ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 148
订阅者
无数据24 小时
-27
-1930
帖子存档
photo content

photo content

photo content

ዕለተ ሐሙስ ሚያዚያ 30/2017ዓ.ምክር በተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ለተደራጁ ስራ ፈላጊዎች የህይወት ክህሎትስልጠና መስጠት ተጀመረ። ከአራዳ ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ 72 ለሚደርሱ የተርሚናል ኢንተ
+7
ዕለተ ሐሙስ ሚያዚያ 30/2017ዓ.ምክር በተርሚናል ኢንተርፕራይዝ  ዘርፍ ለተደራጁ  ስራ ፈላጊዎች የህይወት ክህሎትስልጠና መስጠት ተጀመረ። ከአራዳ ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ 72 ለሚደርሱ የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ (ተራ አስከባሪዎች) ለ5 ቀናት የሚቆይ የህይወት ክህሎት ስልጠና በዛሬው ዕለት መስጠት ተጀምሯል። በመክፈቻ ፕሮግራሙ የተገኙት የኮሌጃችን ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ለሠልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ስልጠናው ጠጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ መሆኑን  እና ከሠልጣኞች ምን ይጠበቃል? በማለት ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ሰልጣኞች በስልጠና ወቅት ለሚገጥሟቸው ችግሮች ከጎናቸው በመሆን አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን በመግለፅ መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተውላቸዋል። በተመሳሳይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ  ስለ ስልጠናው ሂደት ስለኮሌጁ አሰራር እና በቆይታቸው ማድረግ ስለሚገባቸው ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተያያዘም ሠልጣኞች ከህይወት ክህሎት ባለፈ የሰላምና ጸጥታ ፣ የመንገድ ትራንስፖርትን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠሪያው እንደሚሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል።                             ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ረቡዕ መጋቢት 29/2017ዓ.ም በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጁ ሽግግር ክፍል ብቁ ሞዴል ማድረጊያ ስልጠና ተሰጠ ። ከጉለሌ ክፍለ ከተማ እና ከወረዳዎች ለተውጣጡ የኢንተር ፕራይዝ ባለቤቶች
+4
ዕለተ ረቡዕ መጋቢት 29/2017ዓ.ም በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጁ ሽግግር ክፍል  ብቁ ሞዴል ማድረጊያ ስልጠና ተሰጠ ። ከጉለሌ ክፍለ ከተማ እና ከወረዳዎች ለተውጣጡ የኢንተር ፕራይዝ ባለቤቶች ፣ባለሙያዎችና ድጋፍ ለሚያደርጉ አሠልጣኞች ብቁ ሞዴል ማድረጊያ ስልጠና እና የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አሰጣጥ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለመገምገም ታልሞ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑ ተጠቁሟል። በስልጠናው መክፈቻ የተገኙት የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጁ ሽግግር ም/ዲን አቶ ወንድም ሲያምረኝ መኮንን ስልጠናውን ዓላማ በማስተዋወቅ ከስልጠናው ማጠናቀቂያ ስራዎችን በመገምገምና አቅጣጫ በማስያዝ ረገድ በጋራ መስራት እንደሚገባ አውስተው በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች ከከተማው ስራና ክህሎት ቢሮ በወረደው አቅጣጫ በመሆኑ ስልጠናውን በውል እንዲከታተሉ መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል። ስልጠናውን የሰጡት የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ባለሙያ አቶ ብርሃኑ ዘገየ የስልጠናውን አስፈላጊነት ፣ ሞዴል ኢንተር ፕራይዝ መመልመያ መስፈርቶች፣ ከሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምን ይጠበቃል ??፣ ሞዴል ሆነው መውጣታቸው ምን ጠቀሜታ አለው ?? በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ከቤቱ ሰፊ ሃሳብ አስተያየት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።       ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 28/2017ዓ.ም በቴክስታይል ጋርመንት የስልጠና ዘርፍ ለሰለጠኑ ሰልጣኞች ትብብር ስልጠና (cooperative training) የማስተሳሰሪያ መርሀ-ግብር ተካሄደ። በቴክስታይል ጋርመንት ስልጠና ዘርፍ የ2017 ዓ.ም የ1ኛ ዓመት ሠልጣኞች ለ20 ቀናት የሚዘልቅ  የትብብር ስልጠና በእድገት የልብስ ስፌት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የሚወስዱ መሆናቸው ታውቋል ።  እድሉን ያገኙ ሰልጣኞች በኮሌጁ ዲን እና በስልጠና ዘርፍ ተጠሪው መሪነት ወደ ስልጠናው ቦታው ሲደርሱ በኢንደስትሪው የሰው ሃብት አመራር አቶ አለሙ ደቦል   አቀባበል ተደርጎላቸዋል ። የትብብር ስልጠና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ መልእክት ያስተላለፉት የፋብሪካው የሰው ሃብት አስተዳደር አቶ አለሙ ደቦል እና ዲዛይነርና የጥራት አመራር ማናጀር አቶ አጫሉ ደጀኔ ሰልጣኞች በዚህ ድርጅት ጠንካራና ብቁ ባለሙያዎች ያሉበት ተቋም ውስጥ  የትብብር ስልጠና በመውሰዳቸው እድለኛ መሆናቸውን ገለፀው የተቋሙን ህግና ደንብ ማክበር ስነ-ምግባር በተሞላበት አግባብ  ስራቸውን መከወን የቻሉ ሰልጣኞች ከመሰልጠን ባሻገር ተቀጥረው የመስራት ዕድል እንደሚመቻችላቸው ጠቁመዋል።  በተያያዘም የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ እና የስልጠናና አካዳሚክ ምክትል ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ሠልጣኞች በቆይታ ግዜያቸው በቲዎሪ የተማሩትን ወደ መሬት በማውረድ የተግባር ልምምድ እንደሚያደርጉና ከመሰልጠን ባሻገር የስራ ባህልን ጠንቅቆ ለማወቅ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግላቸውና ይህን ታሳቢ በማድረግ ስልጠናውን በአግባቡ መውሰድ እና መከታተል እንደሚጠበቅባቸው በማመላከት መልካም የስልጠና ግዜ እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።                              ኮምንኬሽን ክፍል

photo content
+3

ዕለተ ማክሰኞ ሚያዝያ 28/2017ዓ.ም የመመረቂያ ስራ ግምገማ ተካሄደ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፋይን አርት ተመራቂ ሠልጣኞች የመመረቂያ ስራቸውን በማስገምገም ግብረ-መልስ ተቀበሉ ። ሠ
+9
ዕለተ ማክሰኞ ሚያዝያ 28/2017ዓ.ም የመመረቂያ ስራ ግምገማ ተካሄደ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፋይን አርት ተመራቂ ሠልጣኞች የመመረቂያ ስራቸውን በማስገምገም ግብረ-መልስ ተቀበሉ ። ሠልጣኞቹ የ2017 ዓ.ም ተመራቂዎች ሲሆኑ የእያንዳንዳቸው ለመመረቂያ የተዘጋጀ የስራ ውጤት ለታዳሚዎቹ በገለጻም በምስልም ካቀረቡ በኋላ ከታዳሚዎቹ ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽ ተሠጥቶ ሃሳብ አስተያየት ከታከለባቸው በኋላ ገንቢ የሆኑትን ነጥቦች በመቀበል ስራቸውን በተሻሻለ መንገድ አስተካክለው ለፍጻሜ እንደሚያቀርቡት ከግብረ መልሳቸው ለመረዳት ተችሏል። በዚህ ግምገማ አምስት ተመራቂዎች ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ሁለቱ አቅራቢዎች የህይወት ገጠመኞቻቸውን በስራው ላይ ለማንጸባረቅ የሞከሩበት ነበር ፤ የቀሪዎቹ ስራ ደግሞ ከግል እይታቸውና እምነታቸው የመነጩ ጉዳዮችን ባቀረቡት ስራዎቻቸው ላይ ለመግለጽ ሞክረዋል ። በተካሄደው የግምገማ ፕሮግራም የኮሌጁን ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድን ጨምሮ ምክትል ዲን ፣የትምህርት ክፍሉ ተጠሪና አሠልጣኞች እና ሠልጣኞች የሞቀ ተሳትፎ አድርገው ሚዛናዊ ሃሳብ አስተያየታቸውን እንደየ ምልከታቸው ለአቅራቢዎቹ ቸሯቸዋል። በዚህ የግምገማ ሂደት መስማት የተሳናቸው የትምህርት ክፍሉ ሠልጣኞች በአስተርጓሚያቸው በመታገዝ በጥያቄና አስተያየት መልክ የነበራቸው ተሳትፎ የግምገማ ሂደቱን የተለየ እንዲሆን ከማድረጉ ባሻገር ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ለመገንዘብ ተችሏል።                  ኮሙኒኬሸን ቡድን

ሰኞ፡- ሚያዚያ 27 ቀን 2017 ዓ.ም 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ዛሬ ተጀመረ። ለአሸናፊዎች የሜዳሊያ፣ የዋንጫና የገንዘብ ሽልማት መዘጋጀቱ ተጠቁሟል። ዘንድሮ የሚካሄደው 4ኛው ሀገር አቀፍ
+2
ሰኞ፡- ሚያዚያ 27 ቀን 2017 ዓ.ም 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ዛሬ ተጀመረ። ለአሸናፊዎች የሜዳሊያ፣ የዋንጫና የገንዘብ ሽልማት መዘጋጀቱ ተጠቁሟል። ዘንድሮ የሚካሄደው 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር " ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች " በሚል ሀሰብ እንደሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታውቋል። መርሃ ግብሩ ከዛሬ ሚያዚያ 27 ቀን እስከ ግንቦታ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት እየተካሄደ ይቆያል። ውድድሩ በክህሎት፣ በቴክኖሎጂና ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዘርፎች ነው የሚካሄደው። በውድድሩም፣ " በሁሉም ክልሎችና በሁለቱም ከተማ አስተዳደሮች በተካሄዱ ተመሳሳይ ውድድሮች አንደኛ ሆነው ያጠናቀቁ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች፣ የኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች ይሳተፋሉ " ተብሏል። ለውድድሩ አሸናፊዎች የሜዳሊያ፣ የዋንጫና የገንዘብ ሽልማት ይበረከታል። የውድድሩ ዓላማ የዘርፉን አዲስ እሳቤ መሠረት ያደረገ የአሰልጣኞች፣ የሠልጣኞችና ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ሙያቸውን እንዲያዳብሩ፣ አቅማቸውን እንዳያሳዩ፣ ቴክኖሎጂችን ባለሃብቶችና ኢንተርፕራይዞች ወደ ምርት አገልግሎት እንዲያሸጋግሩ ጭምር ነው። በ2015 ዓ/ም በ3ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂ የፈጠሩ ተወዳዳሪዎች በ2016 ዓ/ም ከ80 በላይ ቴክኖሎጂዎችን እንዳመረቱ ተነግሯል። ፕሮግራሙ በ2017 በጀት ዓመት “ስኪል ኢትዮጵያ” በሚል ስያሜ ቀጥሎ፣ በአሁኑ ጊዜም 180 የሚሆኑ የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን አምርተው በማውጣት ሂደት እንደሚገኙ ተመልክቷል። ‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት›› ምንጭ፦ ቲክቫህ ኢትዮጵያ

photo content

እንኳን ለ 84ኛው የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ።

የዘመናዊ ትምህርት መለያ https://youtube.com/watch?v=KgcwIbbrG_U&feature=shared

ለአርበኝነት የቀረበው የትምህርት ማዕከል https://youtube.com/watch?v=gQhVRLAolH8&feature=shared

ሰላም እንደምን ዋላችሁ 👉እንደሚታወቀው የከተማው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንትን አስመልክቶ የሚካሄደው የስፖርት ውድድር ከግንቦት አንድ ጀምሮ እንሚካሄድ ይታወቃል። 👉 ከዚህ ጋር ተያይዞ 🧨በአሰልጣኝ እና በሰልጣኝ የወንዶች የእግር ኳስ 🧨 በሰልጣኞች የወንዶቸ የመረብ ኳስ 🧨 በዲኖች መካከል በሁለቱም ጾታ የገመድ ጉተታ 🧨 በሰልጣኝ በሁለቱም ጾታ የጠረቤዛ ቴኒስ 👉👉ውድድር የሚካሄድ ሲሆን እስከ ፊታችን ማክሰኞ ድረስ የሚከተሉት እንድትልኩልን:- 1) የምትሳተፉበትን የውድድር አይነት 2) የተወዳዳሪዎች ስም ዝርዝር 3) አሰልጣኝ 4) ቡድን መሪ እና 5) ወጌሻን 👆👆እስከ ማክሰኞ 6፡30 ድረስ በደብዳቤ እንድታሳውቁን ይሁን። 👉👉የሴቶች የጠረቤዛ ቴኒስ ውድድር ተሳታፊዎች ሲኖሩ ብቻ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

photo content
+1

photo content
+7

ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ትምህርታዊ ጉብኝት ተደረገ። ጉብኝቱን ያደረጉት ሴት ታዳጊ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ 2ኛ ደረጃ ትምህር ቤቶች ውስጥ አንዱ ከሆነው ከደጃዝማች ወንድ ይራድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ናቸው ። የዚህ ጉብኝት ዋና ዓላማ ሴት ተማሪዎቹ በሳይንስ ፣በቴክኖሎጂ፣ በኢንጅነሪንግና በሒሳብ ትምህርቶች በጎ ፍላጎት እንዲያሳድሩ እና ወደ ፊት በሚሰማሩበት የሙያ መስክ የነዚህን ትምህርቶች ጥቅም ለመገንዘብ እንዲችሉ መሆኑን ለጉብኝት ጥያቄ ከተላከው ደብዳቤና አባሪ ከሆነው የስምምነት ማጣቀሻ ለመገንዘብ ተችሏል። ወደ 80 የሚደርሱ ታዳጊ ሴት ጎብኝ ተማሪዎች በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲደርሱ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል በኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ  ተደርጎላቸዋል ። በአጠቃላይ ስለ ቴክኒክና ሙያ ምንነት ፣አስፈላጊነት እና ታሪካዊ ዳራው አጠር ያለ መግለጫ ከተሰጣቸው በኋላ ኮሌጁን እንዲተዋወቁ ተደርጓል። ከአዳራሹ መግለጫ ቀጥሎም በቡድን ተከፋፍለው የስልጠና ዘርፍ ሾፖችን እስከነ ተግባራዊ እንቅስቃሴያቸው ለመጎብኘት ችለዋል። ሴት ታዳጊ ተማሪዎቹ በጉብኝቱ በጣም እንደተደሰቱና በተለያዩ ሞያዎች ላይ የነበራቸውን እውቀት በጉብኝቱ እንደጨመረ ፤ ባዩት መልክ ስልጠና እንደሚሰጥና ኮሌጁ በዚህ ደረጃ የተደራጀ መሆኑን ግንዛቤ እንዳልነበራቸው ፤ በጉብኝታቸው ጠቃሚ ነገሮችን እንደቀሰሙ ከሰጡት አስተያየት ለመረዳት ተችሏል። የጉብኝት ፕሮግራሙ የተዘጋጀው ሀሁ ጆብስ በሳይንስ በተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ እስቴም ኢዱኬሽን ፎር ኢምፓወርመንት ፕሮጀክት ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር መሆኑን ከደረሰን መረጃ ተረድተናል።                  ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

ሚያዝያ 24/2017ዓ.ም በሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና ተካሄደ። በሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ በCulinery Art ከደረጃ 2 ወደ ደረጃ 3 የሚሸጋገሩ 6 ወንዶች እና 16 ሴት ሰ
+5
ሚያዝያ 24/2017ዓ.ም በሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና ተካሄደ። በሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ  በCulinery Art ከደረጃ 2 ወደ ደረጃ 3 የሚሸጋገሩ 6 ወንዶች እና 16 ሴት ሰልጣኞች እንዲሁም ከደረጃ 3 ወደ ደረጃ 4 የሚሸጋገሩ 7 ሴት ሰልጣኞች ለምዘና ተቀምጠዋል። ምዘናው በትምህርት ክፍሉ ተዘጋጅቶ በስልጠና ዘርፉ ተገምግሞና ጸድቆ የሚሰጥ ሲሆን ለምዘና የተቀመጡ ተመዛኞች የተግባር ምዘናውን በብቃት ያጠናቀቁ  ሲሆን የጽሁፍ ፈተና ውጤታቸው ታርሞ በሚቀጥሉት ቀናት የሚታወቅ መሆኑን የትምህርት ክፍሉ ተጠሪ አቶ ገ/መድህን ብርሃኑ መረጃውን አጋርተውናል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን