Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 351 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 646,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 354 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 351 名订阅者。
根据 22 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -133,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 11.78% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 562 次浏览,首日通常累积 1 691 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 34。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 23 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 351
订阅者
-324 小时
-387 天
-13330 天
帖子存档
14 349
"ጸረ አማራ ኃይሎች ሁሉ ወዳጆች ናቸው"⁉️
የማይቀየረው የሄዊ ፖለቲካዊ ድንጋጌ❗️❗️
ምንም እንኳን በአማራ እና በኤርትራ መሀከል የተፈጠረ ጥምረት ባይኖርም ገዢው ፓርቲ ግን "ህውሓትን እና ብአዴንን በማስታረቅ የኤርትራ መንግሥትን እና አማራን ማራራቅ" የሚል እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ነው።
እንደ እውነቱ ከሆነ ግን አብዛኛው የአማራ ኤሊት ከሥርዓት ተሸካሚነት እራሱን ነጻ ባወጣ ማግሥት "ፋሽሽት ነህ" ሲሉት የኖሩትን መሪ "መንግሥት ብቻ ሳትሆን አማልክትም ጭምር ነህ" በሚል ውዳሴ ጫንቃቸውን ለሸክም አዘጋጅተው ወደ አራት ኪሎ የመጡት የሄዊ አመራሮች.... ይሄኛው የብልጽግና እቅድ በተሳካ ማግስትም አስመራ ገብተው አማራን ሲያራክሱና ኢሳያስን ሲያወድሱ መታየታቸው አይቀሬ ነው።
ምክንያቱም የህውሓት ፖለቲካ "ከአማራ ጋር የተቃቃሩ ኃይሎች ሁሉ ወዳጆች ናቸው" በሚል የቁሞ ቀር ፍልስፍና የሚመራ ነው።
ለዚያም ነው ትናንት "እርኩስ" ያደረጉትን አካል ዛሬ "ቅዱስ" ለማለት የደፈሩት...
14 349
የመብራት መሠረተ ልማቶች በመበጣጠሳቸው የተነሳ የሱዳን ወፍጮ ቤቶች ሥራ ስላቆሙ አምሳ ሺህ ኩንታሉ ስንዴ ተፈጭቶ ቢላክላቸው....😂😂
14 349
ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን!
https://www.youtube.com/live/2dD3NcQdIXo?feature=share
14 349
ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን!
https://www.youtube.com/live/6CTE2LAADWk?feature=share
14 349
ኢንተርኔት ከተዘጋ ሶስት ወር ሊሞላው ነው። የወይዘሮ ፍሬሕይወት የሥራ ድርሻም የአማራዎችን ስልክ ማስጠለፍና የግለሰቦችን ገበና መበርበር ሁኗል።
14 349
እንደ ሽፍታ ጋዜጠኞችን እና አክቲቪስቶችን በየወሩ እያገቱ የዋስትና ገንዘብ መሰብሰብ ያሳፍራል።
ወንድማችን የ20 ሺህ ብር ዋስ ተጠይቋል።
14 349
በወርሐ መስከረም ከእኔ፣ ከጎበዜ ሲሳይና ከመዓዛ ጋር ታስሮ የነበረው፣ በወያኔ ጊዜ በሐሰት የሽብር ክስ ከሰባት ዓመት በላይ የታሠረው፣ የመይሳውን ሥነ ልቦና ይዞ ጎንደር ምድር ላይ የበቀለው፣ በአማራነቱ የማይደራደረው፣ በጋዜጠኝነት ዘርፍ በሠራው ሥራ ዓለም አቀፍ ሽልማት የሚገባው፣ ጋዜጠኛ ብቻ ሳይሆን ሐቀኛ በመሆኑ የሚታወቀው፣ ከሰሞኑን በአማራ ተወላጅ የሆኑ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ላይ በተካሄደው አፈና እንደ ጌትነት አሻግሬና ዳዊት በጋሻው ካሉ ብርቱ ጋዜጠኞች ጋር የታሠረው.... ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ ዛሬ ፍርድ ቤት በርቦ ችሎት ላይ ከተናገረው የተወሰደ...
“እስር ቤቱን ከሞላነውና ችሎት ላይ ከቀረብነው መሀከል ከዘጠና ፐርሰንት በላይ የምንሆነው አማራዎች ነን። የሥርዓቱ አገልጋይ በመሆን ፈንታም ሙያችንን እና ሕዝባችንን በማክበራችን ብሎም አማራ በመሆናችን እጅግ በርካታ ኢ-ሠብአዊ ድርጊት እየተፈጸመብን ነው። እንዲያም ሆኖ ግን በማንነት ላይ የተመሠረተ የትኛውም ጥቃት የበለጠ ሊያጠነክረኝ እንጂ ሊሰብረኝ አይችልም።"
በጣም ነው የማከብርህ ክንዴ!
14 349
በየሩብ ዓመቱ ከእጅሽ ላይ ካቴና እያጠለቀ ሲያሰቃይሽ የነበረው አካል "ጀግና ሴት" ሲያሳድድ መክረሙን ተረድቶ ከአበባ ጉንጉን ጋር ቦሌ መገኘት ነበረበት። 😁
እንኳን በሰላም መጣሽ ውዷ እኅቴ
14 349
ከስምንት ወር በፊት ይሄንን ትንቢት መጻፌን የምታስታውሱ ስንቶቻችሁ ናችሁ?😁
ማርክ ማይ ወርድ!
አሳዬ ደርቤ
የአራት ኪሎው መንግሥት ወደ ፈላጭ ቆራጭነት ለመሸጋገርና በወልቃይት መሬት ላይ ለመደራደር ሲያስብ አብን እና ብአዴን የእቅዱ ተገዢ ሆነው ደስ አሰኙት፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ በሶሻል ሚዲያው መድረክ ሕዝባቸውን የሚያነቁ ጦማሪዎችና በጦር ሜዳ ላይ የሚዋደቁ ወጣቶች እንቅፋት ሆነው ታዩት፡፡
እርሱም አለ…
‹‹በወልቃይት ማንነት ዙሪያ ለመደራደርም ሆነ አማራን ለማስገበር የጌታቸው ረዳን ሐሳብ መተግበር ግድ ይላል፡፡ ይሄውም የአማራን ልሳኖችን እና ክንዶች የመስበር ዘመቻ 'ሕግ ማስከበር' ይባል፤››
ከዚህም ውሳኔ በኋላ ከላይ የተዘረዘሩትን ኃይሎች ጠርቶ ወረቀትና ገንዘብ ካቀበላቸው በኋላ "ሕግ አስከብሩ›› አላቸው።
እነርሱም ቦርጫቸውን እንደ ጠረጴዛ በመጠቀም የተሰጣቸውን ወረቀት ካስደገፉበት በኋላ ‹‹ጽንፈኛ›› በሚል ርዕስ ‹‹እንቢተኛ እና ሐቀኛ›› የአማራ ልጆችን ሥም መጻፍ ጀመሩ፡፡ እናም አሁን ላይ ፦
➔አንዳንድ የአብን አመራሮች በብአዴን የሚታፈኑ የአማራ ልጆችን እየጠቆሙ ነው፡፡
➔አንዳንድ ተከፋይ የአማራ ወመኔዎች ‹‹ወገኔ›› የሚሉትን ሕዝብ ለአፈና ዳርገው ‹‹ወያኔ›› የሚሉትን ጠላት እየጠበቁ ነው፡፡
➔አብዛኛው የአማራ ሙሕራን እና ፖለቲከኞች ‹‹ተደራጅ›› ብለው ሲቀሰቅሱት የኖሩት ፋኖ ሲሳደድ እያዩ ‹‹ሕግ እንዲከበር እንፈልጋለን፡፡ በወልቃይት ላይ ለመደራደር ያሰባችሁ ቀን ግን እንጣላለን›› እያሉ ነው፡፡
ይሄውም የመጀመሪያ ምዕራፍ ‹‹የሕግ ማስከበር›› ዘመቻ በስኬት መጠናቀቅ ከቻለ ሁለተኛው ምዕራፍ ‹‹ሰላም አስከባሪ›› የሚል ይሆናል፡፡ እናም ‹‹በአንዳንድ አካባቢዎች የሚነሱ የማንነት ጥያቄዎች መልስ እስኪያገኙ ድረስ በፌደራል መንግሥትና በኮማንድ ፖስት ሊተዳደሩ ይገባል›› መባል ይጀመራል፡፡
ያን ጊዜም ከላይ የተጠቀሱት ተላላኪ ኃይሎች ስምምነታቸውን ገልጸው ከወጡ በኋላ ለይምሰል ያህል ከሕዝብ ጎን ቆመው ቁጣቸውንና ተቃውሟቸውን እንዲገልጹ ይፈቀድላቸዋል፡፡
የሕዝብ ጠበቃና ጠባቂ የሆኑ ወጣቶች ወንጀለኛ እና ጽንፈኛ ተብለው እየተመረጡ ሲታፈኑ በዝምታው አማካኝነት ለዘብተኛ መሆኑን ሲገልጽ የከረመው የአማራ ሙሕርም በብልጽግና ውሳኔ የመናደድ መብቱ ይከበርለታል።
ከወልቃይት ምድርም ‹‹ማንነቴን የምትወስን አንተ ማን ነህ›› የሚል ትግል ይቀጣጠላል፡፡ ‹‹የወገን ያለህ›› የሚል ቃልም ይሰማል፡፡ ሆኖም ግን ያ ጊዜ እንደሚመጣ አውቀው በሸዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ሲደራጁ የከረሙ ፋኖዎች ለአፋና እና ለብተና የተዳረጉ በመሆናቸው ፈጥኖ የሚደርስ ኃይል አይኖርም፡፡
ከዚያ በማስከተል በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ የታፈኑ ሁሉ ያለምንም ፍርድ በነጻ ይለቀቃሉ፡፡ ከእነዚህ መሃከል አብዛኞቹ ትግላቸውን ሲቀጥሉ አንዳንዶቹም ዝምታን ተምረው ይወጣሉ፡፡
አሳሪዎቹ ደግሞ የሚታሠሩበት ቀን እስኪመጣ ድረስ የእነሱ ሕልውና በብልጽግና እድሜ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ተረድተው የህውሓትና የመንግሥት ጋብቻ ሲፈጸም እልልታቸውን ያቀልጣሉ። ‹‹የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም›› በሚል አቋምም ዛሬ ላይ የንቁ ዜጎች ማሸማቀቂያ ካደረጉት ጠላት ጎን ተሰልፈው ሕዝባቸው ላይ ይዘምታሉ፡፡
ይህ ቀን እንዳይመጣ የሚሹ ወገኖች ግን አሁን ላይ እንቅልፍ በተጫጫነው ክልል ውስጥ ቆመው ቀን እና ሌሊት በመታገል ላይ ይገኛሉ። "አፈናው ይቁም" ይላሉ።
14 349
"ነፍጠኛ" እየተባሉ በጥፊ ሲጠፈጠፉና ከንጹሐን ጋር ሲጨፈጨፉ የከረሙ የሃይማኖት አባቶች "የአማራ ልዩ ሃይል ቢጠፋም እኛ አባቶቻችሁ እያለን ማንም አይነካችሁ" በሚል ምልጃ ሕዝብን የማስተኛት ሥራ እየሠሩ ነው።
እናም ለእኒህ አባቶች የምንሰጠው መልስ..."ከእኛ በፊት ሲጨፈጭፉን የከረሙ አሸባሪዎችን ትጥቅ አስፈትታችሁ ከሥጋትና ከጥቃት ገላግሉን" የሚል መሆን አለበት።
14 349
የመስከረም አበራ የስልክ ንግግር የሚባለውና በINSA በኩል ተለቀቀ የሚባለው የድምጽ ቅጂ የእርሷ ቢሆን እንኳን በሚዲያ ከምታወራው የተለየ ነገር የያዘ አይደለም። በዚያ ላይ ደግሞ ድምጽ ማቀናበር ከባድ አይደለም።
በተረፈ መንግሥት ተብዬው አካል የግለሰቦችን ስልክ ከመጥለፍ ባለፈ በየሪዞርቱና በየሆቴሉ የስለላ ካሜራ አስገጥሞ የዜጎችን ብቻ ሳይሆን የእራሱን ባለሥልጣናትም ጭምር ገመና እየሰበሰበ ብላክ ሜይል እንደሚያደርግ የታወቀ ነገር ነው።
ውርጋጥ መራሹ ሥርዓት ከትላልቅ ሆቴሎች መኝታ ቤት ሳይቀር ካሜራ አስገጥሞ የወሲብ ትዕይንት ሲከታተል የሚያድር አሳፋሪ ስብስብ መሆኑን ካወቅን ቆየን። (ለዚያም ነው "ያገራችን ጉዳይ ያገባናል" በሚል ንግግራቸው የሚታወቁ ፖለቲከኞች ሁሉ አንገት ደፍተው የቀሩት 😁
14 349
"ፌደራሊስት" ብሎ እራሱን ለሚጠራው ጨፍላቂ መንጋ
"አቶ ልደቱ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ከእኛ የተለየች አንዲት ሐሳብ አነሳብን" ብለው በጸረ ሕዝብነት የፈረጁትና የሞት ፍርድ የፈረዱበት 'ፌደራሊስት' ተብዬዎች "ኤርሚያስ ከኢትዮ 360 የለቀቀው ለየት ያለ ሐሳብ ማስተናገድ ባለመቻላችሁ ነው" እያሉን ነው።
እኔ ግን እላለሁኝ...
ኤርሚያስ ይሄን ያህል ጊዜ መቆየት የቻለው በወልቃይትና ራያ ማንነት ዙሪያም ሆነ በሄዊ ዙሪያ የሚያራምደውን ሐሳብ ማስተናገድ በመቻላችን ነው።.
በተረፈ ኤርሚ በኡቡንቱም ሆነ በርዕዮት ሚዲያ በተቀጠረ ቅጽበት ስለ አዲስ አበባ ያለውን አቋም ካልቀየረ በማግስቱ "ሐጣ*ራው" ብላችሁ እንደምታፈናቅሉት ጥርጥር የለውም። 😁
14 349
የኤርሚን ሥም ቀርቶ የሌላውንም ቢሆን ያለምክንያት የማንሳት ፍላጎት የለንም። እናም ባለፈው እንደተነበይነው😁 ኤርሚ ከኢትዮ 360 ለቅቋል። በቀጣይ በሌላ ሚዲያ እንደሚመጣና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ¿ ክቡር ዘበኛ ሆኖ የኖረበት ካምፕ ላይ ሲዘምት እንደሚታይ አልጠራጠርም።
ምክንያቱም....
የኤርሚን ሥነልቦና ጠንቅቄ ከተረዳሁ በጣም ቆየሁኝ። በተረፈ ...
የብልጽግና እና የሄዊ ጋብቻ ከተፈጸመበት ጊዜ አንስቶ ኤርሚያስና ሽመልስ በተመሳሳይ ማሊያ መሮጥ ጀምረዋል።
መልካም ጊዜ ይሁንልህ!!
14 349
"እንዴ ግስላ የተቆጣውን ሕዝብ አዘናግታችሁ ያሰብኩትን ዘመቻ የማታሳኩ ከሆነ ከወንበር አንስቼ ወደ መቃብር እንደማወርዳችሁ እወቁ" የሚል ዛቻ ካስተናገዱ የብአዴን አመራሮች "ሕዝቤ ሆይ በሶሻል ሚዲያ የሚወራውን አትስማ" ከማለት ባለፈ "ሕዝቤ ሆይ ጥያቄህን ሰምተናል" የሚል መልስ አይጠበቅም።
አሳዬ ደርቤ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
