Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 346 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 649,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 354 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 346 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -112,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 39.43%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.21% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 656 次浏览,首日通常累积 1 752 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 346
订阅者
-724 小时
-387 天
-11230 天
帖子存档
14 341
‹‹የአማራ ክልል መንግሥት›› ለሚባለው ስብስብ‼️
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
አሁን ላይ አንተን ማብጠልጠሉ ጠቀሜታ እንደሌለው በማመን ብሎም መንግሥታዊ አደረጃጀቱም ሆነ በጀቱ ያለው በእጅህ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ የሚከተሉትን ነገሮች ተግባራዊ ታደርግ ዘንድ እጠይቃለሁ፡፡
➔ለቃቅመህ ያሰርካቸውን ወይም የምታሳድዳቸውን ፋኖዎች ነጻነታቸውን ሰጥተህ እንዲሁም ያባረርካቸውን የጦር መሪዎች ይቅርታ ጠይቀህ ወገናቸውን የሚታደጉበትን እድል ብትፈጥርላቸው….
➔እንደ በላይ አካል የምትቆጥረውን የፌደራል መንግሥት በሙሉ አቅሙ የሚነሳበትን ወቅት መጠበቁን ትተህ ከእጅህ ላይ ያለውን ጸጋ ለትግል ብታውለው፤
➔ከወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ አፋር ግንባር መዝመታቸው ወይም ደግሞ ፕሬዝዳንት ሙሥጠፌ በጦር ግንባር መገኘታቸው ያስገኘውን ፋይዳ ቀላል አይደለምና ከመላው ከፍተኛ አመራር ጋር በጦር ግንባር ተገኝተህ ሕዝብን የማነቃቃት ተግባር ብትፈጽም፤
➔የትኛውም ጠቃሚ ምክር ያለ መንግሥታዊ መዋቅር ምድር ሊነካ አይችልምና ከተሞች ከተወረሩና ከወደሙ በኋላ ነጻ ለማውጣት የሚከፈለውን መስዋዕትነት ጥቃትን ለመከላከል ይውል ዘንድ ያለህን አቅም ሁሉ አሟጥጠህ ብትጠቀም፤
➔በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኝ እያንዳንዱ ወረዳና ቀበሌ በዘመቻው ይሳተፍ ዘንድ የዘማች ኮታ ወስነህ ወደ ታችኛው መዋቅር ብታወርድ….
➔በአውራጃ ደረጃ ወስነህ የወረራ ወረፋ ጠባቂ ያደረግከው ሕዝብ በአማራነት ማዕቀፍ ወደ ተወረሩ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ የመጣበትን ሕዝባዊ ማዕበል ይመክት ዘንድ ብታመቻችለት…
➔በትግል ወቅት በጦር ሜዳ ተገኝቶ ከመተኮስ ባልተናነሰ መልኩ በክልሉ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ የሕዝብን ሞራል መቀስቀስ፣ ስንቅ መለገስ፣ ተተኳሽ ማድረስ… አስፈላጊ በመሆኑ የወገኑ ሕልውና የሚገደው ሁሉ ትግሉን ይደግፍ ዘንድ ጥሪ ብታደርግ…........
የሚሉ ጥያቄዎችን ሳቀርብ በየትኛው የትግል ቦታ ላይ ተገኝቼ የትኛውንም አይነት ወገናዊ ግዴታዬን ለመወጣት ዝግጁ መሆኔን በመግለጽ ነው፡፡
Share
14 341
ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጋር ጥምረት የፈጠረው ሕዝባዊ ጦር እስከ መጨረሻው ምዕራፍ መጓዝ ከተፈቀደለት እንደ አረም የክረምትን ወቅት ጠብቆ የሚመጣውን አሸባሪ ከትግል ሜዳ የማሰናበት አቅም አለው።
14 341
“ምሬ የዚየስ ልጅ፥ መብረቅ መታጠቂያው
መንጋጭላ የሚያረግፍ፥ ምላጩን ሲስበው”
አሳዬ ደርቤ
አንዳንዱ ጥቃት ፈሪና ተሸቆጥቋጭ ዜጎችን ሲፈጥር አንዳንዱ ደግሞ የተደበቁ ጀግኖችን ፈልፍሎ ያወጣል፡፡ በመሆኑም ወራሪው መንጋ በርካታ ንጹሐንን ሰውቶ ቢሄድም በዚያው ልክ ደግሞ የማይሰበሩ ጀግኖችን አስነስቷል፡፡ በወረራ በቆየባቸው ጊዜያት በርካታ መሠረተ ልማቶችን አፈራርሶ፣ የዜጎችን ደም አፍስሶና ሴቶችን አርክሶ ከፍተኛ ጉዳት ቢያደርስም አማራን ለማጥፋት ወስኖ በፈጸመው ወረራ “ፋኖ” የተባለ ሞት አይፈሬ የወጣቶች አደረጃጀት ቀስቅሷል፡፡
ከእነዚህም የአማራ ፋኖዎች መሃከል የምሥራቅ አማራ ፋኖ አንዱ ሲሆን በሕልውና ዘመቻው ወቅት በአምሥት የራያ ግንባሮች ጥቂት ክላሽ ታጥቆ በክትክታ ዱላና በሳንጃ የጀመረውን ትግል የፋሽሽቱን ጦር እየደመሰሰ ወደ ክላሽና ስናይፐር ማሳደግ ችሏል፡፡ ዲሽቃና ታንክ በክላሽ ማርኳል፡፡ የወራሪውን ምሽግ ሰብሮ በመግባት በመከላከያ ሠራዊቱ የሚታወቁ ግዙፍ ጀብዱዎችን ፈጽሟል፡፡
ይሄውም በወሎ ምድር የበቀለው የምሥራቅ አማራ ፋኖ፡-
“ምሬ የዚየስ ልጅ- መብረቅ መታጠቂያው
መንጋጭላ የሚያረግፍ- ምላጩን ሲስበው” ተብሎ በተዜመለት በራያው መብረቅ በሻለቃ ምሬ ወዳጆ የሚመራ ሲሆን ጥቂት ፋኖዎችን ይዞ በጀመረው ትግል በርካታ ጀግኖችን ማፍራትና እልፍ አእላፍ ጀብዱዎችን መሥራት ችሏል፡፡
(ከላይ ያለው ቁራጭ ታሪክ "እልልታ የዋጠው እሪታ" ከሚለው መጽሐፋችን ተቀንጭቦ የወጣ ሲሆን፤ ዛሬም ምሬ ወዳጆ የማይታሰበውን ከበባ ሰብሮ ሌላ ጀብዱ መፈጸሙን በመስማቴ ላጋራችሁ ወደድኩ።)
14 341
ወራሪውን ኃይል "ላሳልፍህ" ከማለት ባለፈ "አዝዬ ላድርስህ" ብትለው እንኳን አራት ኪሎን አይመኛትም። ዒላማው ያነጣጠረው ዶክተር ዐቢይና ዶክተር ይልቃል ላይ ሳይሆን አንተ ላይ ነው!!
14 341
ለወገኔ
▬▬
➔ተፈናቃይ ከመባል ታጋይ መሆንን እንምረጥ።
➔ከተዋረደ ሕይወት ይልቅ የተከበረ መስዋዕትነት እናስበልጥ።
➔መሆን ባለበት ፈንታ መሆን የሌለበት ሲሆን ያየነው በመንግሥት እጦትና በእኛ ቸልተኝነት መሆኑን እንገንዘብ።
➔በባዶ እግሩ የሚሄድ ገበሬ አስተምሮ ለቁም ነገር ያበቃችሁ ሁሉ ወገንን ከእረፍት አልባነት የሚታደግ የትግል ስልት ቀይሱ።
➔በቆቦ የተጀመረውን ወረራ ወደ ቀያችን ማዛመትም ሆነ ቆቦ ላይ ማስቀረት የምንችለው እኛ መሆናችንን አስታውሱ።
➔የሐይማኖት አባቶች መላው ሕዝብ በባርነት ላይ ይሸፍት ዘንድ ቀስቅሱ።
➔ፋኖዎች የወላጆቻችሁን ክብር ለማስጠበቅ ተንቀሳቀሱ። እኅቶች ስንቅ አድርሱ። ባለሃብቶች የአቅማችሁን ለግሱ።
በተረፈ ትግሉ ባልተጀመረበት ሁኔታ ተስፋ መቁረጥን እና ሽንፈትን የምታከፋፍሉ ወገኖች ሱሪያችሁን ለእኅቶቻችሁ ሰጥታችሁ ቀሚሳቸውን ተዋሱ።
14 341
በስምምነት ስለሚጀመር ጦርነት...‼️
(አሳዬ ደርቤ)
➔አንዳንድ ጦርነቶች በተፋላሚዎች ውይይትና ስምምነት ይቋጫሉ፡፡
➔አንዳንድ ጦርነቶች ደግሞ በተፋላሚዎች ስምምነት ይጀመራሉ፡፡
ማለትም....
ሁለት ተፈላሚ ኃይሎች በድብቅም ሆነ በግልጽ ወደ ውይይት ከመጡ በኋላ ቅድመ ሁኔታዎችን ያቀርባሉ፡፡ ሆኖም ግን በአንደኛው ተፋላሚ በኩል የሚቀርቡ ቅደመ ሁኔታዎች በሌለኛው ወገን ተቀባይነት ካገኙ በኋላ ጥያቄዎቹን በሰላማዊ መንገድ ተፈጻሚ ለማድረግ የማያስችሉ ውጫዊ ሁኔታዎችና ሕዝባዊ ፈተናዎች ያጋጥማሉ፡፡
ያን ጊዜም በሁለቱ ወገኖች ስምምነት በቃል ትዕዛዝ ተፈጻሚ መሆን የማይችሉትን ቅድመ ሁኔታዎች በአፈ-ሙዝ ለመስጠት የሚያስችል የይስሙላ ጦርነት እንዲጀመር ይደረጋል፡፡
እንዲህ ያለው ዘመቻ ታዲያ ውጤቱ ከጦርነቱ በፊት የሚወሰን በመሆኑ እስከሆነ ርቀት ድረስ ተሸናፊ ለመሆን ፈርሞ የገባውን አካል የትኛውንም አይነት ድጋፍ ብታደርግለት እንዲያሸንፍ ማድረግ አትችልም፡፡
የጦር መሣሪያ ጭነው ወደ ጠላት ቀጠና የሚገቡ አውሮፕላኖች መኖራቸውን፣ አሸባሪው ቡድን መጠነ ሠፊ ጥቃት ለመሰንዘር መዘጋጀቱን... የሚገልጽ መረጃ ብትሰጠው እንኳን መረጃህን አስተባብሎና አንተን አባብሎ ያስተኛኻል እንጂ የተደገሰውን ጥቃት ያጨናግፈዋል ተብሎ አይታሰብም።
ከዚህ ይልቅ በስምምነት የሚጀመሩ ጦርነቶችን ውጤት መቀየር የሚቻለው የእራስን ሕዝባዊ ኃይል ተጠቅሞ እራስን መከላከል ሲቻል ነው፡፡ እስከሆነ መዳረሻ ድረስ የአባራሪ እና ተባራሪ ውል ከፈረመ መዳፍ ድል በመጠበቅ ፈንታ የእራስን ትግል ለኩሶ የጨዋታውን ውጤት በመቀየር ነው፡፡
በየተራ የምንወረርበትን እለት በመጠባበቅ ፈንታ ወደ ተወረሩት ወገኖችና አካባቢዎች በጋራ በመንቀሳቀስ ነው፡፡ የአማራን ሕዝብ እና ክልል የመታደጊያው ትክክለኛ ቦታ ሰሜን ወሎ እና ወልቃይት ዳርቻ ላይ መሆኑን አውቀን የጋራ ጥቃታችንን አዝሎ የመጣብንን ጠላት በየተራ ከመቀበል ይልቅ በጋራ መከላከል ስንችል ነው፡፡
14 341
ያንተ ወገን ድንበር አልፎ ሌሎችን ሲያጠቃ ገለልተኛ መሆን አይከብድም። በሕዝባዊ ጎርፍ ወገንህን የሚጨፈጭፍ አሸባሪ ሲመጣ ግን
"አትንኩኝ" ብሎ በጋራ መነሳት እንጂ "ምን አገባኝ" ማለት አይታሰብም!
14 341
"ለሰብአዊ አገልግሎት የሚውል 570ሺ ሊትር ነዳጅ በህውሓት ተዘረፈ" ተብሎ በተመድ በኩል የተሰጠውን መግለጫ "ለህውሓት ተላለፈ" ብዬ አነበብኩት። "የተባበሩት" የሚባለው የነዳጅ ማደያ የUN ኑሯል ለካ?😆
14 341
ከብልጽግና እጅ ሰላም የሞላው ሕይወት ቀርቶ ድል ያለው ጦርነት ማግኘት አይቻልም‼️
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
አንዳንዱ ሥርዓቶች በሰላም እጦት ያሰቃዩኻል፡፡
እንደ ብልጽግና ያለ መንግሥት ግን በሰላም ተደላድሎ ለመኖር ይቅርና እራስን ለመከላከል የማያስችል መሰናክል ደርድሮ ተፈናቃይ ያደርግኻል፡፡ ሰላምን ብቻ ሳይሆን ጦርነትንም የማይቻል ያደርግብኻል፡፡
በዚህም መሠረት የአማራ አርሶ አደር ፊቱን ወደ ሰላም እና ልማት አዙሮ ማሳውን መንከባከብ ሲጀምር እንስሳትን የሚረሽን፣ ሴቶችን የሚደፍር፣ ጥሪትን የሚያወድም…. ጠላት የከሰብ ወቅት ጠብቆ ይመጣበታል፡፡
ያን ጊዜም ከማሳው እና ከቀየው የሚያፈናቅል ጠላት አሻግሮ እያዬ ግብር የሚከፍለውን መንግሥት ሲጣራ ‹‹የሰብል ጉብኝት ላይ ስለሆንኩ አትረብሸኝ›› በማለት ያለምጥበታል፡፡ ልክ እንደዚሁ ሁሉ ከብልጽግና እጅ የወደቀው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም በወታደራዊ ሳይንስና በእራሱ የትግል ሰሌዳ የሚያዋጋው ባለቤት አጥቶ ድሮን የማይበርበትን፣ መንግሥት ያንቀላፋበትን… ጊዜ ጠብቆ ጥቃት በሚፈጽም ሽፍታ መክፈል የሌለበትን መስዋዕትነት ሲከፍል ታይቷል፡፡
ከብዙ ጉዳት በኋላም ይሄው ሕዝብ እራሱን እና ልጆቹን አደራጅቶና ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ተቀናጅቶ እንዲሁም የተወረረ ቀየውን በከፊል አጽድቶ ከመከላከል ወደ ማጥቃት ሲሸጋገር በጠላት አፈሙዝ የተጀመረው ውጊያ በመንግሥት ትዕዛዝ እንዲቆም ይደረጋል፡፡
ከዚያም….
ተመትቶ የሸሸው ጠላት በማይወረርና በማይደፈር ክልሉ ውስጥ ሆኖ ከአየር ጥቃት የሚታደገው የክረምት ወቅት እስኪመጣ ድረስ ለሌላ ዙር ጦርነት እራሱን ሲያዘጋጅ ይከርማል፡፡
ለጦሩ ስንቅ የሚሆን ስንዴ እና ነዳጅ ከፌደራል መንግሥት እስኪላክለት ድረስ ስለ ድርድር እያወራ በርካታ ጦር ያሰለጥናል፡፡
ውጫዊ ኃይሎች በአውሮፕላን የሚጭኑለትን ጥይትና ዱቄት ያከማቻል፡፡ ከዚያም ያረቀቀውን የትግል ካሌንደር መሠረት አድርጎ የድል ባለቤት ያደርግልኛል በሚለው ግንባር ጦርነትና ወረራ ይለኩሳል፡፡
የሰላም ሕይወትን መግፋት ቀርቶ በቅጡ መዋጋት የተነፈገው የአማራ ሕዝብ ግን ከጠላት ወረራ ነጻ በወጣ ማግስት ፋኖ ልጆቹን የሚያሳድድ መንግሥት ይመጣበታል፡፡
በእራሱ የትግል ሰሌዳ የሚመራው የሽብር ቡድን ደስ ባለው ግንባር ወረራ ፈጽሞ ወደ እርሱ ሜዳ እስኪመጣ ድረስ ፋኖዎችን የሚያፍስ እና ለወራሪዎች ስንቅ የሚያደርስ የጭነት መኪና ሲቆጥር ይውላል፡፡
ጅምላ ጨራሽ መሳሪያ በአውሮፕላን የሚጫንለት ጠላት ባለበት ሁኔታ ‹‹ጥቁር ክላሽ ታጥቀኻል›› ተብሎ ሲንገላታ ይከርማል፡፡ ሰላማዊ ሕይወትን ብቻ ሳይሆን ለጦርነት መዘጋጀትን ተነፍጎ በክልሉና በፌደራሉ መንግሥት ሲዋከብ ይሰነብታል፡፡ ከዚያም ከወንዝ ማዶ ከባድ መሳሪያ የሚተኩስና ወደ እርሱ ቀዬ የሚገሰግስ ጠላት ተመልክቶ መንግሥትን ፍለጋ ዐይኑን ሲያዞር ብቻውን ቁሞ እራሱን ያገኘዋል፡፡
ባንድ በኩል ያለ ጦርነት መኖር የማይችል ጠላት እጁን ስቦ ወደ ትግል ያስገባዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የማሸነፍ ፍላጎት የሌለው መንግሥት በትግሉ እኩሌታ ላይ እግሩን ወልክፎ ያለ ድል ያስቀረዋል፡፡
እናም የዚህን ቁማርተኛና ዳተኛ መንግሥት ባሕሪይ ስትታዘብ በእነ በላይ ዘለቀ ሲመራ የነበረው መንግሥት አልባ ትግል ይናፍቅኻል፡፡
14 341
7.5.1 ወሎ ላይ የጎመራው የአማራ ሕዝብ አንድነት
▬▬▬▬▬▬▬▬
ትሕነግ እና ኦነግ ወሎ ምድር ላይ ጥምረት ፈጥረው ወደ ሸዋ ሲዘምቱ እንደታየው ሁሉ…. የጎንደር፣ የሸዋ፣ የጎጃምና የወሎ አማራ ፋኖዎችም ጥምረት የፈጠሩት የቤተ-አማራ ማሕጸን በሆነችው የወሎ ምድር ነበር፡፡
በዚህም መሠረት ከጎንደር የተነሳው የአማራ ፋኖ…
‹‹ከራያ አንስቶ ፥ እስከ ሑመራ
እርሳስ ጠርጣሪ ፥ እንደ ሽንብራ›› .... በሚል ፉከራ ደሴ ከተማ ሲገባ፣ የሸዋ አማራ ፋኖ እና ሚኒሻም አማራን በጠላትነት የፈረጀውን ወራሪ ማስቆም የሚቻለው በአማራነት ማዕቀፍ ውስጥ በአንድነት በመቆም መሆኑን ተረድቶ ወደ ወሎ ዘምቷል፡፡
ከሰሜን ወሎ ዞን ወደ ደቡብ ወሎ ለተፈናቀሉ ወገኖቹ ማኛ ጤፉን፣ ስንዴና በርበሬውን ሲጭን የሰነበተው የጎጃም አማራም…
“ከዚያ ወሎ ምድር- የሚያጭዱት አዝመራ
የሚረግፍ እንስሳ - በጥይት፣ በካራ
የሚወድመው ጥሪት
የሚከስመው ሕይወት - በማንም ወንበዴ
ከወሎ እስከ ጎንደር - የኔ አይደለም እንዴ?
ደህና ሰንብት ዓባይ - ጣና ቻው ቻው በቃ
ከእንግዲህ ይበቃል - መውደም በፈረቃ” ... በሚል ቁጣ በእነ ዘመነ ካሴና ማስረሻ ሰጤ የሚመራ ፋኖውን ካዘመተ በኋላ የቤተ-አማራ ማሕጸን በሆነችው የወሎ ምድር ላይ እነ ኤፍሬም አጥናፉን ገብሮ የአማራን አንድነት በደሙ አጽንቷል፡፡
(እልልታ ከዋጠው እሪታ የተቀነጨበ)
14 341
እልልታ በዋጠው እሪታ እሸቴ ሞገስ ሲታገስ
….ከዚያ በማስከተልም ሳላይሽ የደረሰው ጠላት የአሰፋ ታዬን ግቢ ወረረው፡፡ አንበሳው እሸቴም ልጁን ጠርቶ እንደዚህ አለው፡፡
“እኔን ቀድመው ከጣሉኝ ለማምለጥ ሞክር፤ አንተን ከነጠቁኝ ግን ከኋላህ ስለምታገኘኝ እንዳትሸበር!››
ልጅም መለሰ…
“መግደል እና መሞት-
የምርጫ ጉዳይ ነው- ለእራስ የሚለገስ፤
እነሱም ውስጥ አለ-
የሚንጠባጠብ ደም- የሚቆም እስትንፋስ፤
እናም አባቴ ሆይ-
የከበበንን ሞት- ለቅመን ለመጨረስ፤
በምኒልክ ተስፋ-
እግዚአብሔርን አምነህ- ክላሽህን አጉርስ››
እናም ሁለት ሆነው የአሰፋ ታዬን ግቢ የወረረውን ጠላት ገጠሙት፡፡ መንታ ሆነው መላዕከ ሞትን ተጋፈጡት፡፡
ተኩሱ ተቀጣጠለ፡፡ አባትና ልጅ የመሸጉበት ግቢ በጥይት ተነዳደለ፡፡
የአቶ እሸቴ እዳይት የሚበጥስ ተኩስ አምሥት ወራሪን ጣለ፡፡ በይታገሱ ሽጉጥም አንድ ሰለባ ታከለ፡፡
ይሄንንም ጀብዱ ከፈጸሙ በኋላ ምድር ላይ ከተጋደሙት ወራሪዎች መሃከል የአንዱን ትጥቅ በማንሳት አባትና ልጅ ክላሽ ታጠቁ፡፡ ተኩሱ በበረታ ጊዜም የአሰፋ ታዬን ግቢ ለቀቁ፡፡
አንበሳውና ደቦሉ ከማሽላ ማሳ መግባታቸውን የተረዳው ወራሪ ሥድስት ጓዶቹን የቀሙትን ጀግኖች ሕይወት ሊቀማ ሲንደረደር ይታገሱ በማረከው ክላሽ ሦስቱ ወራሪ መንገድ ላይ ከሰመ፡፡ የ31 ዓመቱ ወጣትም ከአባቱ ጎን ሆኖ በታላቅ ጀግንነት እየተዋጋ ሳለ ጥይት የጨረሰ ይመስል ተኩሱን አቆመ፡፡
ያን ጊዜም አቶ እሸቴ ዐይኑን ከዒላማው ላይ አንስቶ ወደ ልጁ ሲልከው ይታገሱ በክላሹ ፈንታ ደረቱን ይዞ ተመለከተ፡፡ ጥይቱን ሳይሆን የምድር ቆይታውን መጨረሱን የተረዳው አባትም፣ የልጁን ጣዕር ተጋርቶ ቃተተ፡፡
ሊያለቅስ ቃጣው፡፡ ልቡ ግን…
“ነውር ነውና- ለጀግና ማልቀስ
እንባህን ውጠህ- ደሙን ቶሎ እበስ” በማለት ገሰጸው....
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
