1 147
订阅者
无数据24 小时
-27 天
-1930 天
帖子存档
1 147
ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ትምህርታዊ ጉብኝት ተደረገ።
ጉብኝቱን ያደረጉት ሴት ታዳጊ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ 2ኛ ደረጃ ትምህር ቤቶች ውስጥ አንዱ ከሆነው ከደጃዝማች ወንድ ይራድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ናቸው ።
የዚህ ጉብኝት ዋና ዓላማ ሴት ተማሪዎቹ በሳይንስ ፣በቴክኖሎጂ፣ በኢንጅነሪንግና በሒሳብ ትምህርቶች በጎ ፍላጎት እንዲያሳድሩ እና ወደ ፊት በሚሰማሩበት የሙያ መስክ የነዚህን ትምህርቶች ጥቅም ለመገንዘብ እንዲችሉ መሆኑን ለጉብኝት ጥያቄ ከተላከው ደብዳቤና አባሪ ከሆነው የስምምነት ማጣቀሻ ለመገንዘብ ተችሏል።
ወደ 80 የሚደርሱ ታዳጊ ሴት ጎብኝ ተማሪዎች በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲደርሱ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል በኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ተደርጎላቸዋል ። በአጠቃላይ ስለ ቴክኒክና ሙያ ምንነት ፣አስፈላጊነት እና ታሪካዊ ዳራው አጠር ያለ መግለጫ ከተሰጣቸው በኋላ ኮሌጁን እንዲተዋወቁ ተደርጓል። ከአዳራሹ መግለጫ ቀጥሎም በቡድን ተከፋፍለው የስልጠና ዘርፍ ሾፖችን እስከነ ተግባራዊ እንቅስቃሴያቸው ለመጎብኘት ችለዋል።
ሴት ታዳጊ ተማሪዎቹ በጉብኝቱ በጣም እንደተደሰቱና በተለያዩ ሞያዎች ላይ የነበራቸውን እውቀት በጉብኝቱ እንደጨመረ ፤ ባዩት መልክ ስልጠና እንደሚሰጥና ኮሌጁ በዚህ ደረጃ የተደራጀ መሆኑን ግንዛቤ እንዳልነበራቸው ፤ በጉብኝታቸው ጠቃሚ ነገሮችን እንደቀሰሙ ከሰጡት አስተያየት ለመረዳት ተችሏል።
የጉብኝት ፕሮግራሙ የተዘጋጀው ሀሁ ጆብስ በሳይንስ በተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ እስቴም ኢዱኬሽን ፎር ኢምፓወርመንት ፕሮጀክት ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር መሆኑን ከደረሰን መረጃ ተረድተናል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 147
+9
ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲካሄድ የቆየው የስፖርት ፌስቲቫል ተጠናቀቀ።
ወገኔ የተሰኘው ራስ አገዝ ማህበር ሲያካሂድ የቆየውን የስፖርት ፌስቲቫል የኮሌጁ ዲኖች በክብር እንግድነት በተገኙበት የፍፃሜ ፕሮግራሙ ተካሂዷል።
በስፖርት ፌስቲቫሉ የወንዶችና የሴት ተወዳዳሪዎች የተሳተፉበት ሲሆን በወንዶች በኩል የአስተዳደር ሰራተኞችን የወከለው ቡድን እና በቴክስታይል ጋርመንት የሌዘር ስልጠና ዘርፍ ቡድን ለዋንጫ ፉክክር ተጫውተው በአሰልጣኞች አሸናፊነት ተጠናቋል በተመሳሳይ በሴት የአስተዳደር ሰራተኞች እና ሴት አሠልጣኞቾ መካከል በተደረገው ውድድር ደግሞ የሴት አስተዳደር ሰራተኞች ቡድን በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል።
በፌስቲቫሉ መክፈቻ ላይ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የመልካም ምኞች መግለጫ ያካተተ ንግግር አድርገዋል። በመዝጊያው ስነ-ስርዓት ላይ ደግሞ የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ማህበሩ ላደረገው በጎ ተግባር ካመሰገኑ በኋላ ወደ ፊት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በመጨረሻም ለአሸናፊዎች የተዘጋጀውን የዋንጫ ሽልማት አበርክተዋል ።
በፌስቲቫሉ ሂደት የተለያዩ የገቢ ማስገኛዎች የተከናወኑ ሲሆን ከነዚህ የገቢ ምንጮች በተገኘ ገንዘብና የማህበሩ ወዳጆች ባበረከቱት የገንዘብ ስጦታ የሙዳይ በጎ አድራጎት ድርጅት ለሚያሳድጋቸው ሦስት ህጻናት የአንድ ዓመት ሙሉ ወጫቸውን ወደ 21,000(ሃያ አንድ ሺህ ብር )የሚጠጋ ገንዘብ ማበርከቱን የማህበሩ ሰብሳቢ አሠልጣኝ ዮናስ መረጃውን አጋርተውናል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 147
+7
ሚያዝያ 24/2017ዓ.ም
ከ2017ዓ.ም ዕጩ ተመራቂ ሠልጣኞች ጋር
ውይይት ተካሄደ።
በስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምዲን ለ2017ዓ.ም ዕጩ ተመራቂ ሠልጣኞች በስልጠናው ሂደት እንዲሁም ከምዘና አኳያ የመንግስትን አቅጣጫ በተለያየ አጋጣሚ በተደጋጋሚ የተገለጸላቸው መሆኑ ይታወቃል።
በዛሬው ዕለት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ከሰባት የስልጠና ዘርፎች 684 ተመራቂ ሠልጣኞች እንደሆኑ የገለጹት የሬጅስትራር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስመኝ ሚደቅሳ ናቸው ።
የመድረኩ ዓላማ እጩ ተመራቂዎች በስልጠና ሂደት ላይ የገጠማቸውን እና መስተካከል አለበት ያሉትን በማንሳት ዉይይት ተደርጎባቸው የመፍትሄ አቅጣጫ ለማሰቀመጥ እንዲቻል ያለመ ነበር።
ሠልጣኞቹ ያነሷቸው አንዳንድ መስተካከል አለባቸው ያሉዋቸውን ጉዳዮች ምክክር ከተደረገባቸው በኋላ የኰሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ውይይቱን በማጠቃለል የተነሱት ችግሮች በየደረጃቸቸው እንደሚፈቱ ጠቁመው መግባባት ላይ ተደርሰዋል።
በኮሌጅ ደረጃ የሚፈቱትን አፋጣኝ ምላሽ እንደሚያገኙ እና በኮሌጁ ደረጃ የማይፈቱት ደግሞ ከሚመለከተው አካል ጋር በመወያየት ምላሽ እንደሚያገኙ በማስረደት ስብሰባው ተጠናቋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 147
+5
ሚያዚያ 21/2017 ዓ.ም
የመቶኛ ዓመት በዓል አከባቡር የክትትል ግምገማ ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 100ኛ ዓመት በዓል አከባበር መጀመሩን ተከተሎ የዕቅድ ክንውን የክትትል ግምገማ በኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ተካሄደ።
በበዓል አከባበሩ የመጀመሪያ ቀን ከውጭና ከሃገር ውስጥ በታደሙ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር አባላት በዋናነት፤የራስ ተፈሪያንስ ተጋባዦች ደግሞ በእንግድነት ተሳትፈው ባደመቁት አንፀባራቂ በዓል የኮሌጁ ማህበረሰብ አጠቃላይ የነበራቸው ተሳትፎ ቀዝቃዛ እንደነበር አልሸሸጉም ፤ ምክንያቱንም ተረድቶ በቀጣይ ተመሳሳይ ስህተት ላለመፈጸም ይረዳ ዘንድ የክትትል ግምገማው ተሳታፊዎች ጠንከር ያሉ ጥያቄዎችን አቅርበው ውይይት ተካሂዷል።
በከፍተኛ ደረጃ የሚጠበቀው የISO የምስክር ወረቀት ለማግኘት ከሚደረገው ጥረት ጋርም ተያይዞ የበዓል አከባበሩ መጠነ ተሳትፎው በጎ አመላካች አለመሆኑን ገልፀዋል። ስለዚህ እያንዳንዱ ሰራተኛ ትኩረት ሰጥቷ ኦንዲንቀሳቀስ በአመራር ላይ ያሉ አካላት ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠበቅ ያለ መመሪያ ሰጥተዋል ።
በዚህ የክትትል ግምገማ ኮር የአመራር አባላት፣የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች፣ አስተባባሪዎች ፣ ዳይሬክቶሬቶች እና ብድን መሪዎች መሳተፋቸውን ለማወቅ ተችሏል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 147
ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ስልጠና ስድስተኛ ቀኑን ይዟል።
ለወጣቶች የህይወት ክህሎት እና የስራ ፍለጋ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል።
ስልጠናው የኢፌዴሪ መንግስት እና በዓለም ባንክ በጋራ መግባባት እየተሰጠ ያለው ስልጠና ነው። የጉለሌ ክ/ከተማ ከከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ስራ አጥ ወጣቶችን ወደ ስራ የሚያስገባ የ12 ቀን የህይወት ክህሎት ፣ ስራ ፍለጋ እና የዲጅታል ክህሎት ስልጠና በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ መስጠት ከተጀመረ ዛሬ ለስድስተኛ ቀን እየተሰጠ ይገኛል።
የፕሮግራሙ ዓላማ እንደ ሀገር የሰፋዉን የወጣቶች ስራ አጥነት መቀነስ እንዲሁም የመንግስት እና የግል ሴክተሩን ማስተሳሰር እንደሆነ ለክፍላችን የገለጹት የጉለሌ ክ/ከተማ የብቃት ወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስፔሻሊስት አቶ ፍቅረስላሴ ንጉሴ እንዳሉት ይህ ስልጠና የአሰልጣኝነት ስልጠና በወሰዱ ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን ሰልጣኞቹ በመረጡት የስልጠና ዘርፍ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር በስራ አውደርዕይ (job fair)እንዲገናኙ በማድረግ ፣ የስራ ላይ ልምምድ እና ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ የሚሰማሩበት ፕሮግራም መሆኑን ተናግረዉ አያይዘዉም እንደ ሀገርም እንደ ክ/ከተማማ ይህ ፕሮግራም ለ3ኛ ጊዜ የተዘጋጀ መሆኑን አዉስተዉ ከዚህ በፊት በተሰጡት 2 ዙሮች መቶ በመቶ ዉጤታማ መሆናቸዉን ገልጸዋል ።
ዛሬ ስድስተኛ ቀኑን ባስቆጠረዉ መርሃግብር እድሜያቸዉ ከ18 እስከ 25 አመት የሆናቸዉ ከጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07፣ወረዳ 08 እና ወረዳ 09 የተመለመሉ 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ እና ከዚያ በታች የሆኑ ስራ አጥ ወጣቶች ስልጠናዉን በአግባቡ እየተከታተሉ እንደሆነ እና 60 በመቶዉ ተሳታፊዎች ሴቶች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
የጉለሌ ክ/ከተማ የብቃት ወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስፔሻሊስት አቶ ፍቅረስላሴ ንጉሴ በመጨረሻም የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ስራዉ የጋራችን ነዉ በማለት በፋሲሊቲ ፣ በማቴርያል ፣ በሞራል እና በሌሎች በኩል ላደረገላቸዉ ድጋፍ የኮሌጁን አመራሮች ፣ ሰራተኞች እና አሰልጣኞችን አመሰግነዋል።
የኮሙኒኬሽን ቡድን
1 147
ሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ስልጠና ስድስተኛ ቀኑን ይዟል።
ለወጣቶች የህይወት ክህሎት እና የስራ ፍለጋ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል።
ስልጠናው የኢፌዴሪ መንግስት እና በዓለም ባንክ በጋራ መግባባት እየተሰጠ ያለው ስልጠና ነው። የጉለሌ ክ/ከተማ ከከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ስራ አጥ ወጣቶችን ወደ ስራ የሚያስገባ የ12 ቀን የህይወት ክህሎት ፣ ስራ ፍለጋ እና የዲጅታል ክህሎት ስልጠና በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ መስጠት ከተጀመረ ዛሬ ለስድስተኛ ቀን እየተሰጠ ይገኛል።
የፕሮግራሙ ዓላማ እንደ ሀገር የሰፋዉን የወጣቶች ስራ አጥነት መቀነስ እንዲሁም የመንግስት እና የግል ሴክተሩን ማስተሳሰር እንደሆነ ለክፍላችን የገለጹት የጉለሌ ክ/ከተማ የብቃት ወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስፔሻሊስት አቶ ፍቅረስላሴ ንጉሴ እንዳሉት ይህ ስልጠና የአሰልጣኝነት ስልጠና በወሰዱ ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን ሰልጣኞቹ በመረጡት የስልጠና ዘርፍ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር በስራ አውደርዕይ (job fair)እንዲገናኙ በማድረግ ፣ የስራ ላይ ልምምድ እና ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ የሚሰማሩበት ፕሮግራም መሆኑን ተናግረዉ አያይዘዉም እንደ ሀገርም እንደ ክ/ከተማማ ይህ ፕሮግራም ለ3ኛ ጊዜ የተዘጋጀ መሆኑን አዉስተዉ ከዚህ በፊት በተሰጡት 2 ዙሮች መቶ በመቶ ዉጤታማ መሆናቸዉን ገልጸዋል ።
ዛሬ ስድስተኛ ቀኑን ባስቆጠረዉ መርሃግብር እድሜያቸዉ ከ18 እስከ 25 አመት የሆናቸዉ ከጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07፣ወረዳ 08 እና ወረዳ 09 የተመለመሉ 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ እና ከዚያ በታች የሆኑ ስራ አጥ ወጣቶች ስልጠናዉን በአግባቡ እየተከታተሉ እንደሆነ እና 60 በመቶዉ ተሳታፊዎች ሴቶች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
የጉለሌ ክ/ከተማ የብቃት ወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስፔሻሊስት አቶ ፍቅረስላሴ ንጉሴ በመጨረሻም የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ስራዉ የጋራችን ነዉ በማለት በፋሲሊቲ ፣ በማቴርያል ፣ በሞራል እና በሌሎች በኩል ላደረገላቸዉ ድጋፍ የኮሌጁን አመራሮች ፣ ሰራተኞች እና አሰልጣኞችን አመሰግነዋል።
የኮሙኒኬሽን ቡድን
1 147
ዕለተ እሁድ ሚያዚያ 19/2017ዓ.ም
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዝያ 19ቀን 2017ዓ.ም መቶኛ ዓመቱን አክብሯል።
ታሪካዊቷ ዕለት የዛሬ 100ዓመት ዕለተ ሰኛ ከጥዋቱ 4:00 የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የተከፈተበት ዕለት ነበር። ዛሬ ላይ ሆነን ይህን የአንድ ምዕተ ዓመት ክብረ በዓል በታሪክ አጋጣሚ ለማክበር መብቃት ምንኛ መታደል ነው ?? የዕለቱ የክብር እንግዳ የቀድሞ የኢፌድሪ ፕሬዘዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ በቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር እና ቤተሰቦቻቸው እንደዚሁም የራስ ተፈሪያንስ ተከታዮች የታደሙበት ነበር ።
የበዓል አከባበሩ በኮሌጁ ግቢ ሰንደቅ ዓላማ የመስቀል ስነ- ስርዓት በኢ/ያ ህዝብ መዝሙር ታጅቦ ተከናውኗል።
ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዘዳንት ብስራት አክሊሉ(ዶ/ር) ለእንግዶች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈው በመናፈሻ ፓርኩ የተሰሩ ስራዎች ላይ የቀድሞ ተማሪዎች ስማቸው ያረፈበት የማረፊያ ስፍራ እና የግቢው በር የደረሰበትን እና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ በመስጠት ታዳሚዎች እየተዘዋወሩ እንዲጎበኟቸው እና እየተሰራ ያለውን የግቢ በር እንዲሁም በስልጠና ዘርፎች ጉብኝት ተደርጓል።
በበዓሉ የክብር እንግዳ የቀድሞ ፕሬዘዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ ታሪክን በቅብብሎሽ እዚህ ላደረሱት ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በበዓሉ ላይ ከተገኙት መካከል የ101ዓመት ዕድሜ ጠገቡ ደጃዝማች ወ/ሰማያት ገ/ወልድ ከ1936-1939ዓ.ም በትምህርት ቤቱ መማራቸውን ገልጸው በዘመናቸው የነበረው ትውልድ የሃገር ወዳድነት /የሃገር ፍቅር ስሜትን በዛሬዎቹ ተተኪ ትውልድ ላይ እንዲታይ እና እንዲሰርጽ ጠንክራችሁ ስሩ በማለት መልእክታቸውን በአጽንኦት አስተላልፈዋል።
በመቀጠልም በየዘርፉ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ለጋራ ውይይት በአዳራሽ ለተሰበሰበው ታዳሚ የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን በማስቀደም ከቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ጋር ያላቸውን መልካም ግኑኝነት ማህበሩ ለኮሌጁ ሲያበረክት የቆየውን አስተዋጽኦ ዋና ዋናዎቹን በመግለፅ ለወደፊቱ ይህ ትብብር እና መተጋገዝ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እምነታቸው መሆኑን በማጉላት ማህበሩ ያቀደውን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲችል የኮሌጁ ድጋፍ እንደማይለየው አረጋግጠዋል።
በተመሳሳይ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዘዳንት ብስራት አክሊሉ(ዶ/ር) ማህበሩ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ለኮሌጁ የተለያዩ ድጋፎችን የፋይናንስ፣ የማቴሪያልና አገልግሎትን ጨምሮ ሲያደርግ መቆየቱን በማስታወስ በአሁኑ ሰዓት የመዝናኛ ስፍራ እድሳት እና ግንባታ፣ የዋናው መግቢያ በር ግንባታ ፣ ባለ 4 ወለል ህንፃ ለመገንባት ጥረት እያደረገ መሆኑን አብስረዋል።
በዚህ የ100ኛ ዓመት ለመታደም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የቀድሞ ተማሪዎች የመጡ ሲሆን አንዳንዶቹ ተሳታፊዎች አባቶቻቸውና አያቶቻቸውን ወክለው በዓሉን ለማክበር በመቻላቸው ደስተኛ እንደሆኑ ይገልጻሉ። በዚህ በዓል የታደሙት የጃማይካ ተወላጆች ወይም ራስ ተፈሪያንስ በሙዚቃ ጥበባቸው መቶኛ ዓመቱን በልዩ ሁኔታ ድምቀት ሆነዋል ለማለት ይቻላል።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሌለው " የለም" ብቻ ነው ። ዘወትር የኮሌጃችን ፈርጥ የሆነው የኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ በሙዚቃው፣ በቲያትርና ሥዕል ስራዎቻቸው የበዓሉ ድምቀት ሆነው የመቶ ዓመት ሂደቱን በሞያቸው ለታዳሚዎች ተደራሽ አድርገዋል ። በተመሳሳይ በቴክስታይል ጋርመንት ስልጠና ዘርፍ በተዘጋጁ ምርቶች ታዳሚውን ያስደመመ የፋሽን ሾው(ትርኢት )አከናውነዋል።
በተጨማሪም የስልጠና ዘርፉ ያፈራቸው የጋርመንትና የቆዳ ውጤቶች በኤግዚቢሽን መልክ ኢንዲታዩ ከመደረጋቸው በላይ ምሮቶቹ (ቀበቶ ፣ቦርሳ፣ ታሸርት፣ ስካርቭ ወ.ዘ.ተ ለሽያጭ ቀርበዋል ።
የዕለቱ የክብር እንግዳ የቀድሞ የኢፌዲሪ ፕሬዘዳንት ክብርት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ አዲስ በተገነባው ዋናው አካባቢ ለማስታወሻነት የሚሆን በብሩሽ ጽሁፋቸውን አኑረዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 147
ከ1985-1988 የተማራችሁ አቤት አቤት እያልን እንኳንም ለ100ኛ ዓመት በዓል አደረሠን በዚህን ወቅት አርቲስት ህብስት ጥሩነህ፣አርቲስት ትግስት በቀለ ታሳቢ ቢደረጉ አብረን አናንሳቸው የገብረክርስቶስ ግርፎች ነንና እንኳን አደረሳችሁ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
