል። ይህም የከተማዋን የገቢ መሠረት በማስፋት የንግድ እንቅስቃሴው ለከተማዋ እድገት የሚኖረውን ድርሻ ከፍ ያደርጋል ተብሏል። ይህ ደንብ በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተፈርሞ የወጣ ሲሆን፣ ከሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የጸና ሆኗል። ‎

📢 #ለመረጃ፡ ማንኛውንም የውጭ ምንዛሬ በተወዳዳሪ ተመን ለመግዛትም ሆነ ለመሸጥ፣ የሮሃ የውጭ ምንዛሬ ቢሮን ይጎብኙ። የዕለቱን የምንዛሬ ተመን በመከታተል ፈጣን፣ አስተማማኝ እና ቀልጣፋ አገልግሎት
📢 #ለመረጃ፡ ማንኛውንም የውጭ ምንዛሬ በተወዳዳሪ ተመን ለመግዛትም ሆነ ለመሸጥ፣ የሮሃ የውጭ ምንዛሬ ቢሮን ይጎብኙ። የዕለቱን የምንዛሬ ተመን በመከታተል ፈጣን፣ አስተማማኝ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ያግኙ። 📍 ቅርንጫፎቻችን ✅ ሳር ቤት — አዳምስ ፓቪሊዮን ✅ ካዛንቺስ — ማህቡባ አፓርትመንት (ግራንድ ፓላስ ሆቴል ፊት ለፊት) ✅ ድሬዳዋ — ብሎሰም ሆቴል ✅ ቦሌ ቡልቡላ (ሬፌንቲ የገበያ ማዕከል) 📞 ለመረጃ እና አቅጣጫ ለመጠየቅ ☎️ +251 956 555 333 ☎️ +251 991 332 000 ☎️ +251 960 444 333 🌐 ማህበራዊ ሚዲያዎቻችን 🔹 Telegram: https://t.me/roohaforex 🔹 Facebook: https://www.facebook.com/share/19hCtXhSH3/?mibextid=wwXIfr 🔹 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/rooha-forex-bureau/Dcn/

ማስጠንቀቂያ_ለእህቶቻችን እና ለወላጆች! በጀሞ አካባቢ የተፈጸመ የእገታ ሙከራ እና የተማርንበት ትልቅ ትምህርት ትላንት በጀሞ አካባቢ በማህበራዊ ሚዲያ (ኢንስታግራም) በተደረገ ትውውቅ ምክንያት በአንዲት እህታችን እና በጓደኛዋ ላይ የወንጀል ሙከራ ተፈጽሟል። ለሁላችንም መማሪያ ይሆን ዘንድ የታሪኩ ዝርዝር እና ሁላችንም ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡ ነገሮች እንደሚከተለው ቀርበዋል። ድርጊቱ እንዴት ተፈጸመ? ግለሰቡ በኢንስታግራም (Instagram) ከአንዲት ሴት ልጅ ጋር ካወራ በኋላ "ጀሞ አካባቢ ነኝ፣ እስቲ እንገናኝ" ይላታል። እሷም ለጥንቃቄ በማሰብ ብቻዋን ከመሄድ ይልቅ ከሴት ጓደኛዋ ጋር በመሆን ልታገኘው ትሄዳለች። ልክ እንደተገናኙ ግን ግለሰቦቹ መኪና ይዘው በመጠበቅ ሁለቱንም ሴቶች በኃይል መኪና ውስጥ አስገብተው ለማገት ይሞክራሉ። መኪናውን ሳያንቀሳቅሱት እዚያው ባለበት ቦታ ላይ ሆነው ወደ ውስጥ ሊያስገቧቸው ሲታገሉ የአንደኛዋን ስልክ ቀምተው "ውረጂ" በማለት ከመኪናው ላይ ሊወረውሯት ሲሞክሩ፣ እህታችን በከፍተኛ ድፍረትና ድንጋጤ ውስጥ ሆና "ሌባ! ሌባ!" በማለት በጩኸት አካባቢውን ታናውጣለች። የአካባቢው ህብረተሰብ የድረሱልኝ ጩኸት በሰማ ጊዜ በፈጠረው ፈጣን ርብርብ እህቶቻችንን ከከፋ አደጋ የታደጋቸው ሲሆን፣ ወንጀለኞቹንም እጅ ከፍንጅ በመያዝ በአሁኑ ሰዓት በጀሞ መርያም ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ ይገኛል። ለደራሹ የጀሞ ህብረተሰብ ትልቅ ክብርና ምስጋና ይገባል! ከዚህ ክስተት ሁላችንም ምን እንማራለን? ዋናው እና ትልቁ መማሪያ ማንም ሰው በማህበራዊ ሚዲያ ስለተዋወቀው ብቻ ሰውን በቀላሉ ማመን እንደሌለበት ነው። በሶሻል ሚዲያ የምናየው ሰው ትክክለኛ ማንነቱን ላይገልጽ ስለሚችል ወንጀለኞች ሰዎችን ለማጥመድ የውሸት አካውንቶችን በስፋት ይጠቀማሉ። በዚህ አደጋ ላይ እንዳየነው ጓደኛ መያዝም ብቻውን ዋስትና አይሆንም፤ ምክንያቱም ወንጀለኞቹ ሁለቱንም በአንዴ ለማገት ሞክረዋል። ስለዚህ ሙሉ በሙሉ ማንነቱ ካልታወቀ ሰው ጋር በአካል መገናኘት በፍጹም አይመከርም። የግድ መገናኘት ካስፈለገ እንኳን ሰፊ ህዝብ ያለበት፣ ግልጽ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ቦታ መሆን አለበት እንጂ ወደ መኪና አካባቢ መጠጋትም ሆነ መግባት ፍጹም የተከለከለ ነው። እባካችሁ ይሄ መረጃ ለብዙ እህቶቻችን፣ ወንድሞቻችን እና ለወላጆች ትልቅ ማስጠንቀቂያ እንዲሆን ሼር (Share) በማድረግ ለሌሎች አጋሩ። ዛሬ የደረሰውን ሰምተን ካልተጠነቀቅን ነገ በኛ ወይም በቤተሰባችን ላይ ሊደርስ ይችላል! #የደህንነት_መልዕክት #ጀሞ #አዲስ_አበባ #ጥንቃቄ

🏗️ ዋቤ ሸበሌ ሆቴል አዲስ ገጽታ ለመልበስ በእድሳት ላይ! ✨ 🏢 በአዲስ አበባ ከታዋቂ ሆቴሎች አንዱ የሆነው ዋቤ ሸበሌ ሆቴል በአሁኑ ጊዜ ሰፊ የእድሳት ሥራ እየተካሄደበት ይገኛል። 🚧🏗️ �
🏗️ ዋቤ ሸበሌ ሆቴል አዲስ ገጽታ ለመልበስ በእድሳት ላይ! ✨ 🏢 በአዲስ አበባ ከታዋቂ ሆቴሎች አንዱ የሆነው ዋቤ ሸበሌ ሆቴል በአሁኑ ጊዜ ሰፊ የእድሳት ሥራ እየተካሄደበት ይገኛል። 🚧🏗️ 🌍 ሆቴሉ በቅርቡ በMIDROC Investment Group መግዛቱ ተነግሯል፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ለሚካሄደው COP32 ዓለም አቀፍ ጉባኤ እንግዶችን በተሻለ ደረጃ ለመቀበል እየተዘጋጀ መሆኑ ይጠበቃል። 🌿♻️ ✨ ይህ እድሳት የሆቴሉን ዘመናዊነት፣ የእንግዳ አገልግሎት ጥራት እና የአዲስ አበባን የቱሪዝም ገጽታ የበለጠ ለማሳደግ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። 🇪🇹🌆 📸 ከድሮው ወደ አዲሱ… ዋቤ ሸበሌ ሆቴል በአዲስ ምዕራፍ ላይ! 🚀🏨

የቤት ኪራይ ጭማሪ " የ11.5% ጭማሪ አነስተኛ ይመስላል፤ በዓለምአቀፍ ደረጃ ሲታይ ግን እጅግ ከፍተኛ ጭማሪ ነው የተደረገው " - የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት 👉 " ሞሎች፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሥር ያሉ ሱቆች ቀድመው የገዙ የሚያከራዩበት ዋጋ ለመስማት የሚዘገንን ነው! " የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮ ዛሬ ጠዋት ይፋ ያደረገው የ11.5% የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ " እጅግ ከፍተኛ " ፣ " አብዛኛው ተከራይ ከፍተኛ ጭማሪ ከተደረበትና ከተፈናቀለ በኋላ ይፋ የተደረገ " በመሆኑ የዘገዬ ውሳኔ መሆኑን የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ለቲክቫህ ኢትዮጵያን ገለጸ። የድርጅቱ መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ቁምላቸው አበበ በሰጡን ቃል፣ " 11.5% የሚለው ጭማሪ ከኛ ሀገር የዋጋ ግሽበት አንፃር ተመጣጣኝ ቢሆንም ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲታይ ከፍተኛ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። " በሌሎች ሀገራት የቤት ኪራይ ጭማሪ የሚደረገው ቤቱን ለማስጠገን የሚያስፈልግ ወጭ ታሳቢ ተደርጎ ከነጠላ አሀዝ ያላለፈ ጭማሪ ነው " ያሉት አቶ ቁምላቸው፣ " የኛ 11.5% ጭማሪ አነስተኛ ይመስላል፤ በዓለምአቀፍ ደረጃ ሲታይ ግን እጅግ ከፍተኛ ጭማሪ ነው የተደረገው " ሲሉ ገልጸዋል። " ለዛውም ለቤቶቹ ፦ - ጥገና ለማድረግ፣ - ቀለም ለመቀባት፣ - ቤት ውስጥ ያሉ ነገሮችን ለማስተካከል ጭምር ነው ? ጭማሪ የተደረገው የሚለው ሳይታሰብ ለዋጋ ግሽበት ብቻ የተደረገ ጭማሪ ነው " ብለውታል። የከተማዋ ቤቶች ልማት አስተዳደር ደግሞ፣ ጭማሪው " በጥናት የተደገፈ ፣ የነዋሪውን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ፣ አከራዮች ወቅታዊውን የኢኮኖሚ ሁኔታ ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ " የሚያስችል ብሎታል። የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በሌላ በኩል፥ " የቢሮው ውሳኔ እንደ መነሻ ይበል የሚያሰኝ ቢሆንም፣ ማስተካከያው ይፋ መደረግ የነበረበት በግንቦትና ሚያዚያ ወር ነበር፤ በጣም የዘገየ ነው " ብሏል። " አብዛኛው ተከራይ ከኪራይ ከተፈናቀለ፣ ከፍተኛ የኪራይ ጭማሪ ከተደረገበት በኋላ ነው ውሳኔው ይፋ የተደረገው " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። ተከራዮች በበኩላቸው፣ የኪራይ ጭማሪው 11.5% ሆኖ ከመወሰኑ በፊት ፦ • " ቤቴን ላድስ ነው" • " ቤተሰብ ሊገባበት ነው " በሚል ሰበብ የተጋነነ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ቅሬታ እያቀረቡ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለዚህ ምን አይነት መፍትሄ ያስፈልጋል ? ሲል ድርጅቱን ጠይቋል። የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቁምላቸው አበበ፣ " የዚህ መመሪያ አንዱ ፈታኝ ነገር አፈጻጸሙ እንዴት ይሆናል ? እግር በእግር ተከታትሎ ማን ያስፈጽመዋል ? " የሚለው መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ በፊት ቤቱ ተከራይቶበት የነበረው ዋጋና አሁን ስንት እንደሚሆን ስለሚታወቅ የጭማሪው አፈጻጸም ስርዓታዊ እንዲሆን አሳስበዋል። " ዛሬ ይፋ የሆነው ውሳኔ፣ እንዴት ይፈጸማል ? ማስፈጸሚያ ስልቱ ምንድን ነው ? የሚለው ግልጽ አይደለም " ብለው በጥናቱ ድርጅታቸው እንዳልተሳተፈ አመልክተዋል። " እንዲህ አይነት ጥናቶች ሲደረጉ እንደ እኛ አይነት የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶችን፣ ተከራዩን፣ አከራዩን በግልጽ ማወያየት ይገባል " ብለዋል። ጉዳዩ በአከራዮችና ተከራዮች መካከል ጭቅጭቅ እንዳያስከትል አፈጻጸሙ ለወረዳ ብቻ ሳይተው የበላይ የመንግስት አካል መከታተል አለበት ባይ ናቸው። ከ50 እስከ 100% ኪራይ ጭማሪ እንደተደረገ፣ በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ፦ ° ባለአንድ መኝታ ቤት ከ9፣ 10 ሺሕ ተነስቶ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደደረሰ፤ ° 15፣ 16 ሺሕ ብር ሲከራይ የነበረው ባለሁለት መኝታ ቤት 28፣ 30 ሺሕ መከራየትና መጠራት እንደተጀመረ ከዚህ ቀደም ማሳወቃቸውንም አስታውሰዋል። " አሁን የወጣው ውሳኔ ቀድሞ ባስቸኳይ ይፋ እንዲደረግ፣ እርምጃ እንዲወሰድ አሳስበን ነበር " ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ " ያን ካሳሰብን በኋላ ዛሬ ይፋ የሆነው ውሳኔ የዘገዬ ነው " ሲሉም ተችተዋል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ፣ " ዋጋ ጭማሪው እና የውል እድሳቱ መነሻ የሚሆነው ከዚህ ቀደም በነበረው ውል ላይ የተቀመጠው የኪራይ ዋጋ ብቻ ነው " ሲል አስታውቋል። የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በሌላ በኩል በሰጠን ገለጻ፣ በቤት ኪራይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የመንግስት አገልግሎቶች፣ የንግድ ዘርፎች ላይ እንዲሁ ተመሳሳይ የዋጋ ጣሪያ የትርፍ ህዳግ ሊወሰን ይገባል ሲል በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስቧል። የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ስለአጠቃላይ ችግሩና መፍትሄው አክለው ምን አሉ ? " ለቤት ኪራይ መወደድ ትልቅ ጫና የፈጠረው በኮሪደር ልማቱ በርካታ ቤቶች ፈርሰው በቂ ተጨማሪ ቤት ባለመገንባቱ በቤት ኪራይ ላይ የመጣው ጫና ነው። ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት፤ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት፤ የኑሮ ውድነት አለ። መንግስት በተለይ ለደመወዝተኛው የዋጋ ግሽበቱን ታሳቢ ያደረገ የደመወዝ ጭማሪ ሊያደርግ ይገባል። ላለው የዋጋ ግሽበት አንዱ ምክንያት የመኖሪያ ቤት እጥረት ነው። እጥረቱ በዘላቂነት ሊቀረፍ የሚችለው በተለያዩ አማራጮች መኖሪያ ቤቶችን በመገንባት ነው። ሌላው ፥ በቤት ኪራይ ከፍተኛ ጭማሪ የሚያደርገው ህገወጥም፣ ህጋዊም ደላላ ነው። ከቤት ባለቤት ደውሎ 'ይህን ያህል ላከራይልህ' በማለት። ዘላቂው መፍትሄ በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን ደላላ በማስወጣት አከራዩ እና ተከራዩ የሚገናኝበትን የቴክኖሎጂ መተግበሪያ መዘርጋት ነው።  በተያያዘ፥ ከፍተኛ የቤት ግንባታ ማድረግ፤ የሊዝ ዋጋ መቀነስ ይገባል። የኛ ሀገር ሊዝ እነ ኒዮርክ፣ ለንደን ያስከፍሉታል ከሚባለው አያንስም በሚል ነው የሚተቸው። ስለዚህ በካሬ ሜትር የሊዝ ዋጋ መቀነስና የመሬት አቅርቦቱን ሌሎች አማራጮችን ፈልጎ መፍትሄ ማማጣት ያስፈልጋል። ያለው ችግር የመኖሪያ ቤት ብቻ አይደለም። የንግድ ቤቶችም በከፍተኛ ዋጋ ነው የሚከራዩት። በከፍተኛ ዋጋ የተከራየ ነጋዴ ባለሱቅ ያንን ዋጋ የሚጭነው ሸማቹ ላይ ነው። ሞሎች፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሥር ያሉ ሱቆችን ቀድመው የገዙ ሰዎች የሚያከራዩበት ዋጋ ለመስማት የሚዘገንን ነው፤ ይሄ መስተካከል አለበት። ለንግድ የኪራይ ቤቶችም ታሪፍና የዋጋ ጣሪያ ሊቀመጥ ይገባል " ብለዋል። በሌላ በኩል ፥ " በአከራዮች ላይ በጣም ስለተጋነነ እንጅ አንዳንድ አከራዮች ደግሞ ልጆች የሚያስተምሩት ባለአንድ መኝታ ቤት ካላቸው ያን አከራይተው፣ ከከተማ ወጣ ያለ ቤት ተከራይተው ነው። የኑሮ ውድነቱ በአከራዩም በተከራዩም ስለሆነ ይህን ችግር ለመፍታት አስታራቂ መፍትሄ ያሻል " ሲሉ አስገንዝበዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም