uk
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 346 підписників, посідаючи 2 649 місце в категорії Блоги та 2 354 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 346 підписників.

За останніми даними від 24 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -112, а за останні 24 години на -7, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 39.43%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.21% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 656 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 752 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 25 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Блоги.

14 346
Підписники
-724 години
-387 днів
-11230 день
Архів дописів
photo content

Mark my word‼️
Mark my word‼️

‹‹የአማራ ክልል መንግሥት›› ለሚባለው ስብስብ‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ አሁን ላይ አንተን ማብጠልጠሉ ጠቀሜታ እንደሌለው በማመን ብሎም መንግሥታዊ አደረጃጀቱም ሆነ በጀቱ ያለው በእጅህ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ የሚከተሉትን ነገሮች ተግባራዊ ታደርግ ዘንድ እጠይቃለሁ፡፡ ➔ለቃቅመህ ያሰርካቸውን ወይም የምታሳድዳቸውን ፋኖዎች ነጻነታቸውን ሰጥተህ እንዲሁም ያባረርካቸውን የጦር መሪዎች ይቅርታ ጠይቀህ ወገናቸውን የሚታደጉበትን እድል ብትፈጥርላቸው…. ➔እንደ በላይ አካል የምትቆጥረውን የፌደራል መንግሥት በሙሉ አቅሙ የሚነሳበትን ወቅት መጠበቁን ትተህ ከእጅህ ላይ ያለውን ጸጋ ለትግል ብታውለው፤ ➔ከወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ አፋር ግንባር መዝመታቸው ወይም ደግሞ ፕሬዝዳንት ሙሥጠፌ በጦር ግንባር መገኘታቸው ያስገኘውን ፋይዳ ቀላል አይደለምና ከመላው ከፍተኛ አመራር ጋር በጦር ግንባር ተገኝተህ ሕዝብን የማነቃቃት ተግባር ብትፈጽም፤ ➔የትኛውም ጠቃሚ ምክር ያለ መንግሥታዊ መዋቅር ምድር ሊነካ አይችልምና ከተሞች ከተወረሩና ከወደሙ በኋላ ነጻ ለማውጣት የሚከፈለውን መስዋዕትነት ጥቃትን ለመከላከል ይውል ዘንድ ያለህን አቅም ሁሉ አሟጥጠህ ብትጠቀም፤ ➔በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኝ እያንዳንዱ ወረዳና ቀበሌ በዘመቻው ይሳተፍ ዘንድ የዘማች ኮታ ወስነህ ወደ ታችኛው መዋቅር ብታወርድ…. ➔በአውራጃ ደረጃ ወስነህ የወረራ ወረፋ ጠባቂ ያደረግከው ሕዝብ በአማራነት ማዕቀፍ ወደ ተወረሩ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ የመጣበትን ሕዝባዊ ማዕበል ይመክት ዘንድ ብታመቻችለት… ➔በትግል ወቅት በጦር ሜዳ ተገኝቶ ከመተኮስ ባልተናነሰ መልኩ በክልሉ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ የሕዝብን ሞራል መቀስቀስ፣ ስንቅ መለገስ፣ ተተኳሽ ማድረስ… አስፈላጊ በመሆኑ የወገኑ ሕልውና የሚገደው ሁሉ ትግሉን ይደግፍ ዘንድ ጥሪ ብታደርግ…........ የሚሉ ጥያቄዎችን ሳቀርብ በየትኛው የትግል ቦታ ላይ ተገኝቼ የትኛውንም አይነት ወገናዊ ግዴታዬን ለመወጣት ዝግጁ መሆኔን በመግለጽ ነው፡፡ Share

ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጋር ጥምረት የፈጠረው ሕዝባዊ ጦር እስከ መጨረሻው ምዕራፍ መጓዝ ከተፈቀደለት እንደ አረም የክረምትን ወቅት ጠብቆ የሚመጣውን አሸባሪ ከትግል ሜዳ የማሰናበት አቅም አለው።

“ምሬ የዚየስ ልጅ፥ መብረቅ መታጠቂያው መንጋጭላ የሚያረግፍ፥ ምላጩን ሲስበው” አሳዬ ደርቤ አንዳንዱ ጥቃት ፈሪና ተሸቆጥቋጭ ዜጎችን ሲፈጥር አንዳንዱ ደግሞ የተደበቁ ጀግኖችን ፈልፍሎ ያወጣል፡፡ በመ
“ምሬ የዚየስ ልጅ፥ መብረቅ መታጠቂያው መንጋጭላ የሚያረግፍ፥ ምላጩን ሲስበው” አሳዬ ደርቤ አንዳንዱ ጥቃት ፈሪና ተሸቆጥቋጭ ዜጎችን ሲፈጥር አንዳንዱ ደግሞ የተደበቁ ጀግኖችን ፈልፍሎ ያወጣል፡፡ በመሆኑም ወራሪው መንጋ በርካታ ንጹሐንን ሰውቶ ቢሄድም በዚያው ልክ ደግሞ የማይሰበሩ ጀግኖችን አስነስቷል፡፡ በወረራ በቆየባቸው ጊዜያት በርካታ መሠረተ ልማቶችን አፈራርሶ፣ የዜጎችን ደም አፍስሶና ሴቶችን አርክሶ ከፍተኛ ጉዳት ቢያደርስም አማራን ለማጥፋት ወስኖ በፈጸመው ወረራ “ፋኖ” የተባለ ሞት አይፈሬ የወጣቶች አደረጃጀት ቀስቅሷል፡፡ ከእነዚህም የአማራ ፋኖዎች መሃከል የምሥራቅ አማራ ፋኖ አንዱ ሲሆን በሕልውና ዘመቻው ወቅት በአምሥት የራያ ግንባሮች ጥቂት ክላሽ ታጥቆ በክትክታ ዱላና በሳንጃ የጀመረውን ትግል የፋሽሽቱን ጦር እየደመሰሰ ወደ ክላሽና ስናይፐር ማሳደግ ችሏል፡፡ ዲሽቃና ታንክ በክላሽ ማርኳል፡፡ የወራሪውን ምሽግ ሰብሮ በመግባት በመከላከያ ሠራዊቱ የሚታወቁ ግዙፍ ጀብዱዎችን ፈጽሟል፡፡ ይሄውም በወሎ ምድር የበቀለው የምሥራቅ አማራ ፋኖ፡- “ምሬ የዚየስ ልጅ- መብረቅ መታጠቂያው መንጋጭላ የሚያረግፍ- ምላጩን ሲስበው” ተብሎ በተዜመለት በራያው መብረቅ በሻለቃ ምሬ ወዳጆ የሚመራ ሲሆን ጥቂት ፋኖዎችን ይዞ በጀመረው ትግል በርካታ ጀግኖችን ማፍራትና እልፍ አእላፍ ጀብዱዎችን መሥራት ችሏል፡፡ (ከላይ ያለው ቁራጭ ታሪክ "እልልታ የዋጠው እሪታ" ከሚለው መጽሐፋችን ተቀንጭቦ የወጣ ሲሆን፤ ዛሬም ምሬ ወዳጆ የማይታሰበውን ከበባ ሰብሮ ሌላ ጀብዱ መፈጸሙን በመስማቴ ላጋራችሁ ወደድኩ።)

ወራሪውን ኃይል "ላሳልፍህ" ከማለት ባለፈ "አዝዬ ላድርስህ" ብትለው እንኳን አራት ኪሎን አይመኛትም። ዒላማው ያነጣጠረው ዶክተር ዐቢይና ዶክተር ይልቃል ላይ ሳይሆን አንተ ላይ ነው!!

ለወገኔ ▬▬ ➔ተፈናቃይ ከመባል ታጋይ መሆንን እንምረጥ። ➔ከተዋረደ ሕይወት ይልቅ የተከበረ መስዋዕትነት እናስበልጥ። ➔መሆን ባለበት ፈንታ መሆን የሌለበት ሲሆን ያየነው በመንግሥት እጦትና በእኛ ቸልተኝነት መሆኑን እንገንዘብ። ➔በባዶ እግሩ የሚሄድ ገበሬ አስተምሮ ለቁም ነገር ያበቃችሁ ሁሉ ወገንን ከእረፍት አልባነት የሚታደግ የትግል ስልት ቀይሱ። ➔በቆቦ የተጀመረውን ወረራ ወደ ቀያችን ማዛመትም ሆነ ቆቦ ላይ ማስቀረት የምንችለው እኛ መሆናችንን አስታውሱ። ➔የሐይማኖት አባቶች መላው ሕዝብ በባርነት ላይ ይሸፍት ዘንድ ቀስቅሱ። ➔ፋኖዎች የወላጆቻችሁን ክብር ለማስጠበቅ ተንቀሳቀሱ። እኅቶች ስንቅ አድርሱ። ባለሃብቶች የአቅማችሁን ለግሱ። በተረፈ ትግሉ ባልተጀመረበት ሁኔታ ተስፋ መቁረጥን እና ሽንፈትን የምታከፋፍሉ ወገኖች ሱሪያችሁን ለእኅቶቻችሁ ሰጥታችሁ ቀሚሳቸውን ተዋሱ።

በስምምነት ስለሚጀመር ጦርነት...‼️ (አሳዬ ደርቤ) ➔አንዳንድ ጦርነቶች በተፋላሚዎች ውይይትና ስምምነት ይቋጫሉ፡፡ ➔አንዳንድ ጦርነቶች ደግሞ በተፋላሚዎች ስምምነት ይጀመራሉ፡፡ ማለትም.... ሁለት ተፈላሚ ኃይሎች በድብቅም ሆነ በግልጽ ወደ ውይይት ከመጡ በኋላ ቅድመ ሁኔታዎችን ያቀርባሉ፡፡ ሆኖም ግን በአንደኛው ተፋላሚ በኩል የሚቀርቡ ቅደመ ሁኔታዎች በሌለኛው ወገን ተቀባይነት ካገኙ በኋላ ጥያቄዎቹን በሰላማዊ መንገድ ተፈጻሚ ለማድረግ የማያስችሉ ውጫዊ ሁኔታዎችና ሕዝባዊ ፈተናዎች ያጋጥማሉ፡፡ ያን ጊዜም በሁለቱ ወገኖች ስምምነት በቃል ትዕዛዝ ተፈጻሚ መሆን የማይችሉትን ቅድመ ሁኔታዎች በአፈ-ሙዝ ለመስጠት የሚያስችል የይስሙላ ጦርነት እንዲጀመር ይደረጋል፡፡ እንዲህ ያለው ዘመቻ ታዲያ ውጤቱ ከጦርነቱ በፊት የሚወሰን በመሆኑ እስከሆነ ርቀት ድረስ ተሸናፊ ለመሆን ፈርሞ የገባውን አካል የትኛውንም አይነት ድጋፍ ብታደርግለት እንዲያሸንፍ ማድረግ አትችልም፡፡ የጦር መሣሪያ ጭነው ወደ ጠላት ቀጠና የሚገቡ አውሮፕላኖች መኖራቸውን፣ አሸባሪው ቡድን መጠነ ሠፊ ጥቃት ለመሰንዘር መዘጋጀቱን... የሚገልጽ መረጃ ብትሰጠው እንኳን መረጃህን አስተባብሎና አንተን አባብሎ ያስተኛኻል እንጂ የተደገሰውን ጥቃት ያጨናግፈዋል ተብሎ አይታሰብም። ከዚህ ይልቅ በስምምነት የሚጀመሩ ጦርነቶችን ውጤት መቀየር የሚቻለው የእራስን ሕዝባዊ ኃይል ተጠቅሞ እራስን መከላከል ሲቻል ነው፡፡ እስከሆነ መዳረሻ ድረስ የአባራሪ እና ተባራሪ ውል ከፈረመ መዳፍ ድል በመጠበቅ ፈንታ የእራስን ትግል ለኩሶ የጨዋታውን ውጤት በመቀየር ነው፡፡ በየተራ የምንወረርበትን እለት በመጠባበቅ ፈንታ ወደ ተወረሩት ወገኖችና አካባቢዎች በጋራ በመንቀሳቀስ ነው፡፡ የአማራን ሕዝብ እና ክልል የመታደጊያው ትክክለኛ ቦታ ሰሜን ወሎ እና ወልቃይት ዳርቻ ላይ መሆኑን አውቀን የጋራ ጥቃታችንን አዝሎ የመጣብንን ጠላት በየተራ ከመቀበል ይልቅ በጋራ መከላከል ስንችል ነው፡፡

ባሕር ማዶ ለሚገኙ ወገኖች እልልታ የዋጠው እሪታን በEMS በኩል እየላክን ስለሆነ ሌሎች ወገኖችም ማዘዝ ትችላላችሁ።
ባሕር ማዶ ለሚገኙ ወገኖች እልልታ የዋጠው እሪታን በEMS በኩል እየላክን ስለሆነ ሌሎች ወገኖችም ማዘዝ ትችላላችሁ።

ያንተ ወገን ድንበር አልፎ ሌሎችን ሲያጠቃ ገለልተኛ መሆን አይከብድም። በሕዝባዊ ጎርፍ ወገንህን የሚጨፈጭፍ አሸባሪ ሲመጣ ግን "አትንኩኝ" ብሎ በጋራ መነሳት እንጂ "ምን አገባኝ" ማለት አይታሰብም!

"ለሰብአዊ አገልግሎት የሚውል 570ሺ ሊትር ነዳጅ በህውሓት ተዘረፈ" ተብሎ በተመድ በኩል የተሰጠውን መግለጫ "ለህውሓት ተላለፈ" ብዬ አነበብኩት። "የተባበሩት" የሚባለው የነዳጅ ማደያ የUN ኑሯል ለካ?😆

ከብልጽግና እጅ ሰላም የሞላው ሕይወት ቀርቶ ድል ያለው ጦርነት ማግኘት አይቻልም‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ አንዳንዱ ሥርዓቶች በሰላም እጦት ያሰቃዩኻል፡፡ እንደ ብልጽግና ያለ መንግሥት ግን በሰላም ተደላድሎ ለመኖር ይቅርና እራስን ለመከላከል የማያስችል መሰናክል ደርድሮ ተፈናቃይ ያደርግኻል፡፡ ሰላምን ብቻ ሳይሆን ጦርነትንም የማይቻል ያደርግብኻል፡፡ በዚህም መሠረት የአማራ አርሶ አደር ፊቱን ወደ ሰላም እና ልማት አዙሮ ማሳውን መንከባከብ ሲጀምር እንስሳትን የሚረሽን፣ ሴቶችን የሚደፍር፣ ጥሪትን የሚያወድም…. ጠላት የከሰብ ወቅት ጠብቆ ይመጣበታል፡፡ ያን ጊዜም ከማሳው እና ከቀየው የሚያፈናቅል ጠላት አሻግሮ እያዬ ግብር የሚከፍለውን መንግሥት ሲጣራ ‹‹የሰብል ጉብኝት ላይ ስለሆንኩ አትረብሸኝ›› በማለት ያለምጥበታል፡፡ ልክ እንደዚሁ ሁሉ ከብልጽግና እጅ የወደቀው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም በወታደራዊ ሳይንስና በእራሱ የትግል ሰሌዳ የሚያዋጋው ባለቤት አጥቶ ድሮን የማይበርበትን፣ መንግሥት ያንቀላፋበትን… ጊዜ ጠብቆ ጥቃት በሚፈጽም ሽፍታ መክፈል የሌለበትን መስዋዕትነት ሲከፍል ታይቷል፡፡ ከብዙ ጉዳት በኋላም ይሄው ሕዝብ እራሱን እና ልጆቹን አደራጅቶና ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ተቀናጅቶ እንዲሁም የተወረረ ቀየውን በከፊል አጽድቶ ከመከላከል ወደ ማጥቃት ሲሸጋገር በጠላት አፈሙዝ የተጀመረው ውጊያ በመንግሥት ትዕዛዝ እንዲቆም ይደረጋል፡፡ ከዚያም…. ተመትቶ የሸሸው ጠላት በማይወረርና በማይደፈር ክልሉ ውስጥ ሆኖ ከአየር ጥቃት የሚታደገው የክረምት ወቅት እስኪመጣ ድረስ ለሌላ ዙር ጦርነት እራሱን ሲያዘጋጅ ይከርማል፡፡ ለጦሩ ስንቅ የሚሆን ስንዴ እና ነዳጅ ከፌደራል መንግሥት እስኪላክለት ድረስ ስለ ድርድር እያወራ በርካታ ጦር ያሰለጥናል፡፡ ውጫዊ ኃይሎች በአውሮፕላን የሚጭኑለትን ጥይትና ዱቄት ያከማቻል፡፡ ከዚያም ያረቀቀውን የትግል ካሌንደር መሠረት አድርጎ የድል ባለቤት ያደርግልኛል በሚለው ግንባር ጦርነትና ወረራ ይለኩሳል፡፡ የሰላም ሕይወትን መግፋት ቀርቶ በቅጡ መዋጋት የተነፈገው የአማራ ሕዝብ ግን ከጠላት ወረራ ነጻ በወጣ ማግስት ፋኖ ልጆቹን የሚያሳድድ መንግሥት ይመጣበታል፡፡ በእራሱ የትግል ሰሌዳ የሚመራው የሽብር ቡድን ደስ ባለው ግንባር ወረራ ፈጽሞ ወደ እርሱ ሜዳ እስኪመጣ ድረስ ፋኖዎችን የሚያፍስ እና ለወራሪዎች ስንቅ የሚያደርስ የጭነት መኪና ሲቆጥር ይውላል፡፡ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያ በአውሮፕላን የሚጫንለት ጠላት ባለበት ሁኔታ ‹‹ጥቁር ክላሽ ታጥቀኻል›› ተብሎ ሲንገላታ ይከርማል፡፡ ሰላማዊ ሕይወትን ብቻ ሳይሆን ለጦርነት መዘጋጀትን ተነፍጎ በክልሉና በፌደራሉ መንግሥት ሲዋከብ ይሰነብታል፡፡ ከዚያም ከወንዝ ማዶ ከባድ መሳሪያ የሚተኩስና ወደ እርሱ ቀዬ የሚገሰግስ ጠላት ተመልክቶ መንግሥትን ፍለጋ ዐይኑን ሲያዞር ብቻውን ቁሞ እራሱን ያገኘዋል፡፡ ባንድ በኩል ያለ ጦርነት መኖር የማይችል ጠላት እጁን ስቦ ወደ ትግል ያስገባዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የማሸነፍ ፍላጎት የሌለው መንግሥት በትግሉ እኩሌታ ላይ እግሩን ወልክፎ ያለ ድል ያስቀረዋል፡፡ እናም የዚህን ቁማርተኛና ዳተኛ መንግሥት ባሕሪይ ስትታዘብ በእነ በላይ ዘለቀ ሲመራ የነበረው መንግሥት አልባ ትግል ይናፍቅኻል፡፡

photo content

7.5.1 ወሎ ላይ የጎመራው የአማራ ሕዝብ አንድነት ▬▬▬▬▬▬▬▬ ትሕነግ እና ኦነግ ወሎ ምድር ላይ ጥምረት ፈጥረው ወደ ሸዋ ሲዘምቱ እንደታየው ሁሉ…. የጎንደር፣ የሸዋ፣ የጎጃምና የወሎ አማራ ፋኖ
7.5.1 ወሎ ላይ የጎመራው የአማራ ሕዝብ አንድነት ▬▬▬▬▬▬▬▬ ትሕነግ እና ኦነግ ወሎ ምድር ላይ ጥምረት ፈጥረው ወደ ሸዋ ሲዘምቱ እንደታየው ሁሉ…. የጎንደር፣ የሸዋ፣ የጎጃምና የወሎ አማራ ፋኖዎችም ጥምረት የፈጠሩት የቤተ-አማራ ማሕጸን በሆነችው የወሎ ምድር ነበር፡፡ በዚህም መሠረት ከጎንደር የተነሳው የአማራ ፋኖ… ‹‹ከራያ አንስቶ ፥ እስከ ሑመራ እርሳስ ጠርጣሪ ፥ እንደ ሽንብራ›› .... በሚል ፉከራ ደሴ ከተማ ሲገባ፣ የሸዋ አማራ ፋኖ እና ሚኒሻም አማራን በጠላትነት የፈረጀውን ወራሪ ማስቆም የሚቻለው በአማራነት ማዕቀፍ ውስጥ በአንድነት በመቆም መሆኑን ተረድቶ ወደ ወሎ ዘምቷል፡፡ ከሰሜን ወሎ ዞን ወደ ደቡብ ወሎ ለተፈናቀሉ ወገኖቹ ማኛ ጤፉን፣ ስንዴና በርበሬውን ሲጭን የሰነበተው የጎጃም አማራም… “ከዚያ ወሎ ምድር- የሚያጭዱት አዝመራ የሚረግፍ እንስሳ - በጥይት፣ በካራ የሚወድመው ጥሪት የሚከስመው ሕይወት - በማንም ወንበዴ ከወሎ እስከ ጎንደር - የኔ አይደለም እንዴ? ደህና ሰንብት ዓባይ - ጣና ቻው ቻው በቃ ከእንግዲህ ይበቃል - መውደም በፈረቃ” ... በሚል ቁጣ በእነ ዘመነ ካሴና ማስረሻ ሰጤ የሚመራ ፋኖውን ካዘመተ በኋላ የቤተ-አማራ ማሕጸን በሆነችው የወሎ ምድር ላይ እነ ኤፍሬም አጥናፉን ገብሮ የአማራን አንድነት በደሙ አጽንቷል፡፡ (እልልታ ከዋጠው እሪታ የተቀነጨበ)

እልልታ በዋጠው እሪታ እሸቴ ሞገስ ሲታገስ ….ከዚያ በማስከተልም ሳላይሽ የደረሰው ጠላት የአሰፋ ታዬን ግቢ ወረረው፡፡ አንበሳው እሸቴም ልጁን ጠርቶ እንደዚህ አለው፡፡ “እኔን ቀድመው ከጣሉኝ ለማምለ
እልልታ በዋጠው እሪታ እሸቴ ሞገስ ሲታገስ ….ከዚያ በማስከተልም ሳላይሽ የደረሰው ጠላት የአሰፋ ታዬን ግቢ ወረረው፡፡ አንበሳው እሸቴም ልጁን ጠርቶ እንደዚህ አለው፡፡ “እኔን ቀድመው ከጣሉኝ ለማምለጥ ሞክር፤ አንተን ከነጠቁኝ ግን ከኋላህ ስለምታገኘኝ እንዳትሸበር!›› ልጅም መለሰ… “መግደል እና መሞት- የምርጫ ጉዳይ ነው- ለእራስ የሚለገስ፤ እነሱም ውስጥ አለ- የሚንጠባጠብ ደም- የሚቆም እስትንፋስ፤ እናም አባቴ ሆይ- የከበበንን ሞት- ለቅመን ለመጨረስ፤ በምኒልክ ተስፋ- እግዚአብሔርን አምነህ- ክላሽህን አጉርስ›› እናም ሁለት ሆነው የአሰፋ ታዬን ግቢ የወረረውን ጠላት ገጠሙት፡፡ መንታ ሆነው መላዕከ ሞትን ተጋፈጡት፡፡ ተኩሱ ተቀጣጠለ፡፡ አባትና ልጅ የመሸጉበት ግቢ በጥይት ተነዳደለ፡፡ የአቶ እሸቴ እዳይት የሚበጥስ ተኩስ አምሥት ወራሪን ጣለ፡፡ በይታገሱ ሽጉጥም አንድ ሰለባ ታከለ፡፡ ይሄንንም ጀብዱ ከፈጸሙ በኋላ ምድር ላይ ከተጋደሙት ወራሪዎች መሃከል የአንዱን ትጥቅ በማንሳት አባትና ልጅ ክላሽ ታጠቁ፡፡ ተኩሱ በበረታ ጊዜም የአሰፋ ታዬን ግቢ ለቀቁ፡፡ አንበሳውና ደቦሉ ከማሽላ ማሳ መግባታቸውን የተረዳው ወራሪ ሥድስት ጓዶቹን የቀሙትን ጀግኖች ሕይወት ሊቀማ ሲንደረደር ይታገሱ በማረከው ክላሽ ሦስቱ ወራሪ መንገድ ላይ ከሰመ፡፡ የ31 ዓመቱ ወጣትም ከአባቱ ጎን ሆኖ በታላቅ ጀግንነት እየተዋጋ ሳለ ጥይት የጨረሰ ይመስል ተኩሱን አቆመ፡፡ ያን ጊዜም አቶ እሸቴ ዐይኑን ከዒላማው ላይ አንስቶ ወደ ልጁ ሲልከው ይታገሱ በክላሹ ፈንታ ደረቱን ይዞ ተመለከተ፡፡ ጥይቱን ሳይሆን የምድር ቆይታውን መጨረሱን የተረዳው አባትም፣ የልጁን ጣዕር ተጋርቶ ቃተተ፡፡ ሊያለቅስ ቃጣው፡፡ ልቡ ግን… “ነውር ነውና- ለጀግና ማልቀስ እንባህን ውጠህ- ደሙን ቶሎ እበስ” በማለት ገሰጸው....

ከማገር ሚዲያ ጋር ያደረግኩት ቆይታ

በውጭ አገራት ለሚገኙ ወገኖች እልልታ የዋጠው እሪታን በፖስታ ቤት በኩል ማድረስ ጀምረናል።
በውጭ አገራት ለሚገኙ ወገኖች እልልታ የዋጠው እሪታን በፖስታ ቤት በኩል ማድረስ ጀምረናል።

የተወሰኑ ኮፒዎችን ለላይብረሪ መለገስ የምትፈልጉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ