Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 337 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 647,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 350 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 337 名订阅者。
根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -108,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.62%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 538 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 337
订阅者
-424 小时
-317 天
-10830 天
帖子存档
14 337
"የምናገርው አለኝ ለታሪክ የሚቀመጥ...ግን እንደት ልተንፍስ ? እ እ እ የሆነ ጊዜ ላይ በአቶ ሺመልስ የተፃፈ ደብዳቤ ቢሮየ መጣ..." ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ
"ዝም በል ተባልክ እኮ" ምክር ቤቱ 😆
14 337
ለአዳነች አቤቤ
አሳዬ ደርቤ (አጭሬ ሆነ መሰል 😆)
እራስሽን ከወንጀሉ ነፃ ለማድረግ በጣም ብዙ እያወራሽ ነው።
ሆኖም ግን እየዋሸሽ እንጂ ገንዘብ ሳይቆጥቡ የኮንዶሚኒየም እጣው ውስጥ ስለተሳተፉት 93 ሺህ ሰዎች በቂ መረጃ ነበረሽ። ምክንያቱም አዲስ አበባ ላይ ሲሠራ የከረመውን እንኳን አንቺ ማንኛውም ዜጋ ጠንቅቆ ይረዳል።
በተረፈ ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ ለምክር ቤት አባላት እውነቱን ለማጋለጥ ሲሞክር፣ በአፈ ጉባዔዋ አማካኝነት የመናገር እድሉን የነፈገሽውና በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፈውን ፕሮግራም ያቋረጥሽው ልትደብቂው የምትሞክሪውን እውነት እንዳያወጣው ፈርተሽ መሆኑ ግልጽ ነው።
እናም ወንጀሉን የፈጸሙትን ዘረኞች እና ዘራፊዎች ከጉያሽ ደብቀሽ የጦስ ዶሮ ፍለጋ መሠማራትሽ ልክ አይደለም።
14 337
"እንደ አሁኑ አይነት ዘረኝነት አላየሁም። ከሀገሬና ከተቋሜ በማንነቴ ምክንያት ተሰድጃለሁ" ጋዜጠኛ እማዋይሽ ግርማ
ሁሉ ነገር ተጨመላልቋል። አይን ያፈጠጠ ዘረኝነት ነው ያለው። እኔ በሁለቱም ሰርዓት ሰርቻለሁ። እንደ አሁኑ አይነት ዘረኝነት ግን አላየሁም። በአጠቃላይ ETV የሀገሪቱን ምስቅልቅል ፖለቲካ ይመስላል።
በግሌ ለ10 አመት ከሰራሁበት ETV በማንነቴ ተገፍቻለሁ። ሌሎችም በማንነታቸው ተገፍተዋል። ችሎታ ሳይሆን ማንነት ተቆጥሮ የማይመጥነን ቦታ ተመድበናል። ሀላፊዎቻችን ETV ን እየመሩ የማህበራዊ ሚዲያ ኘሮፋይላቸው ግን የOBN ጋዜጠኛ ነው የሚለው።
ፈጣሪ ካልታከለበት የሚመጣ ለውጥ ያለ አይመስለኝም። ነገሮች እየተወሳሰቡ ሄደዋል። በሀገሬ ተስፋ ቆርጫለሁ። በተቋሜ ተስፋ ቆርጫለሁ። በዚህም ለስልጠና በሄድኩበት ሀገረ ኔዘርላድ ጥገኝነት ጠይቄ ቀረቻለሁ። ከሀገሬና ከተቋሜ በማንነቴ ተሰድጃለሁ።
እማዋይሽ ግርማ - የETV ጋዜጠኛ የነበረች
"መፍትሔው ግን ጥገኝነት አልነበረም። ዘረኛ ያልሽውን ሥርዓት ለማስወገድ የአቅምን ማበርከት እንጂ..."
14 337
በነገራችን ላይ በትሕ-ኦነግ ኃይሎች ዘንድ የፌደራሊስት መገለጫው አገር ማፍረስ፣ የአማራን ደም ማፍሰስና ኮከብ ያለው ባንድራ መልበስ ነው። ለኢትዮጵያ ከምትሮጠው ለተሰንበት ይልቅ ለባሕሬየን የምትሮጠውን አትሌት በጉጉት መመልከት ነው።
ለእኛ ለአማራዎች ግን...
➔ደራርቱንም ሆነ ለተሰንበትን ማክበር ነው፤
➔ በክልላችን ያሉ ብሔረሰቦችን በልዩ ዞንና ወረዳ ማዋቀር ነው
➔ቋንቋቸውን የሥራ ቋንቋ ማድረግ ነው።
➔ባሕልና ሃይማኖታቸውን ማክበር ነው።
➔በራሳቸው መሪዎች የሚገለገሉበትን እድል መፍጠር ነው።
እናም እልኻለሁ...
ሐቀኛው የአማራ ፌደራሊስት የትኛዋም አትሌት አገሯን እንደምትወክል ተረድቶ "የእኛ" እያለ ሲያወድሳት ስግብግቡና ጥቅመኛው ፌደራሊስት ግን ብሔሯን አስታውሶ "የእኔ ብቻ" እያለ ሲሟገት ታገኘዋለህ።
14 337
በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አትሌት ለተሰንበት ግደይ በ10 ሺህ ሜትር የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ለአገሯ አስገኝታለች። አይበገሬ አትሌት!! የሚገርም ትንቅንቅ!
14 337
➔የሚገርመኝ እኮ 12 ሺህ ፋኖ መታሰሩ አይደለም፡፡
በአማራ ክልል ውስጥ ሆነው አማራን የሚታገሉ ኦነጎች፣ ሸንጎዎች፣ ኮሚቴዎች... በብልጽግና እገዛ አቅማቸውን አጠናክረው ሲወጡ መመልከቴ እንጂ…
➔የሚያናድደኝ እኮ የወልቃይት ማንነት በብአዴን አማካኝነት ለገበያ መቅረቡን መረዳቴ አይደለም፡፡
መላው አማራ ለወልቃይት ሕዝብ- በጀት የሚለቀቅበትን፣ በወለጋ የሚኖሩት ወገኖቹ ደግሞ እረፍት የሚያገኙበትን ቀን ሲጠብቅ… የደቡብ ወሎን ዞን ለሁለት የሚሰነጥቅ…. ሰቆጣን ከአማራ ጉያ የሚነጥቅ…. አዊን- ከጎጃም፣ ጭልጋን- ከጎንደር የሚያራርቅ…. ሸዋን ከፊንፊኔ ጋር የሚሰለቅጥ…. እንደ አጠቃላይም የአማራ ክልልን ከካርታ ላይ የሚፍቅ… ግዙፍ ፕሮጀክት በትሕነግ ተረቅቆ፣ በብልጽግና ጸድቆ፣ በብአዴን ተቋራጭነት ወደ ተግባር ምዕራፍ መሸጋገሩ እንጂ….
ይሄን የረዥም ጊዜ ፕሮጀክት ታዲያ በቀላሉ ማክሸፍ የሚቻል ቢሆንም፣ ከእያንዳንዱ መፍትሔ ስር ብአዴን የተባለው የጎጥ ኮንትራክተር ‹‹ችግር›› ሆኖ ስለሚከሰት ብዙ ማውራቱ እርባና የለውም፡፡
14 337
ያለ ሙሥና ብልጽግና አለ እንዴ?
➔ሻል ሻል ያሉ አመራሮቹን "ደካሞች" ብሎ ያባረረ፣
➔ለፍትሕ የሚሟገቱ አክቲቪስቶችን እና ጋዜጠኞችን "ወንጀለኞች" ብሎ ያሰረ፤
➔12 ሺህ ፋኖዎችን በአሸባሪነት ወንጅሎ በወሕኒ ቤት ያጎረ፤
➔60 ሚሊዮን ብር የተከፋፈሉ የብአዴን ባለሥልጣናትን በምህረት አልፎ እነ ዮሐንስ ቧያለውን የሻረ፤
➔በርካታ ቢሊዮን ብር የተያዘላቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለኮንትራክተር በመስጠት ሒደት ውስጥ ሕጋዊ መንገድን እና ጨረታን ያስቀረ፤
➔በነፃ የሚሰጡ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በጉቦ የሚሸጡ አመራሮችንና ባለሙያዎችን በየቢሮው ያዋቀረ... መናኛ ሥርዓት "ሙሠኛ ባለሥልጣናትን ተጠያቂ ማድረግ ጀምሬያለሁ" ብሎ ቢናገር ማን ያምነዋል?
በእውኑ ከብልጽግና የሥነ ምግባር መርሖች መሀከል ቀዳሚው "ሙሥና መብላት" የሚል አይደለምን?
14 337
የአማራ ክልል ፍርድ ቤት በ30 ሺህ ብር ዋስ ሲለቃቸው የፌደራሉ መንግሥት "እኔ እፈልጋቸዋለሁ" ብሎ ወደ አዲስ አበባ አመጣቸው። ለቀናት ካሠራቸው በኋላም በ20 ሺህ ብር ዋስ ዛሬ እንዲለቀቁ ፈቀደላቸው።
እናም የፊንፊኔው መንግሥት ከመንገድ ላይ እንዳያግታቸው እየጸለይኩላቸው ነው።
14 337
ይሄንን ሐቅ ስጽፍ የሰደባችሁኝ ይቅርታ አትጠይቁኝም ወይ?
የከተማ መስተዳድሩ እኮ ላለልተመዘገቡ ሰዎች ማከፋፈሉን አምኖ ይቅርታ ጠይቋል። 😆
የቀን ጅቡ ሄዶ የጉም ጅቡ መጣ!
14 337
ጂሌ ጥሙጋ ላይ ሲሰለጥን የከረመው የኦነግ ታጣቂ በኤፍራታና ግድም ወረዳ በሰነዘረው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ሁለት መንደሮችን አውድሞ በአጣዬ ዙሪያ መሰባሰብ ጀምሯል። በርካታ የአማራ ልዩ ኃይል አባላትን እና ገበሬዎችን ገድሏል።
አገሩን ሲያስከብር የኖረው የአማራ ሕዝብ በብአዴን እና በአብን ይሁንታ እራሱን ማስከበር ተስኖት የማንም መጫዎቻ መሆኑ ያንገበግባል።
14 337
"በዚህ ስድስት ወር ብቻ 104 አሜሪካውያን ተገድለዋል" በተባለበት የዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ወገኖቻችን በወለጋ ዞን የተፈጸመውን ጭፍጨፋ በማውገዝ ላይ ይገኛሉ፡፡
እናም በባለፈው ዓመት በአሜሪካ አገር 20 ሺህ ዜጎች መገደላቸውን በመረጃ ላይ ተመስርቶ የነገረን መንግሥት ኢትዮጵያ ዜጎቿን በማስጨፍጨፍም ሆነ በማሰለፍ ከአሜሪካ የተሻለች አገር መሆኗን የሚያሳይበትን መድረክ መስቀል አደባባይ ላይ አዘጋጅቶ ‹‹በሎስ አንጀለስ፣ በፊላደልፊያ፣ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በባልቲሞር፣ በኒውዮርክና በቺካጎ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድምጽ እንሁናቸው›› እንዳይለን እሰጋለሁ።
14 337
በአርቲ ቡርቲ ንግግር የታጀበው የእለቱ መልዕክት
▬▬▬▬
➔በኢትዮጵያ ውስጥ የተገደለው አማራ ቁጥር ከአሜሪካውያን ጋር ሲወዳደር ኢምንት ነው። ስለዚህ ጭፍጨፋው ይቀጥላል።
➔እናቴ ከሠጠችኝ ዙፋን ላይ ማንም አይነቀንቀኝም።
➔ሰው የሞተበት ቦታ ላይ ችግኝ እንተክላለን
ቢያንስ አስክሬኑ ጥላ እንዲኖረው...
➔እኛ ያደግንበትን ቁማር ተጠቅማችሁ እኔን እና ሽመልስን መነጣጠል የምትሞክሩ አይሳካላችሁም።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
