ch
Feedback
OZONE SCHOOL OFFICIAL ®️

OZONE SCHOOL OFFICIAL ®️

前往频道在 Telegram

@ozoneschool ከኦዞን አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ማንኛውንም መረጃ ለማግኘት ቀጥሎ በተጠቀሰው ስልክ ቁጥር☎️ መጠቀም እንደምትችሉ በአክብሮት እንገልፃለን። 📞 0116606078 📞

显示更多
5 605
订阅者
+424 小时
+97
+3230
帖子存档
photo content

photo content

የካርኒቫል ትኬት ክፍያ ማረጋገጫ ውድ ወላጆች/አሳዳጊዎች፣ የካርኒቫሉን ትኬት ክፍያ ከፈጸሙ በኋላ የክፍያውን ስክሪንሾት (Screenshot) ወይም ደረሰኝ (Receipt) ፎቶ በቴሌግራም ወደሚከተለው
የካርኒቫል ትኬት ክፍያ ማረጋገጫ ውድ ወላጆች/አሳዳጊዎች፣ የካርኒቫሉን ትኬት ክፍያ ከፈጸሙ በኋላ የክፍያውን ስክሪንሾት (Screenshot) ወይም ደረሰኝ (Receipt) ፎቶ በቴሌግራም ወደሚከተለው ቁጥር እንዲልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን። 0963216560 የክፍያ ማረጋገጫው ከደረሰን በኋላ ትኬቱን መውሰድ ይችላሉ። ለትብብራችሁ እናመሰግናለን!

photo content

IMPORTANT MESSAGE TO STUDENTS ✅ Be Punctual Prepare your admission card, pencil, eraser, and sharpener the night before. Arrive at the examination venue early and begin your exam calmly and confidently. ✏️ Read Questions Carefully Make sure you fully understand what each question is asking. Pay close attention to key phrases, especially statements such as “Which of the following is NOT correct?” ✅ Answer Easy Questions First If you encounter a difficult question, do not spend too much time on it. First answer the questions you know well, then return to the more challenging ones if time permits. 📝 Mark Your Answers Carefully When filling in your answers on the answer sheet, ensure that you follow the correct question numbers and mark the appropriate answer spaces accurately. 🌟 Review Your Work Before Submission Before submitting your paper, carefully review all your answers to ensure that every question has been answered and that there are no marking errors. ✅ Stay Calm and Confident Before the examination begins, take a deep breath, inhale slowly, and exhale gently. This helps reduce anxiety and improves concentration. 👪 Message to Parents A child's examination performance depends not only on their preparation and study habits but also on the support and emotional stability they receive at home. 🌟 Encourage Your Children Avoid using threatening or discouraging language. Instead, motivate them with positive words and reassurance. 🏆 Be Positive Use encouraging statements such as: “Do your best; we believe in you and are confident in your abilities.” ✍️ Create a Comfortable Environment Provide a peaceful and supportive home environment that is conducive to both study and rest. 🔕 Minimize Distractions Reduce distractions such as loud television or radio noise and avoid unnecessary conflicts that may affect your child's concentration. 🌟 Best Wishes Dear Students, We sincerely wish each and every one of you great success and outstanding results in your examinations. May your hard work and dedication be rewarded. Good luck and best wishes! 🏆✨

IMPORTANT MESSAGE TO STUDENTS ✅ Be Punctual Prepare your admission card, pencil, eraser, and sharpener the night before. Arrive at the examination venue early and begin your exam calmly and confidently. ✏️ Read Questions Carefully Make sure you fully understand what each question is asking. Pay close attention to key phrases, especially statements such as “Which of the following is NOT correct?” ✅ Answer Easy Questions First If you encounter a difficult question, do not spend too much time on it. First answer the questions you know well, then return to the more challenging ones if time permits. 📝 Mark Your Answers Carefully When filling in your answers on the answer sheet, ensure that you follow the correct question numbers and mark the appropriate answer spaces accurately. 🌟 Review Your Work Before Submission Before submitting your paper, carefully review all your answers to ensure that every question has been answered and that there are no marking errors. ✅ Stay Calm and Confident Before the examination begins, take a deep breath, inhale slowly, and exhale gently. This helps reduce anxiety and improves concentration. 👪 Message to Parents A child's examination performance depends not only on their preparation and study habits but also on the support and emotional stability they receive at home. 🌟 Encourage Your Children Avoid using threatening or discouraging language. Instead, motivate them with positive words and reassurance. 🏆 Be Positive Use encouraging statements such as: “Do your best; we believe in you and are confident in your abilities.” ✍️ Create a Comfortable Environment Provide a peaceful and supportive home environment that is conducive to both study and rest. 🔕 Minimize Distractions Reduce distractions such as loud television or radio noise and avoid unnecessary conflicts that may affect your child's concentration. 🌟 Best Wishes Dear Students, We sincerely wish each and every one of you great success and outstanding results in your examinations. May your hard work and dedication be rewarded. Good luck and best wishes! 🏆✨

ወሳኝ መልዕክት ለተማሪዎች በሰዓቱ መገኘት⌚️የመፈተኛ ካርድ፣ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ ማታ አዘጋጁ። በፈተና ቦታ ቀድማችሁ በመድረስ በመረጋጋት ፈተናችሁን ጀምሩ። ✏️ ጥያቄዎችን በጥንቃቄ ማንበብ ጥያቄው ምን እንደሚጠይቅ በሚገባ አረጋግጡ። በተለይ “ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?” የሚሉ ቁልፍ ቃላትን በጥንቃቄ አስተውሉ። ቀላል ጥያቄዎችን በቅድሚያ መሥራት አስቸጋሪ ጥያቄ ሲያጋጠማችሁ ብዙ ጊዜ አታጥፉበት። መጀመሪያ የምታውቋቸውን ጥያቄዎች በፍጥነት መልሱ፤ ከዚያ ጊዜ ሲተርፋችሁ ወደ ቀሩት ተመለሱ። 📝መልሶቻችሁን በጥንቃቄ ማጥቆር በመልስ መስጫ ወረቀቱ (Answer Sheet) ላይ ምርጫዎችን ስታጠቁሩ የጥያቄ ቁጥሮችን እና የማጠቆሪያውን መስመር በትክክል መከተላችሁን አረጋግጡ። 🌟ከማስረከባችሁ በፊት ደግማችሁ መመልከት ሁሉንም ጥያቄዎች በአግባቡ መመለሳችሁን እና ያለ ምንም ስህተት ማጥቆራችሁን እርግጠኛ ለመሆን መልሳችሁን በጥንቃቄ ከልሱ። መረጋጋት እና በራስ መተማመን ፈተናው ከመጀመሩ በፊት ጥልቅ ትንፋሽ (Deep Breath) ወደ ውስጥ አስገቡ፣ ቀስ ብላችሁም ተንፍሱ። ይህ ፍርሃትን አስወግዶ ትኩረትን ያጠናክራል።  👪 መልዕክት ለወላጆች የልጆች የፈተና ውጤት በጥናታቸው ብቻ ሳይሆን በቤት ውስጥ በሚያገኙት ድጋፍና ስነ-ልቦናዊ መረጋጋትም ይወሰናል። ልጆችን አበረታቱ፦ የፍርሃት ወይም የዛቻ ንግግሮችን በፍጹም አስወግዱ። 🏆 አዎንታዊ ሁኑ፦ “የቻልከውን/ሽን ሁሉ አድርግ/ጊ፤ እኛ በአንተ/በአንቺ እንተማመናለን” የሚሉ አበረታች ቃላትን ተጠቀሙ። ✍️ ምቹ ሁኔታን ፍጠሩ፦ ለጥናትና ለእረፍት የሚሆን ሰላማዊ የቤት ውስጥ አካባቢ አመቻቹ። ትኩረት የሚረብሹ ነገሮችን አስወግዱ፦ የተማሪውን ትኩረት የሚበትኑ ከፍተኛ ድምጾችን (ቲቪ/ሬዲዮ) እና አላስፈላጊ ግጭቶችን አስወግዱ። ****  🌟 ውድ ተማሪዎች፣ ለሁላችሁም በፈተናችሁ ስኬትና ከፍተኛ ውጤት ከልብ እንመኛለን! 🏆✨

photo content

ቀን፦ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ለየ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ወላጆች እና አሳዳጊዎች ጉዳዩ፦ ስለ ሚኒስቴር ፈተና ግንዛቤ ማስጨበጫ  (ኦሬንቴሽን) መርሃ ግብር ​ውድ ወላጆች እና አሳዳጊዎች፤ ​የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በፈተና ክፍላቸው ውስጥ የሚካሄድ እና ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽሕፈት ቤት በሚመጡ ባለሙያዎች የሚሰጥ የባለሙያ የግንዛቤ ማስጨበጫ (ኦሬንቴሽን) መርሃ ግብር ላይ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደሚሳተፉ እንገልጻለን። ​ይህ የኦሬንቴሽን መርሃ ግብር በስኬት ይከናወን ዘንድ ተማሪዎች የሚከተሉትን መመሪያዎች መሰረት በማድረግ ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ እንድታደርጉ በትህትና እንጠይቃለን፦ ​1. የትምህርት ቤት መግቢያ ሰዓት እና ትራንስፖርት ​ሰዓት፦ ሁሉም ተማሪዎች ከጥዋቱ  1:00 ሰዓት በፊት ትምህርት ቤት መገኘት አለባቸው። ​የዚህ በፊት የመደበኛ ክ/ጊዜ ሰርቪስ ተጠቃሚዎች፦ በትምህርት ቤቱ ሰርቪስ የሚጠቀሙ ተማሪዎች በመጀመሪያው ዙር አገልግሎት መጠቀም ይኖርባቸዋል። ​በግል የሚመጡ፦ ልጆቻቸውን በራሳቸው ትራንስፖርት የሚያመጡ ወላጆች ተማሪዎቹ በትክክለኛው ሰዓት (ከጥዋቱ 1:00 ሰዓት በፊት) ትምህርት ቤት መድረሳቸውን ማረጋገጥ አለባቸው። 1. ​የመጓጓዣ ሁኔታ፦ ተማሪዎች ከትምህርት ቤት ተነስተው ወደ ፈተናው ማዕከል የሚጓዙት በትምህርት ቤቱ አውቶቡሶች (ሰርቪሶች) አማካኝነት ነው። ​2. ተማሪዎች ይዘዋቸው ሊመጡ የሚገቡ ነገሮች ሀ. ​ምግብ እና መጠጥ፦ ቁርስ , ምሳ  እና በቂ የመጠጥ ውሃ። ለ. ​የጽሕፈት መሣሪያዎች፦ እርሳስ ,መቅረጫ እና ማስታወሻ ደብተር። ሐ. የት/ቤት መታወቂያ እና አድሚሽ ካርድ። ​3. ይዞ መምጣት የተከለከሉ ዕቃዎች ​ተማሪዎች የሚከተሉትን ዕቃዎች ወደ ትምህርት ቤትም ሆነ ወደ ፈተናው ማዕከል ይዞ መምጣት በጥብቅ የተከለከለ ነው፦ ሀ. ​የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎች (ሞባይል ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ላፕቶፖች፣ ስማርት ሰዓቶች እና መሰል ዕቃዎች) ለ. ​የውበት መዋቢያዎች (ኮስሞቲክስ)​ ሐ. ሹል እና ስለታም ነገሮች ወ.ዘ.ተ:: ​4. የደንብ ልብስ እና የግል ንጽህና ሀ. ​ሁሉም ተማሪዎች መደበኛውን የትምህርት ቤት ደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) መልበስ አለባቸው። ለ. ​ተማሪዎች (በተለይም ወንዶች ልጆች) ጸጉራቸውን በአግባቡ የተስተካከለ፣ ንጹህና ስልጡን በሆነ መልኩ ተቆርጠው መምጣት ይኖርባቸዋል። ​5. ወደ ቤት የመመለሻ ሰዓት ​የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሩ ከተጠናቀቀ ተማሪዎች በተለመደው የጉዞ መስመራቸው መሠረት በግምት ከምሽቱ 9:30 ሰዓት ላይ ወደየቤታቸው  በመደበኛው ስርቢስ ይመለሳሉ። የት/ቤቱ አስተዳዳር

ቀን፦ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ለየ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ወላጆች እና አሳዳጊዎች ጉዳዩ፦ ስለ ሚኒስቴር ፈተና ግንዛቤ ማስጨበጫ  (ኦሬንቴሽን) መርሃ ግብር ​ውድ ወላጆች እና አሳዳጊዎች፤ ​የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በፈተና ክፍላቸው ውስጥ የሚካሄድ እና ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽሕፈት ቤት በሚመጡ ባለሙያዎች የሚሰጥ የባለሙያ የግንዛቤ ማስጨበጫ (ኦሬንቴሽን) መርሃ ግብር ላይ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደሚሳተፉ እንገልጻለን። ​ይህ የኦሬንቴሽን መርሃ ግብር በስኬት ይከናወን ዘንድ ተማሪዎች የሚከተሉትን መመሪያዎች መሰረት በማድረግ ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ እንድታደርጉ በትህትና እንጠይቃለን፦ ​1. የትምህርት ቤት መግቢያ ሰዓት እና ትራንስፖርት ​ሰዓት፦ ሁሉም ተማሪዎች ከጥዋቱ  1:00 ሰዓት በፊት ትምህርት ቤት መገኘት አለባቸው። ​የዚህ በፊት የመደበኛ ክ/ጊዜ ሰርቪስ ተጠቃሚዎች፦ በትምህርት ቤቱ ሰርቪስ የሚጠቀሙ ተማሪዎች በመጀመሪያው ዙር አገልግሎት መጠቀም ይኖርባቸዋል። ​በግል የሚመጡ፦ ልጆቻቸውን በራሳቸው ትራንስፖርት የሚያመጡ ወላጆች ተማሪዎቹ በትክክለኛው ሰዓት (ከጥዋቱ 1:00 ሰዓት በፊት) ትምህርት ቤት መድረሳቸውን ማረጋገጥ አለባቸው። 1. ​የመጓጓዣ ሁኔታ፦ ተማሪዎች ከትምህርት ቤት ተነስተው ወደ ፈተናው ማዕከል የሚጓዙት በትምህርት ቤቱ አውቶቡሶች (ሰርቪሶች) አማካኝነት ነው። ​2. ተማሪዎች ይዘዋቸው ሊመጡ የሚገቡ ነገሮች ሀ. ​ምግብ እና መጠጥ፦ ቁርስ , ምሳ  እና በቂ የመጠጥ ውሃ። ለ. ​የጽሕፈት መሣሪያዎች፦ እርሳስ ,መቅረጫ እና ማስታወሻ ደብተር። ሐ. የት/ቤት መታወቂያ እና አድሚሽ ካርድ። ​3. ይዞ መምጣት የተከለከሉ ዕቃዎች ​ተማሪዎች የሚከተሉትን ዕቃዎች ወደ ትምህርት ቤትም ሆነ ወደ ፈተናው ማዕከል ይዞ መምጣት በጥብቅ የተከለከለ ነው፦ ሀ. ​የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎች (ሞባይል ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ላፕቶፖች፣ ስማርት ሰዓቶች እና መሰል ዕቃዎች) ለ. ​የውበት መዋቢያዎች (ኮስሞቲክስ)​ ሐ. ሹል እና ስለታም ነገሮች ወ.ዘ.ተ:: ​4. የደንብ ልብስ እና የግል ንጽህና ሀ. ​ሁሉም ተማሪዎች መደበኛውን የትምህርት ቤት ደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) መልበስ አለባቸው። ለ. ​ተማሪዎች (በተለይም ወንዶች ልጆች) ጸጉራቸውን በአግባቡ የተስተካከለ፣ ንጹህና ስልጡን በሆነ መልኩ ተቆርጠው መምጣት ይኖርባቸዋል። ​5. ወደ ቤት የመመለሻ ሰዓት ​የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሩ ከተጠናቀቀ ተማሪዎች በተለመደው የጉዞ መስመራቸው መሠረት በግምት ከምሽቱ 9:30 ሰዓት ላይ ወደየቤታቸው  በመደበኛው ስርቢስ ይመለሳሉ። የት/ቤቱ አስተዳዳር

photo content

photo content

የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣ ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

Dear Parents and Guardians of Grade 6 and Grade 8 Students, ​Please be informed that we are currently awaiting scheduling confirmation from the Addis Abeba Education Bureau regarding the upcoming national exam orientation. We anticipate receiving this information within the week and will announce the official orientation date immediately upon receipt. ​In the meantime, we kindly request that you continue to support and encourage your children to remain diligent in their studies and thoroughly prepare for the upcoming national examinations. ​Thank you for your continued cooperation and partnership in your child's education. ​Sincerely, The School Administration የውድ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ወላጆች/አሳዳጊዎች፤ ​የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ስለ ብሔራዊ ፈተናው ኦረንቴሽን (ገለጻ) የሚሰጥበት ቀን እንዲያሳውቁን እየተጠባበቅን መሆኑን እንገልጻለን። የኦረንቴሽን ቀን እንደተወሰነ ወዲያውኑ የምናሳውቅዎ ይሆናል። ​እስከዚያው ድረስ ግን፥ ልጆቻችሁ በትምህርታቸው ላይ ጠንክረው እንዲሰሩና ለሚመጣው ብሔራዊ ፈተና ራሳቸውን በሚገባ እንዲያዘጋጁ አስፈላጊውን ድጋፍና ማበረታቻ እንድታደርጉላቸው በአክብሮት እንጠይቃለን። ​ለልጆችዎ ትምህርት ስኬት ለምታደርጉት ቀጣይነት ያለው ትብብርና አጋርነት አስቀድመን ምስጋናችንን እናቀርባለን። ​ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር

📢🐝 Dear Parents/Guardians, 🐝📢 Last Saturday, we held the Final Round of This Year's Spelling Bee Competition (2026). The School Administration is delighted to announce the winners from our Elementary Campus. 🏆 Grade 1 Winners of This Year's Spelling Bee Competition 🏆 🥇 1st Place: Eldana Gashahun 🥈 2nd Place: Eyoatam Daniel 🥉 3rd Place: Yohanan Nebiyou 🏆 Grade 2 Winners of This Year's Spelling Bee Competition 🏆 🥇 1st Place: Eyuel Gashahun 🥈 2nd Place: Christina Alemtsehay 🥉 3rd Place: Nablis Tewodros 🏆 Grade 3 Winners of This Year's Spelling Bee Competition 🏆 🥇 1st Place: Eyoatam Tatek 🥈 2nd Place: Eyuel Nigussie 🥉 3rd Place: Amen Engida 🏆 Grade 4 Winners of This Year's Spelling Bee Competition 🏆 🥇 1st Place: Nathan Gashahun 🥈 2nd Place: Barkon Temesgen 🥉 3rd Place: Barkot Moges 🏆 Grade 5 Winners of This Year's Spelling Bee Competition 🏆 🥇 1st Place: Alula Temesgen 🥈 2nd Place: Yokabed Abebe 🥉 3rd Place: Hosanna Tomas 🏆 Grade 7 Winners of This Year's Spelling Bee Competition 🏆 🥇 1st Place: Ruhama Daniel 🥈 2nd Place: Naomi Kewani 🥉 3rd Place: Nahom Wondmagegn 🐝🌟 Special Recognition 🌟🐝 This year's Spelling Bee competition saw a remarkable achievement by the Gashahun family, with three siblings winning 1st Place in their respective grade levels: 🥇 Grade 1: Eldana Gashahun 🥇 Grade 2: Eyuel Gashahun 🥇 Grade 4: Nathan Gashahun 👏🐝🏆 What an extraordinary accomplishment! 🎉 The School Administration extends its sincere appreciation to all students, teachers, and parents for their dedication and support in making this year's competition a success. The School Administration 🐝📚✨🏆

photo content

photo content
+6

📅 ቀን፦ 21/9/2018 ዓ.ም ለውድ የኦዞን ት/ቤት ወላጆች/አሳዳጊዎች: በቅድሚያ የከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን፣   በት/ቤታችን በመማር ላይ የሚገኙ ልጆችዎን የትምህርት አገልግሎት የኳርተር ክፍያ በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በብርሃን ባንክ እና በአቢሲኒያ ባንክ በተዘጋጀው ኮድ እንዲፈጸም በተደጋጋሚ መልዕክቶችንና ማሳሰቢያዎችን ስናስተላልፍ ቆይተናል። ሆኖም የት/ቤት አገልግሎት ክፍያን በወቅቱ ባለመፈጸማችሁ የዓመቱ የሥራ ማጠናቀቂያ ተግባራችን ላይ ክፍተት እየፈጠረ ይገኛል። ስለዚህ የሚጠበቅባችሁን ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች ያለባችሁን ቀሪ ክፍያ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እያሳሰብን፣ ይህ ሳይደረግ ቢቀር ት/ቤቱ በሚወስደው የእርምት ተግባር ምክንያት ችግር እንዳይፈጠር ይህን የመጨረሻ ማሳሰቢያችንን በታላቅ አክብሮት እናስተላልፋለን። 📌 ማሳሰቢያ ቀሪ ክፍያችሁን በወቅቱ ላጠናቀቃችሁ ወላጆች ከልብ ምስጋናችንን እየገለጽን፣ ይህ መልዕክት የማይመለከታችሁ መሆኑን እናሳውቃለን። ከሰላምታ ጋር፣ የት/ቤቱ አስተዳደር