ar
Feedback
Ethiopian Business Network

Ethiopian Business Network

الذهاب إلى القناة على Telegram

የኢትዮጵያ ብቸኛ የስራ ፈጠራ መድረክ! ማንኛውንም ፕሮጀክት፣ ሃሳብ ለህዝብ በማድረስ አዳዲስ ድርጅቶችን ለማቋቋም የነፃ እገዛ እናደርጋለን! ያነጋግሩን!

إظهار المزيد
4 541
المشتركون
+124 ساعات
+57 أيام
-2230 أيام
أرشيف المشاركات
ለ10 በጎች የ90 ቀን (3 ወራት) ማደለብ ፕሮጀክት የቀረቡትን መረጃዎች መነሻ በማድረግ የተሟላ የፋይናንስ እና የቴክኒክ ትንተና ከዚህ በታች ተዘጋጅቷል። በጎቹ በቀን በአማካይ 700 ግራም የተመጣጠነ መኖ (Concentrate feed) እና የደረቅ ሳር ድብልቅ ያስፈልጋቸዋል ተብሎ ታስቧል። 1. የወጪ ትንተና (Investment & Running Costs) የወጪ ዓይነቶቹ በቋሚ ኢንቨስትመንት (አንድ ጊዜ የሚወጣ) እና በስራ ማስኬጃ (ለየዙሩ የሚወጣ) ተለይተው ቀርበዋል። ሀ. ቋሚ ኢንቨስትመንት (Fixed Capital) ✅የቤት መስሪያ፡ 40,000 ብር (ለረጅም ጊዜ የሚያገለግል) ለ. የስራ ማስኬጃ ወጪ (Operating Cost ለ 1 ዙር) ✅የበጎች መግዢያ፡ 10 በግ × 14,000 ብር = 140,000 ብር ✅የመድኃኒትና ክትባት፡ 20,000 ብር (ለ 10 በግ 20,000 ብር ከፍተኛ ስለሆነ፣ ሙሉ የሕክምና እና የክሊኒክ ወጪን ያጠቃልላል) የመኖ ወጪ ስሌት፡ ⚫️1 በግ በቀን = 0.7 ኪሎግራም መኖ ⚫️10 በግ በቀን = 7 ኪሎግራም ለ 90 ቀናት ጠቅላላ መኖ = 7 ኪሎግራም×90 ቀን=630 ኪሎግራም (6.3 ኩንታል) ጠቅላላ የመኖ ዋጋ = 6.3 ኩንታል × 2,500 ብር = 15,750 ብር 2. ጠቅላላ የካፒታል ፍላጎት (Total Budget) የወጪ ዝርዝር--- መጠን(ብር)--መቶኛ (%) ✅የቤት መስሪያ (ቋሚ)40,000------18.5% ✅የበጎች መግዢያ140,000------------64.9%✅የመኖ ወጪ (6.3 ኩንታል)15,750----7.3% ✅የመድኃኒትና ክትባት-20,000--9.3% ጠቅላላ ድምር215,750100% ማሳሰቢያ፡ በመጀመሪያው ዙር ጠቅላላ= 215,750 ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፣ ከሁለተኛው ዙር ጀምሮ ግን የቤት መስሪያ ወጪ (40,000 ብር) ስለማይኖር የስራ ማስኬጃ ወጪው ወደ 175,750 ብር ይወርዳል። 3. የትርፍ እና ኪሳራ ግምት (Feasibility & Profitability) በጎቹ በ90 ቀን ውስጥ ጥሩ ክብደት (በቀን ከ150–200 ግራም) እንዲጨምሩ ከተደረገ፣ በገበያ ወቅት አንዱ በግ በአማካይ 26,000 ብር ይሸጣል ተብሎ ቢገመት፡ ጠቅላላ የሽያጭ ገቢ (Revenue)፦ 10 በግ × 26,000 ብር = 260,000 ብር የመጀመሪያው ዙር የተጣራ ትርፍ (Net Profit)፦ የሽያጭ ገቢ−ጠቅላላ ወጪ=260,000−215,750=44,250 ብር ከሁለተኛው ዙር ጀምሮ የሚገኝ ትርፍ፦ የሽያጭ ገቢ−የስራ ማስኬጃ ወጪ=260,000−175,750=84,250 ብር 4. ስኬታማ ለመሆን ሊተገበሩ የሚገቡ ነጥቦች የበግ አመራረጥ፡ ለመደለብ የሚገቡት በጎች ዕድሜያቸው ከ1–1.5 ዓመት የሆኑ፣ ሰፊ ፍሬምና አጥንት ያላቸው (በተለይ የአገር ውስጥ ምርጥ ዝርያዎች ለምሳሌ ቦረና፣ አፋር ወይም አርሲ-ባሌ) መሆን አለባቸው። ✅የጤና አጠባበቅ፡ በጎቹ ወደ ማደለቢያው ከመግባታቸው በፊት የውስጥና የውጭ ጥገኛ ተውሳክ (Endo and Ectoparasite) መድኃኒት መውሰድና ለኩፍኝ (PPR) እና ለፎረፎር (Sheep Pox) መከተብ አለባቸው። ✅የአመጋገብ ስልት (Feeding Routine)፡ የመጀመሪያዎቹን 1–2 ሳምንታት መኖውን መልመጃ (Adaptation period) በማድረግ ቀስ እያሉ መጨመር ያስፈልጋል። ንጹህ ውሃ ሁልጊዜ ማግኘት አለባቸው። ምንጭ Accubreed

33 ሚሊየን ብር ዘራፊዎች በተኩስ ልውውጥ ተያዙ! *** ወንጀሉ የተፈፀመው ካዲስኮ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ኖክ ግምታቸው 33 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ 200 በርሜል የሞተር ዘይት ለዊ ቢዩልድ ኮይሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክት የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡት ከአንድ ግለሰብ ጋር ከስምምነት ላይ ይደርሳል። በስምምነቱ መሰረት አሽከርካሪው መንጃ ፍቃድ እና ሊብሬ አቅርቦ እንዲሁም የተሽከርካሪውን ሰሌዳ አስመዝግቦ የሞተር ዘይቱ ቢጫንም ጭነቱ ኮይሻ እንዳልደረሰ ኖክ ያረጋግጣል። ጉዳዩንም ለአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ሪፖርት ያደርጋል። ግለሠቡ ያቀረበው ሊብሬ እና መንጃ ፈቃድ ሀሰተኛ እንደሆነ እንዲሁም ጠፍቷል ተብሎ የተመዘገበ የሌላ ተሽከርካሪ ሰሌዳን አሽከርካሪው መጠቀሙን ፖሊስ ባደረገው ምርመራ አረጋግጧል። አሽከርካሪውን ከኖክ ጋር ያገናኘውን ግለሰብ እና ከወንጀል ድርጊቱ ጋር ተሳትፎ ያላቸውን አብዱልሠላም ወራኪ፣ አብዱራህማን ሀሰን፣ መሀመድ ቢላል፣ ደረጄ በቀለ፣ አብዱልሀፊዝ አብዱልሽኩር፣ ነጃ ካሚል የተባሉት ተጠርጣሪዎችን ፓሊስ በቁጥጥር ስር በማዋል ንብረቱን ማስመለስ ችሏል። ኤግዚቢቶቹ በሸገር ከተማ አሸዋ ሜዳ እና በቢሾፍቱ ከተማ እንደተገኙ ዋና ፖሊስ መምሪያው ገልጿል። ከወንጀለኞቹ ውስጥ ነጃ ካሚል የተባለው ከዚህ ቀደም በግድያና በዘረፋ ወንጀሎች ተጠርጥሮ በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በወንጀል ምርመራ ምክትል ዋና ጠቅላይ መምሪያ ሲፈለግ እንደነበር ታውቋል። ግለሰቡ በፖሊስ ላለመያዝ ሲሞክር ያሽከረክር በነበረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 17262 አማ መኪና ለማምለጥ ሲሞክር ጎማው በጥይት ተመቶ ተይዟል። ተጠርጣሪው በወቅቱ መረጃ ለማጥፋት ሲል በእጁ ይዞት የነበረውን ውድ ዋጋ ያለውን ሞባይል ስልክ መስበሩ አደገኛ ወንጀል ፈጻሚ መሆኑን እንደሚያሳይ ፖሊስ አረጋግጧል። ፖሊስ ንብረቱን በህግ አግባብ ለናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ አክሲዮን ማህበር አስረክቧል። ዘገባ፦ ም/ሳጅን ፍፁም በቀለ

photo content
+3

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከ40 ዓመታት በኋላ የነዳጅ ምርት ማጓጓዝ ጀመረ ​የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት (ኢባትሎ) ሀገሪቱ ከውጭ የምታስገባውን የነዳጅ
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከ40 ዓመታት በኋላ የነዳጅ ምርት ማጓጓዝ ጀመረ ​የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት (ኢባትሎ) ሀገሪቱ ከውጭ የምታስገባውን የነዳጅ ምርት የማጓጓዝ ሥራ ከ40 ዓመታት በኋላ በድጋሚ መጀመሩን አስታወቀ። ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከናይጄሪያ የተገዛን የኤቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በቻርተር መርከቦች ማጓጓዝ ችሏል። ​በሆርሙዝ ባህር ሰርጥ አካባቢ በተቀሰቀሰው ግጭት ምክንያት በተፈጠረው የትራንስፖርት መስተጓጎል እና በሀገር ውስጥ እየጨመረ የመጣውን የነዳጅ ፍላጎት ለማሟላት መንግሥት የነዳጅ ግዢ ምንጮቹን እያሰፋ ይገኛል። በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያለበትን ከፍተኛ የአውሮፕላን ነዳጅ ፍላጎት ለማሟላትና አማራጭ መስመሮችን ለመጠቀም ከናይጄሪያው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግዢ ተፈጽሟል። ​ኢባትሎ እንዳስታወቀው ተቋሙ መንግሥት በፈጠረው ምቹ ሁኔታ በመጠቀም 120 ሺህ ሜትሪክ ቶን የአውሮፕላን እና የናፍጣ ነዳጅ በሦስት ተከታታይ ጉዞዎች ወደ ጅቡቲው ሆራይዘን ተርሚናል ማጓጓዝ ችሏል። ይህ ስኬት ነዳጅ የማጓጓዝ ልምድ ላልነበረውና "አቅም የለውም" ተብሎ ለሚታሰበው የሎጂስቲክስ ተቋም ትልቅ የሥራ ክንውን መሆኑን አስምሮበታል።

የሚከራይ ወይም የሚሸጥ ቤት አለዎት? ዘመናዊውን መንገድ ይጠቀሙ! 🚀 የአዲስ አበባ ህጋዊ ደላሎች ብቻ መገኛ! በአሮጌው አሰራር ጊዜዎንና ገንዘብዎን አያባክኑ። ፎቶ ያንሱ 📸፣ ዋጋ ያስገቡ 💰፣ ዛሬውኑ በነፃ ፖስት ያድርጉ! ማስታወቂያዎ ወዲያውኑ ለብዙ ሺዎች ይደርሳል፤ 👇 አሁኑኑ ፓስት ያድርጉ ወይም ይጠይቁ! https://t.me/Addislembosa

#INSA ከ14,000 በላይ አመልካቾች የተመዘገቡበት የኢመደአ 2018 ሰመር ካምፕ ወደ ሚቀጥለው ቻሌንጅ/ፈተና ያለፉ ተወዳዳሪዎች ውጤት ይፋ ሆነ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ
#INSA ከ14,000 በላይ አመልካቾች የተመዘገቡበት የኢመደአ 2018 ሰመር ካምፕ ወደ ሚቀጥለው ቻሌንጅ/ፈተና ያለፉ ተወዳዳሪዎች ውጤት ይፋ ሆነ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) የ2018 ሰመር ካምፕን ለማድረግ በዘርፉ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣት እና ታዳጊዎች ምዝገባ ያደረገ ሲሆን በዚህም ከ14,000 በላይ በሀገራችን እና ከሀገር ውጪ የሚገኙ ተመዝጋቢዎች ተመዝግበዋል። ከተመዘገቡት ውስጥ የመጀመሪያ ዙርን ምልመላ ያለፉት የታወቁ ሲሆን ሁለተኛ ዙር ቻሌንጅ በስድስት የፈተና ጣቢያዎች አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ከሰኔ 17 - 19 እንዲሁም አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፣ ሀረማያ ዩኒቨርስቲ ፣ ጅማ ዩኒቨርስቲ ፣ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሰኔ 13 እና 14  የሚስጥ ይሆናል። ተወዳዳሪዎች ማለፋቸውን በታለንት ምዕከሉ ፖርታል https://ctc.insa.gov.et/ ላይ ወይም ቴሌግራም ቻናል ላይ @insactc በመግባት ማለፍ እና አለማለፋቸውን ማረጋገጥ ይችላሉ። 5ኛው ዙር ሰመር ካምፕ በኢመደአ ተለንት ማዕከል እና በሌሎች 6 ዩኒቨርስቲዎች የሚሰጥ ይሆናል። ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ/ም

መደበኛ በረራ ተጀመረ‼️ አየር መንገዱ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ መደበኛ በረራ ይጀምራል‼️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ደብረማርቆስ ከተማ የቅድ
መደበኛ በረራ ተጀመረ‼️ አየር መንገዱ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ መደበኛ በረራ ይጀምራል‼️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ደብረማርቆስ ከተማ የቅድመ ምረቃ በረራዎችን እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ መንገደኞች የበረራ ቲኬቶችን በሁሉም የቲኬት መሸጫ ቢሮዎች ማግኘት እንደሚችሉ የአየር መንገዱ መረጃ አመላክቷል።

"ኪራይ ዝም ብሎ አይጨመርም፤ ዋጋ መወሰን የሚችለው መንግሥት ብቻ ነው" መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ እንደገለጹት፣ የአከራይና ተከራይ ግንኙነትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን በተጀመረው ዲጂታል ምዝገባ እስካሁን 500 ሺህ የሚጠጉ ቤቶች ወደ ሲስተሙ ገብተዋል። ይህ አሰራር ያለ አግባብ የሚደረግን የዋጋ ጭማሪ ሙሉ በሙሉ ያስቀራል ሲል ለአዲስ ቲቪ ተናግረዋል። 📌 አከራዮች በራሳቸው ዋጋ መጨመር አይችሉም። መንግሥት የገበያ ጥናት ካደረገ በኋላ በየዓመቱ ሰኔ 30 ላይ በሚያወጣው ይፋዊ መግለጫ መሠረት የጭማሪውን ፐርሰንት ይወስናል። 📌 እንግልትን ለማስቀረት የውል ማደስ ሥራውን በኢንተርኔት (ኦንላይን) ለማከናወን ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ነው። ዋጋ ሳይጨመር መቀጠል የሚፈልጉ በኦንላይን ማደስ ይችላሉ። 📌የተከራዮች መብት፦የውል ጊዜ በማብቃቱ ብቻ አከራዮች ተከራይን አስወጥተው ሌላ ሰው ቢያስገቡ እንኳ ዋጋ ጨምረው ማከራየት አይችሉም። ተከራዮች ያለ ሕጋዊ መነሻ ክፍያ መጨመር የለባቸውም።በአጠቃላይ በየሁለት ዓመቱ የኪራይ ውልን በሕጋዊ መንገድ ማደስ ግዴታ መሆኑ ተገልጿል። video 👇Like + Follow👇

ፌስቡክ በአሁኑ ሰዓት ተቋርጧል‼ ችግሩ ተጠቃሚዎች ከፌስቡክ እና ከሜሴንጀር (Messenger) ላይ በራሱ ጊዜ "Log out" እያደረጋቸው እንደሆነና ተመልሰው ለመግባት ሲሞክሩ "unexpected e
ፌስቡክ በአሁኑ ሰዓት ተቋርጧል‼ ችግሩ ተጠቃሚዎች ከፌስቡክ እና ከሜሴንጀር (Messenger) ላይ በራሱ ጊዜ "Log out" እያደረጋቸው እንደሆነና ተመልሰው ለመግባት ሲሞክሩ "unexpected error" (ያልተጠበቀ ስህተት) የሚል መልዕክት እያሳያቸው እንደሆነ ሪፖርት እያደረጉ ነው። በአፕሊኬሽኑም ሆነ በዌብሳይት ለመጠቀም አስቸጋሪ ሆኗል። 📌ችግሩ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከዛሬ ሰኔ 5/2018  ከቀኑ 9:30 (በአውሮፓውያን 2:30 PM) አካባቢ ጀምሮ ነው በስፋት የታየው።   ችግሩ በአለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተ ሲሆን፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በየደቂቃው መግባት አለመቻላቸውን ሪፖርት እያደረጉ ይገኛሉ። ከፌስቡክ በተጨማሪ አንዳንድ የኢንስታግራም (Instagram) ክፍሎች ላይም መቆራረጥ እየታየ ነው። ችግሩ ከፌስቡክ (Meta) ማዕከላዊ ሰርቨር ጋር የተያያዘ ስለሆነ ከእርስዎ ስልክ ወይም አካውንት ጋር የተያያዘ ችግር አይደለም። ሜታ (Meta) ችግሩን አስተካክሎ እስኪጨርስ ድረስ የተወሰነ ጊዜ ሊወስድ ስለሚችል በትዕግስት መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ተዘግቧል።

photo content

በአሁን ሰአት 1000 ዶሮዎች ያለው ሰው እና 850 እንቁላል እያገኘ ያለ ሰው ግምታዊ የሚያገኘው ወርሀዊ ትርፍ ወርሀዊ ወጪ ኢትዮ መኖ በወር 36 ኩንታል × በ7300 ብር = 262,800 ብር ወርሀ
በአሁን ሰአት 1000 ዶሮዎች ያለው ሰው እና 850 እንቁላል እያገኘ ያለ ሰው ግምታዊ የሚያገኘው ወርሀዊ ትርፍ ወርሀዊ ወጪ ኢትዮ መኖ በወር 36 ኩንታል × በ7300 ብር = 262,800 ብር ወርሀዊ ቤት ኪራይ 20,000 ብር ወርሀዊ ሰራተኛ 10,000 ብር ወርሀዊ መብራት እና ውሀ 3,000 ብር ወርሀዊ መድሀኒት እና ቪታሚን 3000 ብር ጠቅላላ ወርሀዊ ወጪ፦ 298,800 ብር ወርሀዊ ሽያጭ 850 እንቁላል × 30 ቀን = 25,500 እንቁላል 25,500 እንቁላል × 20 ብር = 510,000 ብር ትርፍ ወርሀዊ ሽያጭ - ወርሀዊ ወጪ = ወርሀዊ ትርፍ 510,000 ብር - 298,800 ብር = 211, 200 ብር ዶሮዎቻችሁ 80%75% ከጣሉ በዚህ መልኩ ሂሳባችሁን መስራት ትችላላችሁ። ዋጋውንም እንደ አካባቢያችሁ መስራት ትችላላችሁ።

2.3 ትሪሊየን ብር በጀት ቀረበ‼ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ለቀረበው የፌዴራል መንግሥት ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምፅ አፅድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መራ።
+2
2.3 ትሪሊየን ብር በጀት ቀረበ‼ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ለቀረበው የፌዴራል መንግሥት ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምፅ አፅድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መራ። ለመደበኛ፣ ለካፒታል፣ ለክልሎች ድጋፍና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የቀረበው የዚህ በጀት አጠቃላይ መጠን ከ2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን ብር በላይ (2,339,268,126,738) ነው። በጀቱ የአሥር ዓመቱን መሪ የልማት ዕቅድና የማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፍን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። WasuMohammed

መኪና የሚወረስበት አዋጅ ዛሬ ይፀድቃል‼ ​የኮንትሮባንድ እቃ የጫኑ ተሽከርካሪዎች በቀጥታ ተወርሰው ለመንግሥት ገቢ እንዲደረጉ የሚያዘው አዲስ የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ፣ ዛሬ ሰኔ 2 በሕዝብ ተወ
+2
መኪና የሚወረስበት አዋጅ ዛሬ ይፀድቃል‼ ​የኮንትሮባንድ እቃ የጫኑ ተሽከርካሪዎች በቀጥታ ተወርሰው ለመንግሥት ገቢ እንዲደረጉ የሚያዘው አዲስ የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ፣ ዛሬ ሰኔ 2 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ​ቀደም ሲል የነበረው የ100 ሺህ ብር ቅጣት ወንጀሉን ባለማስቆሙ እና ኮንትሮባንዲስቶች ልዩ መደበቂያና የጥይት መከላከያ የገጠሙላቸውን የረቀቁ ተሽከርካሪዎችን መጠቀም በመጀመራቸው አዲሱ ጥብቅ ማሻሻያ አስገዳጅ ሆኗል። በዚህም መሠረት መደበቂያ የተገጠመለት ወይም ከገደብ በላይ እቃ የጫነ ማንኛውም ተሽከርካሪ የዕቃው ዋጋ ከግምት ውስጥ ሳይገባ በቀጥታ ይወረሳል። ​ይሁን እንጂ አዋጁ ተሽከርካሪው ከመወረሱ በፊት ባለቤቱ ቀርቦ ማስረጃ በማቅረብ ራሱን የመከላከል መብት እንዳለው ይደነግጋል። ምክር ቤቱ ነገ በምታካሂደው 24ኛ መደበኛ ስብሰባ ረቂቅ አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።ፎቶ:-ፋይል

|| " ሰራተኞች እንፈልጋለን " - ጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ በከፍተኛ የሰው ኃይል እጥረት ምክንያት ከአቅሙ በታች እያመረተ መሆኑን የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ባይ
|| " ሰራተኞች እንፈልጋለን " - ጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ በከፍተኛ የሰው ኃይል እጥረት ምክንያት ከአቅሙ በታች እያመረተ መሆኑን የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ባይነሳኝ ዘሪሁን አስታውቀዋል። ተቋሙ 2 ሺህ 310 ቋሚ እና ከ24 ሺህ በላይ ጊዜያዊ ሠራተኞችን የሚፈልግ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ከ5 ሺህ በላይ የቀን ሠራተኞች ከሚያስፈልጉት ውስጥ ማግኘት የቻለው 623 ሰራተኞችን ብቻ ነው። ይህ የሰው ኃይል እጥረት ፋብሪካው በቀን ማምረት ከሚችለው 12 ሺህ ቶን በላይ ስኳር ውስጥ 3 ሺህ 600 ቶን ብቻ እንዲያመርት አድርጎታል። በመሆኑም ሥራ ፈላጊ ወጣቶች ወደ ፋብሪካው በመምጣት የተፈጠረውን የሥራ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል። Sky First

አሻራ መስጠት ሊቀር ነው‼️ ለፓስፖርት በአካል አሻራ መስጠት ሊቀር ነው‼ 📌ዜጎች ፓስፖርታቸውን ቤት ሆነው መጨረስ ይችላሉ ተብሏል። ​የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ተገልጋዮች ለአሻራ በአካል መገኘት ሳያስፈልጋቸው የፓስፖርት አገልግሎትን በኦንላይን ብቻ ማግኘት የሚችሉበት አዲስ አሰራር እየዘረጋ መሆኑን አስታወቀ። ​የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት እንደገለጹት፣ አዲሱን አሰራር ለመተግበር የፓስፖርት ሲስተሙ ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር እየተቀናጀ ይገኛል። ይህም ዜጎች በፋይዳ ላይ ያለውን መረጃ በቀጥታ በመጠቀም ከቤታቸው ሳይወጡ ፓስፖርታቸውን በእጃቸው እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። ​በተጨማሪም በኦንላይን ምዝገባ ስም የሚፈጸሙ ማጭበርበሮችን ለመከላከል፣ አንድ ሰው ከአንድ ቦታ ሆኖ ከ10 በላይ ሰዎችን መመዝገብ እንዳይችል ጥብቅ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋቱን ተቋሙ አስታውቋል።

Canada is seeking top talent, including: • medical doctors, researchers and senior managers with Canadian work experience • workers with French-language proficiency • health care and social services professionals • tradespersons • educators • professionals in science, technology, engineering and mathematics (STEM) occupations • professionals in transport occupations These categories provide clear pathways to permanent residence for top international talent. Find out how Express Entry category-based rounds of invitations work: https:// bit.ly/4s0UAFi

photo content
+9

#ለመረጃ ጥሬ ገንዘብ ያላቸው ግለሰቦችና ተቋማት ገንዘባቸውን በማዋጣት በጋራ በተቋቋመ ፈንድ አማካኝነት በተለያዩ የትርፍ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ የሚያስችል “የጋራ ኢንቨስትመንት ፈንድ” ረቂቅ መመሪያን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ተዘጋጅቷል ሰነዱን በማንበብ አስተያየት መስጠት ለምትፈልጉ ከላይ ተቀምጧል!