ch
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

前往频道在 Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Chat us! Buy ads: https://telega.io/c/consite

显示更多
3 607
订阅者
-324 小时
-77 天
+1130 天
帖子存档
በ40/60 የጋራ ሕንፃዎች ላይ የሚገኙ የንግድ ቤቶች ጨረታ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ ➖▭‼️▭➖ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ክ/ከተሞች ተገንብተው በተጠናቀቁ የ40/60 የጋራ ህንጻዎች ላይ የሚገኙ ንግድ ቤቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በሽያጭ ለማስተላለፍ ከነሃሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመሸጥ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ከጨረታ ተሳታፊዎች ፍላጎት በመነሳት እና ለዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ መመለሻ በቂ ጊዜ ለመስጠት ሲባል የጨረታ ሰነድ መሸጫና መመለሻ ጊዜን ማራዘም አስፈላጊ መሆኑ በኮርፖሬሽኑ ስለታመነበት ከመስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር/10 ተከታታይ የሥራ ቀናት/ቅዳሜን ሙሉ ቀን ጨምሮ/የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን፤ ጨረታው ጥቅምት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ተዘግቶ በጨረታ መመሪያው በተገለጸው ቅደም ተከተል መሠረት ከጥቅምት 08 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚከፈት መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን     

በ40/60 የጋራ ሕንፃዎች ላይ የሚገኙ የንግድ ቤቶች ጨረታ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ ➖▭‼️▭➖ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ክ/ከተሞች ተገንብተው በተጠናቀቁ የ40/60 የጋራ ህንጻዎች ላይ የሚገኙ ንግድ ቤቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በሽያጭ ለማስተላለፍ ከነሃሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመሸጥ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ከጨረታ ተሳታፊዎች ፍላጎት በመነሳት እና ለዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ መመለሻ በቂ ጊዜ ለመስጠት ሲባል የጨረታ ሰነድ መሸጫና መመለሻ ጊዜን ማራዘም አስፈላጊ መሆኑ በኮርፖሬሽኑ ስለታመነበት ከመስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር/10 ተከታታይ የሥራ ቀናት/ቅዳሜን ሙሉ ቀን ጨምሮ/የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን፤ ጨረታው ጥቅምት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ተዘግቶ በጨረታ መመሪያው በተገለጸው ቅደም ተከተል መሠረት ከጥቅምት 08 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚከፈት መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን     

+9
FIDIC Contracts Reference BOOK.pdf1.94 MB

ድርጅታችን ሚትዮራይት ኮንስትራልሽን ሃ/የተ/የግ/ማህበር ከዚህ በታች በተገለጹት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጸውን መስፈርት የምታ
ድርጅታችን ሚትዮራይት ኮንስትራልሽን ሃ/የተ/የግ/ማህበር ከዚህ በታች በተገለጹት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጸውን መስፈርት የምታሟሉና መወዳደር የምትፈልጉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 (ሰባት) ተከታታይ የስራ ቀናት ዉስጥ አዳማ ከተማ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በድርጅቱ የኢሜል አድራሻ emnu203@gmail.com  ወይንም ደግሞ በተጠቀሱት ቁጥሮች የቴሌግራም አድራሻ በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

👉ባለስልጣኑ የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማነቃቃት የሀገር ውስጥ ተቋራጮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ አስታወቀ! የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማነቃቃት የሀገር ውስጥ ተቋራጮች ላይ ትኩረት በማድረግ፤ ለግል ኮንስትራክሽን ማኅበራት ቅድሚያ ሰጥቶ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ለአሐዱ አስታውቋል።  የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር)፣ "መንግሥት የሕግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ለሀገር ውስጥ ኮንስትራክሽን ማኅበራት ቅድሚያ ሰጥቷል" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል። አንዳንድ የኮንስትራክሽን ተቋማት "መንግሥት ከሀገር ውስጥ ይልቅ ለውጭ ተቋራጮች ቅድሚያ እየሰጠ ነው" የሚል ቅሬታ እንዳላቸው ከአሐዱ ለተነሳላቸው ጥያቄ ዋና ዳይሬክተሩ ሲመልሱ፤ "መንግሥት የሚያሰራቸው ትልልቅ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ተቋራጮች የመፈፀም አቅም በላይ ሲሆኑ ፕሮጀክቱ ለውጭ ኩባንያዎች ይሰጣል" ብለዋል። አንዳንድ ሥራዎች ላይ የውጭ ኩባንያዎች መሳተፋቸው እና ቅድሚያ ማግኘታቸው አስፈላጊ የሚሆንበት ጊዜ እንዳለም አብራርተዋል። ፕሮጀክቶች ለውጭ ተቋራጮች ሲሰጡ የኩባንያዎቹ የመፈጸም አቅም እና የመምራት ችሎታ ታይቶ እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተውበታል። አክለውም "መንግሥት የሕግ ማዕቀፍ እያዘጋጀ ቢሆንም በትልልቅ ፕሮጀክቶች ላይ የሀገር ውስጥ ተቋራጮች አቅም ውስንነት አለ። ይህንን ድክመት ከውጭ ከሚመጡ ኩባንያዎች የአሰራር ሂደት፣ የቴክኖሎጂ እና የአፈጻጸም ብቃት በምንወስደው ልምድ አቅማችንን ለማሳደግ ልንጠቀምበት ይገባል” ብለዋል። የኮንስትራክሽን ዘርፉ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ድርሻ ያለው ቢሆንም፤ ዘርፉ በሚገባው ልክ እንዳያድግ እንቅፋት ከሆኑ ነገሮች መካከል የግሉ ዘርፍ አለመጠናከር፣ የግዢ ሥርዓት ፍትሐዊ አለመሆን፣ ግጭቶችና የበጀት ማነስ፣ ለችግሮች አፋጣን እና ግልጽ የመፍትሄ አለመስጠት በዋነኝነት ተጠቅሰዋል።

ጊዜያዊ የረዥም ጊዜ (የኮንትራት) ቅጥር ማስታወቂያ በዚህ ሊንክ ገብተው ይመዝገቡ https://forms.gle/oqbteUcWuRneaMGE6
ጊዜያዊ የረዥም ጊዜ (የኮንትራት) ቅጥር ማስታወቂያ በዚህ ሊንክ ገብተው ይመዝገቡ https://forms.gle/oqbteUcWuRneaMGE6

👉 INTERCON Construction Chemicals ● Concrete Admixtures ● Bonding Agents ● Waterproofings ● Wall Putty, Prime Coat ● Concret
👉 INTERCON Construction Chemicals  ● Concrete Admixtures ● Bonding Agents ● Waterproofings ● Wall Putty, Prime Coat ● Concrete Repair Mortar ● Floor hardener, Epoxy ● Grout, Self-level mortar ● Quartz paint, Contextra ● Tile Adhesive & Tile Joint Fillers  ● Geotextiles and other construction chemicals and materials Tel: 0961955555 Address 1: Signal road, around Dinberwa Addres 2: Wellosefer, around Dani Plaza

🔷invitation for National Competitive Bid Development Bank of Ethiopia!
🔷invitation for National Competitive Bid Development Bank of Ethiopia!

🕳የንግድ ቤቶች ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ
🕳የንግድ ቤቶች ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ

👉የቅድመ ክፍያ እና በኮንትራክተሩ ሚሰጥ ማስያዥያ:- 💫ቅድመ ክፍያ ማለት ምን ማለት ነው? -አንድ ተቋራጭ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ዉል ከገባ በዉሉ ሰነድ ላይ በተቀመጠው መሰረት ቅድመ ክፍያ ይከፈለዋል ያው ወለድ የሌለው ብድር አሰሪው ለ ሥራ ተቋራጩ ይሰጠዋል ማለት ነው። - ይህ ቅድመ ክፍያ የሚከፈለው ተቋራጩ ስራዉን ለመጀመር እንዲረዳው ነው። - ስቶር ለመስራት ማሽነሪ እና የሰው ሃይል ሞቢላይዝ ለማድረግ ለግንባታ ስራ የሚረዱ አስፈላጊ የሆኑ ማቴርያል እንዲገዛ እና ወዘተ ለሆኑ እንቅስቃሴዎች ተቋራጩ ቅድመ ክፍያ ይከፈለዋል። 🏷በአብዛኛው የ ሃገራችን የዉል ሰነድ ላይ የምንመለከተው ቅድመ ክፍያ የዉሉን ዋጋ 20 ወይንም 30% ነው። ለ ምሳሌ ፕሮጀክቱ 100,000,000 ከሆነ እንዴት አሰሪው 20,000,000 ብር አምኖ ለተቋራጩ ዉል ስለገቡ ብቻ ይሰጠዋል። እንግዲህ የኮንስትራክሽን ዉሎች መሰረት ተደርገው የሚዘጋጁት የሃገሪቱን ህግ መሰረት በማድረግ ነው የሃገሪቱ ህግ ደግሞ አለማችን ላይ በሰፊው ከምንጠቀመው የኮንስትራክሽን ህግ የወጣ ነው። አንዳንዴ ቀጥታም ልንጠቀመው እንችላለን። ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ scc & gcc የሚባሉ ህጎች ዉላችን ላይ አሉ። - So ተቋራጩ ለሚወስደው ቅድመ ክፍያ እኩል የሆነ ማስያዥያ ለ አሰሪው ማቅረብ ይኖርበታል። - FIDIC RED book 2017( GCC )የምንለው ከዚህ የተቀዳ ነው። በአንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ስለ ቅድመ ክፍያ ማስያዝያ እንዲህ ይላል። - ስራ ተቋራጩ ለሚወስደው የቅድመ ክፍያ በወሰደው መጠን ልክ ማስያዝያ ለ አሰሪው ማቅረብ ዪጠበቅበታል ኮፒ ደግሞ ለ እንጂነሩ/ ሳይተ ሱፐርቪሶሩ መስጠት ግዴታ አለበት - ይህ የቅድመ ክፍያ ማስያዝያ የሚቀርበው ሃገር ውስጥ ህጋዊ ሰዉነት ካለው የፋይናንስ ተቋም ሲሆን እና አሰሪው የተስማማበት መሆን ይጠበቅበታል። ይህ የፋይናንስ ተቋም ዋስትናውን የሚሰጠው የዉሉ ወይንም የጨረታ ሰነዱ ላይ በተዘጋጀው ናሙና ቅጽ መሰረት ዪሆናል አንዳንዴም ባንኩ በራሱ ቅጽ አቅርቦ አሰሪው የተስማማበት ከሆነ its okay። - ስራ ተቋራጩ የቅድሚያ ክፍያ ዋስትናው ቅድመ ክፍያውን ከፍሎ እስኪያጠናቅቅ ድረስ ተቀባይነት እና ተፈፃሚ ያለው መሆኑን ያረጋግጣል ነገር ግን ያስያዘውን የገንዘብ መጠን ተቋራጩ በከፈለው መጠን ደረጃ በደረጃ ሊቀንስ ይችላል። የከፈለው መጠን እና የሚቀረው መጠን በክፍያ የምስክር ወረቀት ላይ ይገለጻል። - የቅድመ ክፍያ ዋስትናው የሚያበቃበት ጊዜ ተጠቅሶ ከሆነ እና ተቋራጩ የወሰደውን ቅድመ ክፍያ ዋስትናው ከመጠናቀቁ 28 ቀን በፊት አጠናቆ ሳይከፍል የሚቀር ከሆነ 1. ተቋራጩ ቅድመ ክፍያው እስኪከፈል ድረስ የዚህን ዋስትና ትክክለኛነት ያራዝማል ቀኑን ያራዝመዋል ማለት ነው። 2. ተቋራጩ ይህንን የማራዘምያ ማስረጃ ወዲያውኑ ለአሠሪው ያቀርባል ለኢንጅነሩ ወይንም ሱፐርቫይሰሩ ግልባጭ ይዞ 3. አሠሪው ይህንን ማስረጃ ዋስትና ከማለቁ ከ7 ቀናት በፊት ካልተቀበለ፣ አሠሪው ያልተከፈለውን የቅድሚያ ክፍያ መጠን በዋስትናው መሠረት የመጠየቅ መብት አለው። - ተቋራጩ የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና በሚቀርብበት ጊዜ ማመልከቻ ወይንም በደብዳቤ መልክ ለወሰደው ቅድመ ክፍያ ማስያዣ እንዳቀረበ መግለጽ ይጠበቅበታል።

የ ኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ…

#ነዳጅ ከዛሬ መስከረም 21 ቀን 2018 ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ፦ - የቤንዚን - የነጭ ናፍጣ - የኬሮሲን - የቀላል ጥቁር ናፍጣ - የከባድ ጥቁር ናፍጣ መሸጫ ዋጋ በመስከረም ወር ሲሸጥበት በነበ
#ነዳጅ ከዛሬ መስከረም 21 ቀን 2018 ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ፦ - የቤንዚን - የነጭ ናፍጣ - የኬሮሲን - የቀላል ጥቁር ናፍጣ - የከባድ ጥቁር ናፍጣ መሸጫ ዋጋ በመስከረም ወር ሲሸጥበት በነበረው እንዲቀጥል መወሰኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል። የአውሮፕላን ነዳጅ የችርቻሮ መሽጫ ዋጋ በአዲስ አበባ ከተማ በሊትር 120 ብር ከ10 ሳንቲም እንዲሆን በመንግሥት መወሰኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።