Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 346 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 649,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 354 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 346 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -112,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 39.43%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.21% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 656 次浏览,首日通常累积 1 752 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 346
订阅者
-724 小时
-387 天
-11230 天
帖子存档
14 341
ሰላም ትባላለች፡፡
ታናሽ እኅቴ ናት፡፡
‹‹እልልታ የዋጠው እሪታ በአማራ ክልል በሚገኙ የተወሰኑ ላይብረሪዎች ውስጥ ተደራሽ ሆኖ መነበብ አለበት›› በሚል ውሳኔ የአምሳ መጽሐፍት ወጪ ሸፍናለች ፡፡ እናም ውዷ እኅቴ ላደረገችው አበርክቶ እያመሰገንኩ የራሴን አምሳ መጽሐፍት ጨምሬ ለተወሰኑ ላይብረሪዎች የማደርስ ይሆናል።
አከፋፋዮች
▬▬▬▬
ጃፋር (ለገሐር)
ጦቢያ (ካሳንቺስ)
ሀሁ (ሜክሲኮ)
ጌታቸው መጽሐፍት (ፒያሳ)
14 341
እልልታ የዋጠው እሪታ ላይ ስለ ጄኔራሉ ከተጻፈው
....በሕይወት ካሉት የብአዴን አመራሮች በላይም በሕዝብ ልብ ውስጥ ሕያው ሆኖ ምሥሉ ከወጣቶች ደረትና የፌስቡክ አካውንት ላይ ሲለጠፍ ይውላል፡፡ ኮረዶች ስለ ጀግንነቱ ይዘፍናሉ፡፡ ጎረምሦች “በእኛ ዘመን የተከሰትክ አጼ ቴዎድሮስና አስራት ወልደየስ ነበርክ” እያሉ ሥሙን ከፍ ከፍ ያደርጋሉ፡፡
በእርግጥም ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ከአጼ ቴዎድሮስ ጋር የሚመሳሰል ነገር ነበረው፡፡ በዚህም መሠረት አገሩን እንጂ እራሱን ሆኖ የማያውቀው ባተሌ ንጉሥ ምድራዊ ኑሮ፡-
“እንደው በዘልማድ -
ንጉሥ አሉት እንጂ - ካሳ መች ነገሰ
የአገሬው ጭሰኛ -
መች እንደሱ አረረ - መቼ እንደሱ ጨሰ?
አንድ ነው ይሉታል- ለእናቱ ቴዎድሮስ
ኢትዮጵያ ናት እንጂ - አንድ ሁኖ አያውቅ እሱስ፡፡
አገሩን ሊያዋኽድ - ከወታደሩ ጋር - ቀን ሌሊት ሲባክን
ባንዱ አጥሮ ሲመለስ- ባንዱ እያፈረሱ- እየናዱት ሕልሙን
ከግዙፍ ሐሳብ ጋር -
በአሳቻ ቦታ ላይ - ያለ ወቅት ተወልዶ
የቴዎድሮስ ነገር
አንዳንድ ቀን ብዙ፣ አንዳንደዜ ባዶ” በሚል ስንኝ ሊገለጽ እንደሚችለው ሁሉ በተመሳሳይ መልኩ ከግል ምቾት ይልቅ የሕዝብ ስጋት ተጋርቶ፣ ከወራዳ ሕይወት ይልቅ የክብር ሞት ጥፍጥናውን ተረድቶ፣ በአሽከርነት ከሚገኝ ቪ8 ይልቅ የጀግና ቃሬዛን መርጦ፣ ለሕዝብ ሲል የተሰዋው የብ/ጄ አሳምነው ጽጌ ሕይወትም
የቤተሰቡን ጥቅም -የግል ምቾቱን -ሳቅ ደስታውን ትቶ
የሕዝቡን ወረርሽኝ -የወገኑን ስቃይ - ጥቃቱን ተጋርቶ
አገሬው ሲተኛ-በውድቅ ሌሊት- እራሱን አንቅቶ
ከጠላት ቀለበት
የወደቀ ሕዝቡን -ከከበባ ሊያድን
ወገን ሕያው ሊያደርግ
መድሃኒት ሲቀምም-ተጎንጭቶ ሞቱን
አሳምን ያረፈ
እንደ አጼ ቴዎድሮስ-እንደ አስራት ወልደየስ- ሳይኖረው ሕይወቱን” ተብሎ ቢገለጽ ግነት አይኖረውም
14 341
ለጨዋዎች የተከለከለ ጨዋታ!!
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
በአማራ ጉዳይ ተመስጬ እንደ አባወራ የሚጠበቅብኝን ተጋድሎ እርግፍ አድርጌ መተዌን ብርዱ አስታውሶኝ ከጠባብ ክፍሌ ስወጣ... እሜቴ የመኝታ ቤቱን በር እንደ ወሎ መስመር ጥርቅም አድርጋው ተኝታለች፡፡
በዚህም ሁኔታ ተገርሜ ‹‹ሕዝብ አነቃለሁ የሚል አክቲቪስት ያገባች ሴት በሦስት ሰዓት መተኛት የቻለችው እንዴት ነው›› ብዬ መጠየቅ ስጀምር… በእሜቴ ሞባይል የተከፈተው ብሎም እንደ ክላሲካል ሙዚቃ ታዳሚውን አባብሎ የሚያስተኛው ቻናል ‹‹በኢትዮጵያ መሬት ላይ የሚታየው መረጋጋት ከቀላጩ ዘይት የላቀበት ምክንያት›› የሚል ትንታኔ ያቀርብ ጀመር፡፡
እንዲያም ሆኖ ታዲያ በዚህ ታሪካዊ ምሽት ላካሂደው ያሰብኩት ኦፕሬሽን በምንም አይነት ምክንያት ሊሰረዝ የሚችል ባለመሆኑ መዳፌን ጨብጬ በሩን ሳንኳኳ ቆየሁ፡፡ እሜቴ ግን ምንም አይነት ምላሽ ባለመስጠቷ ‹‹ከእንቅልፍም አልፎ ግጭት ቀስቃሽ ነው›› እየተባለ በካድሬዎች የሚብጠለጠለውን ሚዲያ ድምጹን ከፍ አድርጌ ስጋብዛት ከመኝታዋ ነቅታ ‹‹ማነው?›› የሚል ጥያቄ አቀረበች፡፡
ያን ጊዜም አንዱ የሶሻል ሚዲያ ባላንጣዬ ያስታቀፈኝን ማዕረግ እንደወረደ ተቀብዬ ‹‹እኔ የስውሩ መንግሥት አክቲቪስት የሆንኩ ውዱ ባለቤትሽ ነኝ›› ብዬ ስመልስላት ‹‹እንቅልፍ ላይ ስለሆንኩ አትረብሸኝ›› በማለት መለሰች፡፡
‹‹የአዲስ አበባ ነዋሪ ይመስል እንቅልፍ አላበዛሽም?››
‹‹የአዲስ አበባ ነዋሪ መሆኔ ቀረ እንዴ?››
‹‹አልሰሜን ግባ በለው! የምንኖርበት ሰፈር ከጭሰኛው አካባቢ ተገንጥሎ ወደ ተረኛው መካለሉን አልሰማሽም እንዴ? ይልቅ በሩን ክፈቺውና 'ሲንጃላዳ' እንባባል››😆
‹‹ባልና ሚስት እቅፍቅፍ ብለው በሚተኙበት የክረምት ወራት ክፍልህን ዘግተኽ እንደከረምክ ሁሉ እኔም ክፍሌን ዘግቼ ስለተኛሁ አትረብሸኝ››… እሜቴ ተነጫነጨች፡፡
ይሄውም ቅሬታዋ ተገቢ መሆኑን በማመን ‹‹በሦስት እግሬ ተንበርክኬ እየለመንኩሽ ስለሆነ በሩን ክፈቺውና በመሀከላችን የተፈጠረውን ችግር በአልጋ ዙሪያ ድርድር እንፍታው›› ስላት ‹‹ለሚስቱ ጊዜ ከማይሰጥ ሰው ጋር በትዳር መኖር ስለደከመኝ ምንም አይነት ድርድር አልፈልግም›› በማለት መለሰች፡፡
ያን ጊዜም ‹‹በትዳር ተሳስረን መኖር ከደከመሽ በክላስተር ተደራጅተን መኖር ስለምንችል ክፈቺውና እንመካከር›› ከሚል ወቅታዊ ሐሳብ ጋር በሩን መደብደብ ስጀምር… መኝታ ቤቱን ከፍታ ‹‹አጀንዳህን ማቅረብ ትችላለህ›› በማለት ተናገረች፡፡
ወደ ድርድር ከመግባታችን በፊትም "ግድባችንን እንሙላ›› የሚል ቅድመ ሁኔታ ሳቀርብ ‹‹መቅደም ያለበት ሙሊቱ ሳይሆን ውይይቱ ነው›› በማለት ተቃወመች፡፡
ያንጊዜም ‹‹በርካታ ላብ ያፈሰስኩበትን ግድብ ከእኔው በሚመነጭ የተፈጥሮ ሀብት ለመሙላት ምንም አይነት ውይይት አያስፈልግም›› በሚል ቁጣ የሕግ ማስከበር ዘመቻ አውጄ እንደ ብአዴን አፈንኳት፡፡
ከዚያም የተርባይን ተከላ አከናውኜ ለታችኞቹ ተፋሰስ አገራት መትረፍ የሚችል እምቅ ኃይል ማመንጨት ስጀምር… ከስራችን ካለው ብሎክ ውስጥ የምትኖረው ኮረዳ ‹‹በተርባይን ዘመን የናፍጣ ጄኔሬተር ታቅፌ የማድረው እስከ መቼ ድረስ ይሆን?›› እያለች ቀጠናውን በሚረብሽ መልኩ ከአንገቷ ተወትፎ የሚያንኮራፋ ባሏን ታማርር ጀመር፡፡😆
14 341
እልልታ የዋጠው እሪታ
▬▬▬▬▬▬▬
➔ከሥልጣን ሽግግሩ ዋዜማ አንስቶ እስካለንበት ጊዜ ድረስ በመንግሥታዊ እልልታዎች የተዋጡትን ሕዝባዊ እሪታዎች በወግና በስንኝ የሚተርከው...
➔እንደ ሕዝብ ያከሸፍናቸውን መልካም አጋጣሚዎች፣ የቀበርናቸውን ወገኖች፣ ያስተናገድናቸውን ማንነት ተኮር ወረራዎችና ጥቃቶች፣ የተከፈሉልንን መስዋዕቶች እንዳጠቃላይም ባለፉት አራት ዓመታት ተከስተው የዘነጋናቸውን አበይት ክስተቶች፣ ከምሥልና ከቃል ማስረጃ ጋር የሚያወሳው 4ኛ መጽሐፋችን ለአንባቢያን ቀርቧል።
አከፋፋይ
➔ጃፋር መጽሐፍት መደብር ለገሐር
➔ጦቢያ መጽሐፍት ካዛንቺስ
➔በተናጠል ለሚፈልጉ ደግሞ በሁሉም የመጽሐፍት መሸጫ ሱቆች ያገኙታል።
Share & Post
14 341
የወቅቱ ፖለቲካ ግላዊ ነፃነትህን የምታጣበት እንጂ ሕዝብን ነፃ የምታወጣበት አይደለም። የእራስህን ሕይወት ከመገበር ባለፈ የሕዝብን የጅምላ ሞት ማስቀረት አትችልም።
እናም እስክንድር ነጋ እንደ ስንታየሁ ቸኮል እስር ቤት ገብቶ ያለ አስታዋሽ ከሚቀር ጥሩ ውሳኔ ወስኗል። በተረፈ ከ ብረት የጠነከረ ስብዕና ባለቤት የሆነው እስክንድር ነጋ የተረኞችን ጫና መቋቋም ተስኖት ከፓርቲው መልቀቁ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለጥቅመኞች እንጂ ለእውነተኛ ታጋዮች ቦታ እንደሌለው ያመለክታል።
መልካም ጊዜ እስኬው።
ስላሳለፍከው የትግል ጊዜ አመሠግናለሁ።
14 341
ባንድ ቤት ፥ ሦስት ልደት🥤
ዛሬ… አሳዬ ደርቤ የተወለደበት እለት ነው። ከዚህ ባለፈም ሦስተኛ ልጄ "እቴጌ አሳዬ" አባቷ የተወለደበትን ቀን ጠብቃ ወደዚህች መሬት የመጣችበት እለት ነው፡፡
እንዳጋጣሚ ሆኖ ደግሞ እኔና እቴጌ በተወለድንበት ቀን ብዙ የለፋሁበትና ‹‹እልልታ የዋጠው እሪታ›› የሚል መጠሪያ የሰጠሁት አራተኛ መጽሐፌ (ልጄ) ከማተሚያ ማሽን ወጥቶ ከእጄ የገባበት ቀን ሆኗል፡፡
ይሄውም መጽሐፍ ከሥልጣን ሽግግሩ ዋዜማ አንስቶ ያሳለፍናቸውን ሒደቶች እንዲሁም የዩቲዩብ ሰበር ዜና ሆነው የረሳናቸውን ዓበይት ክስተቶች በስንኝና በወግ መልክ የሚተርክ ሲሆን በርካታ የምሥልና የቃል ማስረጃዎችም ተካትተውበታል፡፡
እናም በእኔና በእቴጌ የልደት ቀን የእስኪነጋ ድረስ፣ የጎዳናው እስኪቋጭ እና የሐሳብ ቀንዘሎች ታናሽ ወንድም የሆነውን አራተኛ መጽሐፌን አሳትሜ የሚጠበቅብኝን ወገናዊ ግዴታ በመወጣቴ ደስ ብሎኛል፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ደግሞ በሁሉም መጽሐፍት ቤቶች ውስጥ የሚገኝ ይሆናል፡፡
በተረፈ ይህ መጽሐፍ ታትሞ ለአንባቢ ይደርስ ዘንድ በተለያየ መልኩ ያገዙኝን ወዳጆቼን እያመሰገንኩ እንዲሁም መጽሐፉን የማስተዋወቅ ተግባሩን ለቀሪ ወዳጆቼ እያስረከብኩ ለእኔና ለእቴጌ ‹‹መልካም ልደት›› ፤ ለአንባቢዎቼ ደግሞ ‹‹መልካም ንባብ›› እመኛለሁ፡፡
አሳዬ ደርቤ
#Share_post
14 341
በወሎ ሥም የሚቀነቀነው ክልላዊ ጩኸት‼️
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔ደቡብ ወሎ ላይ አዲስ ዞን በመመስረት ነባሩን ዞን በኦነግ ፖለቲካ የመሰልቀጥ ምኞት ያለው፤
➔በተመሳሳይ የፌስ ቡክ ሥም የተደራጀ የኦነግና የብልጽግና የሳይበር ጦር የሚያራግበው፤
➔ሕዝባዊ መሠረት የሌለው፤
➔አማራን ወደ ማይኖሪቲ አውርዶ ኦሮ፤ሚያን ብቸኛ ማጆሪቲ የማድረግ ሕልም ያለው ፤
➔የኃይማኖት ግጭት የመፍጠር ተልዕኮ የተሰጠው፤
➔የቤተ አማራዎች እትብት መቀበሪያ ምድር ወሎ መሆኗ የተዘነጋው፤
➔ትልቁን የአማራ ዞን አንዲት ወረዳ ከማታክል ልዩ ዞን ስር የማዋል እቅድ ያለው...
እናም እንላለን...
ብልጽግና ሆይ ያሰብከው ቅዠት በእኛና በፋኖዎች ዘመን ሊተገበር ስለማይችል በክልልነት ሥም ወሎን የመሰልቀጥ ምኞትህን ጥለህ ለጉራጌ የክልልነት ጥያቄ መልስ ስጥ።
14 341
የትኛውም ፖለቲከኛ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ የአቋም መዛነፍ ሊታይበት ይችላል።
ይሄንንም ሁኔታ የተረዱ ወገኖች አስተያየት ሲሰጡ "መንጋ" እያሉ ከማንቋሸሽ ይልቅ እንደ የሱፍ ኢብራሒም እራስን መፈተሽና ይቅርታ መጠየቅ ለሁሉም ይበጃል።
በተረፈ ወዳጄ የሱፍ ኢብራሒምን ለአማራ ቀርቶ ለአገር የሚተርፍ አቅም ካላቸው ፖለቲከኞች መሀከል አንዱ እንደመሆንህ መጠን በመንግሥት በጀት ከሚታገዘውና ጥቅመኛን ካሰባሰበው የጎጠኞች መንገድ ርቀህ በያዝከው አቋም ቀጥል" ማለት እሻለሁ።
ዝንታለም አማራ‼️
14 341
አንዱ ደፋር "እባክህ አሳዬ የወሎን ጉዳይ ለእኛ ለወሎዬዎች ተውልን" የሚል ኮሜንት በተደጋጋሚ ሲሰጠኝ "የትውልድ ስፍራዬን ፌስ ቡክ ላይ ስሞላ ተሳስቼ ይሆን እንዴ?" በሚል ጥርጣሬ ፕሮፋይሌን ከፍቼ ዐየሁት።
አልተሳሳትኩም።
"ወሎ አማራ ሳይንት" መወለዴን በትክክል ሞልቻለሁ።
እናም ኮሜንቱን የሠጠኝን ልጅ አካውንት ገልጬ ስመለከት የፕሮፋይል ምሥሉ ወሎን በሚጠቀልለው የኦነግ ካርታ አሸብርቋል።
የትውልድ ቦታው ላይ ደግሞ "ወለጋ" የሚል ሥም ሰፍሯል። 😆
እኔ እምለው ግን...
የወለጋ ልጅ ከወሎ ተወላጅ በላይ በወሎ ጉዳይ ቅርብ መሆን የጀመረው ከመቼ ወዲህ ነው?
14 341
ጨለማቸውን ለሚያወዳድሩ ከንቱዎች!!
አሳዬ ደርቤ
አማራን ሊያዋርዱ ከአማራ ሕዝብ አብራክ የተወለዱ የብልጽግና ዞምቤዎች "በአማራ ክልል ከሚገኙ ዞኖች መሀከል በልማትና በእድገት ወደኋላ የቀረው የእኔ ዞን ነው›› የሚል አጀንዳ ለኩሰው የኋላ ቀርነት ውድድሩን አጧጡፈውታል፡፡
እኔ ግን እላለሁ…
አማራን ለመከፋፈል የሚውል የአበል በጀት ተመድቦላችሁ ካልሆነ በቀር በቅርቡ በሁሉም ዞኖች ስንቀሳቀስ ለብስጭት እንጂ ለምቀኝነት የሚያነሳሳ ልማት በክልሉ ውስጥ አላየሁም፡፡
በጎንደርም ሆነ በወሎ፣ በሸዋም ሆነ በጎጃም ያስተዋልኩት… እንደ ገበጣ መጫወቻ የተቆፋፈረ አስፓልት፣ ውሃ የጠማው ቧንቧ፣ መብራት የናፈቀው አምፖል፣ ግንበኛና የግንባታ ቦታ አግኝቶ የግንባታ ማቴሪያል የቸገረው ጅምር ሕንጻ፣ ጠላት ታቅፎ መንግሥት የተሰወረበት ሕዝብ፣ እንቅልፍ የለሽ ፍጥረት አዝሎ ያንቀላፋ ከተማ… እና የመሳሰሉትን ነው፡፡
ለአዲስ አበባ ካላት ቅርበትና ለኢንቨስትመንት ካላት ተመራጭነት አንጻር የተወሰነ መነቃቃት ከሚታይባት የደብረ ብርሐን ከተማ ውጭ ‹‹ምድረ ገነት›› እያልን የምናወድሳት የባሕር ዳር ከተማ እንኳን የኮብል ስቶን ዘመን ላይ ተገትራ የምትቆዝም ሆናለች፡፡ አብዛኞቹ የወሎ፣ የጎንደርና የሸዋ ከተሞችም በመሠረተ ልማት ፈንታ ‹‹የማይወረሩ ወራሪዎች›› የሚጠብቁ ሆነዋል፡፡
ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ እንደ አገር የተለኮሰው ጦርነት ‹‹የሰሜን ኢትዮጵያ›› በሚል ሥያሜ አማራ ክልል ትከሻ ላይ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ለወጣቶች የሥራ እድል መፍጠሪያ ሲውል የነበረው በጀት ለሕልውና ማስቀጠያ የሚውል መሆኑ ነው፡፡ ከብአዴን ዝርፊያ የሚተርፈው በጀት አዲስ መሠረተ ልማት ለመዘርጋት ቀርቶ በወራሪዎች የወደሙትን ተቋማት ወደነበሩበት ለመመለስ የማይበቃ መሆኑ ነው፡፡
እናስ የእራስን ጥያቄ ከማቅረብ ባለፈ በሌለ ልማት ዞንን ከዞን እያወዳደራችሁ የጋራ ውድመት ከተሸከመ ሕዝብ መሀከል ተጠቃሚ ከምትፈልጉ ከክልሉ ወጣ ብላችሁ "በክላስተርና በትራክተር የሚዘራው ስንዴ በትሕ-ኦነግ ወራሪዎች የሚፈናቀሉ ወገኖችን ፍጆታ በመሸፈን ረገድ ስላለው ፋይዳ ብታስረዱን አይሻልም ወይ?
14 341
በወሎ መስመር የሚታየው የሰሞኑ እገታ የጸጥታ ችግርን ከመፍራት የመነጨ ሳይሆን "በእለት ጉርስ እጦት የቀን ሠራተኛ ለመሆን አቅደው ከተለያዩ የወሎ አካባቢዎች የሚመጡ አማራዎች የዲሞግራፊ ለውጡን እያዛቡ ስለሆነ በዚያ መስመር የሚመጣ የትኛውም ተሳፋሪ ወደ አዲስ አበባ መግባት የለበትም" የሚል ትዕዛዝ በመተላለፉ የተነሳ ነው።
14 341
➔አገር የማፍረስ ሂደቱን አጋምሰውት ስለነበር "እርሳቸው ካልተመለሱ ይህች አገር መፈራረሷ አይቀሬ ነው" የሚል ጭንቀት አልተከሰተም።
➔ከሚዲያ የተሰወሩት ከፓርላማ በተላለፈ የጥላቻ ንግግር ከሁለት ሺህ በላይ ነፍሶች ወደ ጅምላ መቃብር በገቡ ማግሥት በመሆኑ "የንጉሡ መጥፋት የእርስ በእርስ መጠፋፋት ያመጣ ይሆን" የሚል ሥጋት የተሰማው አልነበረም።
➔"የጠሚው አለመኖር በአገር እና በገዢው ፓርቲ እጣ ፈንታ ላይ የሚያስከትለው አደጋ" የሚል ትንታኔም አልተሰማም። ምክንያቱም ከሚዲያ መራቃቸውን እያወቀም፣ እኩሉ አመራር አፋኝ፣ እኩሉ ደግሞ ታፋኝ ሆኖ እርስ በእርሱ ሲጠዛጠዝ ነበር።
በመሆኑም ሶሻል ሚዲያውን የሞላው ብቸኛ ርዕስ "ምን ሆነው ጠፉ?" የሚል ቀላል ጥያቄ ነበረ። 😆
14 341
ተቀዳሚ ሙፍቲ
(የእኛ ዘመን ጌታው ሸህዬ)
አማራዎችን በሀይማኖት ከፋፍሎ ለማክሰም በርካታ ጥረት ተደርጎ ነበር።
እርስዎ ግን እሳት ላይ ቤንዚን ከማርከፍከፍ ይልቅ ውሀን መረጡ። በወንድማማች መሀከል የተፈጠረ ክስተትን ከማጋጋል ይልቅ ማሸማገልን አስቀደሙ።
እናም በእርስዎ አርቆ አሳቢነት የከሸፈውን የሃይማኖት ግጭት ሳስብ ‹‹የምን ጊዜም ታላቅ የሃይማኖት አባት›› ብዬ ላመሰግንዎ ወደድኩ፡፡
ማሳሰቢያ፡- ይህ ጽሁፍ ከመጅሊስ ጋር የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ ስድብ አይበረታታም፡፡
14 341
ሒስ እና መወድስ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
➔የዓመቱ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና አነጋጋሪ ሚዲያ - ኢትዮ 360
➔›› ›› አደናጋሪ ሚዲያ- EMS
➔›› ›› የግፉአን ድምጽ- የኛ ቲቪ፣ አዲስ ድምጽና ሮሐ ሚዲያ
➔›› ›› ሐቀኛ ጋዜጠኛ- ተመስገን ደሳለኝ እና ጎበዜ ሲሳይ
➔›› ›› እውነት ጠል ጋዜጠኛ- ፋሲል የኔ ዓለም
➔›› ›› መድሎኛ ጋዜጠኛ- ግሩም ጫላ
➔›› ›› ገለልተኛ ጋዜጠኛ- ኤሊያስ መሠረት
➔›› ›› ሕዝበኛ ፓርቲ- እናት ፓርቲ እና ባልደራስ
➔›› ›› ግለኛ ፓርቲ- ኢዜማ እና አብን
➔›› ›› ቁማርተኛ ፓርቲ- ብልጽግና
➔›› ›› ድንቅ ፖለቲከኛ- ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ
➔›› ›› ጽኑ አርበኛ- ዘመነ ካሤ
➔›› ›› አሰላሳይ ልሂቅ- ረ/ፕ ትንግርቱ ገብረ ጻድቅና መስከረም አበራ
➔›› ›› መካሪ ያጣ አማካሪ- ገምቱ እስቲ 😆
➔›› ›› የሕዝብ አርቲስት - ቴዲ አፍሮ
➔›› ›› የመንግሥት አርቲስት - አቤል ሙሉጌታ
➔የዓመቱ ጥቃት ቀስቃሽና ደም አፋሳሸ የጥላቻ ንግግር ማሠራጫ ስቲዲዮ- የፓርላማው አዳራሽ
አልጨረስኩም.... 😆
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
