fa
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Assaye Derbie

کانال Assaye Derbie (@asayede) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 351 مشترک است و جایگاه 2 646 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 354 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 351 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 22 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -133 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.76% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 11.78% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 562 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 691 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 34 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 23 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

14 351
مشترکین
-324 ساعت
-387 روز
-13330 روز
آرشیو پست ها
"ጸረ አማራ ኃይሎች ሁሉ ወዳጆች ናቸው"⁉️ የማይቀየረው የሄዊ ፖለቲካዊ ድንጋጌ❗️❗️ ምንም እንኳን በአማራ እና በኤርትራ መሀከል የተፈጠረ ጥምረት ባይኖርም ገዢው ፓርቲ ግን "ህውሓትን እና ብአዴንን በማስታረቅ የኤርትራ መንግሥትን እና አማራን ማራራቅ" የሚል እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ ግን አብዛኛው የአማራ ኤሊት ከሥርዓት ተሸካሚነት እራሱን ነጻ ባወጣ ማግሥት "ፋሽሽት ነህ" ሲሉት የኖሩትን መሪ "መንግሥት ብቻ ሳትሆን አማልክትም ጭምር ነህ" በሚል ውዳሴ ጫንቃቸውን ለሸክም አዘጋጅተው ወደ አራት ኪሎ የመጡት የሄዊ አመራሮች.... ይሄኛው የብልጽግና እቅድ በተሳካ ማግስትም አስመራ ገብተው አማራን ሲያራክሱና ኢሳያስን ሲያወድሱ መታየታቸው አይቀሬ ነው። ምክንያቱም የህውሓት ፖለቲካ "ከአማራ ጋር የተቃቃሩ ኃይሎች ሁሉ ወዳጆች ናቸው" በሚል የቁሞ ቀር ፍልስፍና የሚመራ ነው። ለዚያም ነው ትናንት "እርኩስ" ያደረጉትን አካል ዛሬ "ቅዱስ" ለማለት የደፈሩት...

የመብራት መሠረተ ልማቶች በመበጣጠሳቸው የተነሳ የሱዳን ወፍጮ ቤቶች ሥራ ስላቆሙ አምሳ ሺህ ኩንታሉ ስንዴ ተፈጭቶ ቢላክላቸው....😂😂
የመብራት መሠረተ ልማቶች በመበጣጠሳቸው የተነሳ የሱዳን ወፍጮ ቤቶች ሥራ ስላቆሙ አምሳ ሺህ ኩንታሉ ስንዴ ተፈጭቶ ቢላክላቸው....😂😂

ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን! https://www.youtube.com/live/2dD3NcQdIXo?feature=share
ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን! https://www.youtube.com/live/2dD3NcQdIXo?feature=share

ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን! https://www.youtube.com/live/6CTE2LAADWk?feature=share
ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን! https://www.youtube.com/live/6CTE2LAADWk?feature=share

photo content

ኢንተርኔት ከተዘጋ ሶስት ወር ሊሞላው ነው። የወይዘሮ ፍሬሕይወት የሥራ ድርሻም የአማራዎችን ስልክ ማስጠለፍና የግለሰቦችን ገበና መበርበር ሁኗል።
ኢንተርኔት ከተዘጋ ሶስት ወር ሊሞላው ነው። የወይዘሮ ፍሬሕይወት የሥራ ድርሻም የአማራዎችን ስልክ ማስጠለፍና የግለሰቦችን ገበና መበርበር ሁኗል።

እንደ ሽፍታ ጋዜጠኞችን እና አክቲቪስቶችን በየወሩ እያገቱ የዋስትና ገንዘብ መሰብሰብ ያሳፍራል። ወንድማችን የ20 ሺህ ብር ዋስ ተጠይቋል።
እንደ ሽፍታ ጋዜጠኞችን እና አክቲቪስቶችን በየወሩ እያገቱ የዋስትና ገንዘብ መሰብሰብ ያሳፍራል። ወንድማችን የ20 ሺህ ብር ዋስ ተጠይቋል።

በወርሐ መስከረም ከእኔ፣ ከጎበዜ ሲሳይና ከመዓዛ ጋር ታስሮ የነበረው፣ በወያኔ ጊዜ በሐሰት የሽብር ክስ ከሰባት ዓመት በላይ የታሠረው፣ የመይሳውን ሥነ ልቦና ይዞ ጎንደር ምድር ላይ የበቀለው፣ በአማ
በወርሐ መስከረም ከእኔ፣ ከጎበዜ ሲሳይና ከመዓዛ ጋር ታስሮ የነበረው፣ በወያኔ ጊዜ በሐሰት የሽብር ክስ ከሰባት ዓመት በላይ የታሠረው፣ የመይሳውን ሥነ ልቦና ይዞ ጎንደር ምድር ላይ የበቀለው፣ በአማራነቱ የማይደራደረው፣ በጋዜጠኝነት ዘርፍ በሠራው ሥራ ዓለም አቀፍ ሽልማት የሚገባው፣ ጋዜጠኛ ብቻ ሳይሆን ሐቀኛ በመሆኑ የሚታወቀው፣ ከሰሞኑን በአማራ ተወላጅ የሆኑ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ላይ በተካሄደው አፈና እንደ ጌትነት አሻግሬና ዳዊት በጋሻው ካሉ ብርቱ ጋዜጠኞች ጋር የታሠረው.... ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ ዛሬ ፍርድ ቤት በርቦ ችሎት ላይ ከተናገረው የተወሰደ... “እስር ቤቱን ከሞላነውና ችሎት ላይ ከቀረብነው መሀከል ከዘጠና ፐርሰንት በላይ የምንሆነው አማራዎች ነን። የሥርዓቱ አገልጋይ በመሆን ፈንታም ሙያችንን እና ሕዝባችንን በማክበራችን ብሎም አማራ በመሆናችን እጅግ በርካታ ኢ-ሠብአዊ ድርጊት እየተፈጸመብን ነው። እንዲያም ሆኖ ግን በማንነት ላይ የተመሠረተ የትኛውም ጥቃት የበለጠ ሊያጠነክረኝ እንጂ ሊሰብረኝ አይችልም።" በጣም ነው የማከብርህ ክንዴ!

በየሩብ ዓመቱ ከእጅሽ ላይ ካቴና እያጠለቀ ሲያሰቃይሽ የነበረው አካል "ጀግና ሴት" ሲያሳድድ መክረሙን ተረድቶ ከአበባ ጉንጉን ጋር ቦሌ መገኘት ነበረበት። 😁 እንኳን በሰላም መጣሽ ውዷ እኅቴ
በየሩብ ዓመቱ ከእጅሽ ላይ ካቴና እያጠለቀ ሲያሰቃይሽ የነበረው አካል "ጀግና ሴት" ሲያሳድድ መክረሙን ተረድቶ ከአበባ ጉንጉን ጋር ቦሌ መገኘት ነበረበት። 😁 እንኳን በሰላም መጣሽ ውዷ እኅቴ

photo content

ከስምንት ወር በፊት ይሄንን ትንቢት መጻፌን የምታስታውሱ ስንቶቻችሁ ናችሁ?😁 ማርክ ማይ ወርድ! አሳዬ ደርቤ የአራት ኪሎው መንግሥት ወደ ፈላጭ ቆራጭነት ለመሸጋገርና በወልቃይት መሬት ላይ ለመደራደር ሲያስብ አብን እና ብአዴን የእቅዱ ተገዢ ሆነው ደስ አሰኙት፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ በሶሻል ሚዲያው መድረክ ሕዝባቸውን የሚያነቁ ጦማሪዎችና በጦር ሜዳ ላይ የሚዋደቁ ወጣቶች እንቅፋት ሆነው ታዩት፡፡ እርሱም አለ… ‹‹በወልቃይት ማንነት ዙሪያ ለመደራደርም ሆነ አማራን ለማስገበር የጌታቸው ረዳን ሐሳብ መተግበር ግድ ይላል፡፡ ይሄውም የአማራን ልሳኖችን እና ክንዶች የመስበር ዘመቻ 'ሕግ ማስከበር' ይባል፤›› ከዚህም ውሳኔ በኋላ ከላይ የተዘረዘሩትን ኃይሎች ጠርቶ ወረቀትና ገንዘብ ካቀበላቸው በኋላ "ሕግ አስከብሩ›› አላቸው። እነርሱም ቦርጫቸውን እንደ ጠረጴዛ በመጠቀም የተሰጣቸውን ወረቀት ካስደገፉበት በኋላ ‹‹ጽንፈኛ›› በሚል ርዕስ ‹‹እንቢተኛ እና ሐቀኛ›› የአማራ ልጆችን ሥም መጻፍ ጀመሩ፡፡ እናም አሁን ላይ ፦ ➔አንዳንድ የአብን አመራሮች በብአዴን የሚታፈኑ የአማራ ልጆችን እየጠቆሙ ነው፡፡ ➔አንዳንድ ተከፋይ የአማራ ወመኔዎች ‹‹ወገኔ›› የሚሉትን ሕዝብ ለአፈና ዳርገው ‹‹ወያኔ›› የሚሉትን ጠላት እየጠበቁ ነው፡፡ ➔አብዛኛው የአማራ ሙሕራን እና ፖለቲከኞች ‹‹ተደራጅ›› ብለው ሲቀሰቅሱት የኖሩት ፋኖ ሲሳደድ እያዩ ‹‹ሕግ እንዲከበር እንፈልጋለን፡፡ በወልቃይት ላይ ለመደራደር ያሰባችሁ ቀን ግን እንጣላለን›› እያሉ ነው፡፡ ይሄውም የመጀመሪያ ምዕራፍ ‹‹የሕግ ማስከበር›› ዘመቻ በስኬት መጠናቀቅ ከቻለ ሁለተኛው ምዕራፍ ‹‹ሰላም አስከባሪ›› የሚል ይሆናል፡፡ እናም ‹‹በአንዳንድ አካባቢዎች የሚነሱ የማንነት ጥያቄዎች መልስ እስኪያገኙ ድረስ በፌደራል መንግሥትና በኮማንድ ፖስት ሊተዳደሩ ይገባል›› መባል ይጀመራል፡፡ ያን ጊዜም ከላይ የተጠቀሱት ተላላኪ ኃይሎች ስምምነታቸውን ገልጸው ከወጡ በኋላ ለይምሰል ያህል ከሕዝብ ጎን ቆመው ቁጣቸውንና ተቃውሟቸውን እንዲገልጹ ይፈቀድላቸዋል፡፡ የሕዝብ ጠበቃና ጠባቂ የሆኑ ወጣቶች ወንጀለኛ እና ጽንፈኛ ተብለው እየተመረጡ ሲታፈኑ በዝምታው አማካኝነት ለዘብተኛ መሆኑን ሲገልጽ የከረመው የአማራ ሙሕርም በብልጽግና ውሳኔ የመናደድ መብቱ ይከበርለታል። ከወልቃይት ምድርም ‹‹ማንነቴን የምትወስን አንተ ማን ነህ›› የሚል ትግል ይቀጣጠላል፡፡ ‹‹የወገን ያለህ›› የሚል ቃልም ይሰማል፡፡ ሆኖም ግን ያ ጊዜ እንደሚመጣ አውቀው በሸዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ሲደራጁ የከረሙ ፋኖዎች ለአፋና እና ለብተና የተዳረጉ በመሆናቸው ፈጥኖ የሚደርስ ኃይል አይኖርም፡፡ ከዚያ በማስከተል በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ የታፈኑ ሁሉ ያለምንም ፍርድ በነጻ ይለቀቃሉ፡፡ ከእነዚህ መሃከል አብዛኞቹ ትግላቸውን ሲቀጥሉ አንዳንዶቹም ዝምታን ተምረው ይወጣሉ፡፡ አሳሪዎቹ ደግሞ የሚታሠሩበት ቀን እስኪመጣ ድረስ የእነሱ ሕልውና በብልጽግና እድሜ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ተረድተው የህውሓትና የመንግሥት ጋብቻ ሲፈጸም እልልታቸውን ያቀልጣሉ። ‹‹የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም›› በሚል አቋምም ዛሬ ላይ የንቁ ዜጎች ማሸማቀቂያ ካደረጉት ጠላት ጎን ተሰልፈው ሕዝባቸው ላይ ይዘምታሉ፡፡ ይህ ቀን እንዳይመጣ የሚሹ ወገኖች ግን አሁን ላይ እንቅልፍ በተጫጫነው ክልል ውስጥ ቆመው ቀን እና ሌሊት በመታገል ላይ ይገኛሉ። "አፈናው ይቁም" ይላሉ።

"ነፍጠኛ" እየተባሉ በጥፊ ሲጠፈጠፉና ከንጹሐን ጋር ሲጨፈጨፉ የከረሙ የሃይማኖት አባቶች "የአማራ ልዩ ሃይል ቢጠፋም እኛ አባቶቻችሁ እያለን ማንም አይነካችሁ" በሚል ምልጃ ሕዝብን የማስተኛት ሥራ እየሠሩ ነው። እናም ለእኒህ አባቶች የምንሰጠው መልስ..."ከእኛ በፊት ሲጨፈጭፉን የከረሙ አሸባሪዎችን ትጥቅ አስፈትታችሁ ከሥጋትና ከጥቃት ገላግሉን" የሚል መሆን አለበት።

የመስከረም አበራ የስልክ ንግግር የሚባለውና በINSA በኩል ተለቀቀ የሚባለው የድምጽ ቅጂ የእርሷ ቢሆን እንኳን በሚዲያ ከምታወራው የተለየ ነገር የያዘ አይደለም። በዚያ ላይ ደግሞ ድምጽ ማቀናበር ከባድ አይደለም። በተረፈ መንግሥት ተብዬው አካል የግለሰቦችን ስልክ ከመጥለፍ ባለፈ በየሪዞርቱና በየሆቴሉ የስለላ ካሜራ አስገጥሞ የዜጎችን ብቻ ሳይሆን የእራሱን ባለሥልጣናትም ጭምር ገመና እየሰበሰበ ብላክ ሜይል እንደሚያደርግ የታወቀ ነገር ነው። ውርጋጥ መራሹ ሥርዓት ከትላልቅ ሆቴሎች መኝታ ቤት ሳይቀር ካሜራ አስገጥሞ የወሲብ ትዕይንት ሲከታተል የሚያድር አሳፋሪ ስብስብ መሆኑን ካወቅን ቆየን። (ለዚያም ነው "ያገራችን ጉዳይ ያገባናል" በሚል ንግግራቸው የሚታወቁ ፖለቲከኞች ሁሉ አንገት ደፍተው የቀሩት 😁

ጧሒር መሐመድ.... ከሌሎች የአብን አመራሮች በተሻለ መልኩ ከሕዝብ ጎን ተሰልፎ የተገኘ!!
ጧሒር መሐመድ.... ከሌሎች የአብን አመራሮች በተሻለ መልኩ ከሕዝብ ጎን ተሰልፎ የተገኘ!!

photo content

"ፌደራሊስት" ብሎ እራሱን ለሚጠራው ጨፍላቂ መንጋ "አቶ ልደቱ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ከእኛ የተለየች አንዲት ሐሳብ አነሳብን" ብለው በጸረ ሕዝብነት የፈረጁትና የሞት ፍርድ የፈረዱበት 'ፌደራሊስት
"ፌደራሊስት" ብሎ እራሱን ለሚጠራው ጨፍላቂ መንጋ "አቶ ልደቱ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ከእኛ የተለየች አንዲት ሐሳብ አነሳብን" ብለው በጸረ ሕዝብነት የፈረጁትና የሞት ፍርድ የፈረዱበት 'ፌደራሊስት' ተብዬዎች "ኤርሚያስ ከኢትዮ 360 የለቀቀው ለየት ያለ ሐሳብ ማስተናገድ ባለመቻላችሁ ነው" እያሉን ነው። እኔ ግን እላለሁኝ... ኤርሚያስ ይሄን ያህል ጊዜ መቆየት የቻለው በወልቃይትና ራያ ማንነት ዙሪያም ሆነ በሄዊ ዙሪያ የሚያራምደውን ሐሳብ ማስተናገድ በመቻላችን ነው።. በተረፈ ኤርሚ በኡቡንቱም ሆነ በርዕዮት ሚዲያ በተቀጠረ ቅጽበት ስለ አዲስ አበባ ያለውን አቋም ካልቀየረ በማግስቱ "ሐጣ*ራው" ብላችሁ እንደምታፈናቅሉት ጥርጥር የለውም። 😁

የኤርሚን ሥም ቀርቶ የሌላውንም ቢሆን ያለምክንያት የማንሳት ፍላጎት የለንም። እናም ባለፈው እንደተነበይነው😁 ኤርሚ ከኢትዮ 360 ለቅቋል። በቀጣይ በሌላ ሚዲያ እንደሚመጣና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ¿ ክ
የኤርሚን ሥም ቀርቶ የሌላውንም ቢሆን ያለምክንያት የማንሳት ፍላጎት የለንም። እናም ባለፈው እንደተነበይነው😁 ኤርሚ ከኢትዮ 360 ለቅቋል። በቀጣይ በሌላ ሚዲያ እንደሚመጣና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ¿ ክቡር ዘበኛ ሆኖ የኖረበት ካምፕ ላይ ሲዘምት እንደሚታይ አልጠራጠርም። ምክንያቱም.... የኤርሚን ሥነልቦና ጠንቅቄ ከተረዳሁ በጣም ቆየሁኝ። በተረፈ ... የብልጽግና እና የሄዊ ጋብቻ ከተፈጸመበት ጊዜ አንስቶ ኤርሚያስና ሽመልስ በተመሳሳይ ማሊያ መሮጥ ጀምረዋል። መልካም ጊዜ ይሁንልህ!!

"እንዴ ግስላ የተቆጣውን ሕዝብ አዘናግታችሁ ያሰብኩትን ዘመቻ የማታሳኩ ከሆነ ከወንበር አንስቼ ወደ መቃብር እንደማወርዳችሁ እወቁ" የሚል ዛቻ ካስተናገዱ የብአዴን አመራሮች "ሕዝቤ ሆይ በሶሻል ሚዲያ የሚወራውን አትስማ" ከማለት ባለፈ "ሕዝቤ ሆይ ጥያቄህን ሰምተናል" የሚል መልስ አይጠበቅም። አሳዬ ደርቤ