Joseph Math Tutor
前往频道在 Telegram
Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580
显示更多1 755
订阅者
-124 小时
+507 天
+8630 天
帖子存档
1 756
+1
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ በታሰበው ዕቅድ ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሊያደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ መንግሥት ዕቅድ መያዙ ይታወቃል፡፡
በዕቅዱ ላይ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት ቢደረግም፤ ከክልሎች፣ ከትምህርት ቤቶች እና ከፀጥታ አካላት ጋር ውይይት አለመካሔዱን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
መንግሥት "ዕቅዱ ተግባራዊ ይሆናል ብሎ እስካሁን ውሳኔ አለማሳለፉን" የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በቀጣይ ሳምንታት ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና የሕዝብ ተወካዮችን ጨምሮ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ይደረጋል ብለዋል፡፡
ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በተደረገው ውይይት ከሎጂስቲክስ እና ከአካዳሚክ ጉዳዮች ጋር እንዴት ይጣጣማል በሚለው ላይ ጥያቄ ከማቅረብ ውጪ፤ "ሀሳቡ ተግባራዊ ቢሆን እንደሚደግፉት" መግለጻቸውን ጠቅሰዋል።
ከውይይቱ በኋላ ሀሳቡ ለፓርላማ እንደሚቀርብና የራሱ የሆነ ተቋም ተቋቁሞለት ሕግ ይወጣለታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኮራ አስረድተዋል። ዕቅዱ ተቀባይነት ካገኘ በ2019 ዓ.ም እንደሚተገበር ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ሆኖም በውይይቱ ወቅት ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የትምህርት ማኅበረሰቡ ዕቅዱን ካልፈለገው የሚቀርበት ሁኔታ እንዳለም ጠቁመዋል፡፡
#ሪፖርተር
1 756
#URGENT 🔔
#ATTENTION‼️ #WARNING ⚠️
ባይረጋገጥም አንድ መረጃ በሰፊው እየተሰራጨ ይገኛል። ይህም የቴሌግራም Privacy & Security ላይ ችግር ተፈጥሯል የሚል መረጃ ሲሆን random የሆኑ አካውንቶች ፣ ግሩፖች እና ቻናሎች target እየተደረጉ ነው እየተባለ ነው። ተጨማሪ መረጃ ከፎቶው ላይ መመልከት ትችላላችሁ።
ስለዚህ አሁኑኑ ይህንን አድርጉ 👇
1. የአካውንታችሁን profile picture ማን ማየት እንዳለበት የምታስተካክሉበት setting ላይ My Contacts ወይም Nobody አድርጉት። ወይም ደግሞ ለጊዜው አጥፉት እና ባዶ ይቀመጥ። እዛው setting ላይ እንደ ስልክ ቁጥር ያሉ መረጃዎችንም ሌላ ሰው እንዳያይ አድርጉ።
2. የአካውንታችሁን Username ቀይሩ።
3. ቻናል ወይም ግሩፕ ካላችሁ cover ፎቶአቸውን አጥፉ።
4. የአካውንታችሁን password ቀይሩ።
5. Two step verification አብሩ። Recovery email ካላስገባችሁ አስገቡ እናም ሌላ ማድረግ አለብኝ የምትሉትን ነገር አድርጉ።
እውነት እንደሆነ አልተረጋገጠም። ነገርግን እውነት ሊሆን ስለሚችል መጠንቀቁ አይከፋም። እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ ምንም ችግር የማይፈጠር ከሆነ ሁሉንም ወደቦታው ትመልሳላችሁ። እኛም አዲስ መረጃ ለማግኘት ጥረት እናደርጋለን።
#SHARE‼️
1 756
+1
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ይሰጣል። - ትምህርት ሚኒስቴር
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገልፀዋል፡፡
ባለፉት ሁለት ዓመታት የመልቀቂያ ፈተናው በወረቀት እና በበይነ መረብ ሲሰጥ እንደነበር፣ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግማሽ ዓመት አፈጻጸም መድረክ ላይ የተገኙት ሚኒስትሩ አስታወሰዋል፡፡
ዘንድሮ ፈተናውን ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት የተለያዩ ግብዓቶች ለክልሎች ድጋፍ እየተደረገ ሲሆን፤ በፈተና ጣቢያዎች በቂ የኢንተርኔት አቅርቦት እንዲኖር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመነጋገር ይሠራል ብለዋል።
ክልሎች በቂ ኮምፒዩተር፣ ኔትዎርክ እና አማራጭ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በትኩረት እንዲዘጋጁ ያሳሰቡት ሚኒስትሩ፤ ለተማሪዎች በቂ ስልጠና መስጠት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
በዚህም የክልል እና የከተማ መስተዳድሮች ሀገር አቀፍ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን እንደሚሰጥ አውቀው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል።
በ2017 ዓ.ም ለመልቀቂያ ፈተናው ከተቀመጡ 585,882 ተማሪዎች መካከል 134,609 ወይም 23% ያህሉ ፈተናውን በኦንላይን የወሰዱ መሆናቸው ይታወሳል፡፡
1 756
Repost from N/a
+3
Everything is well prepared.
The tutor will start on February 03/18 (February 10/26)
1 756
Repost from N/a
+3
Students Enrolled in Applied Math II Tutor
Please check your name
1 756
የአለማችን ከፍተኛ የትምህርት ደረጃ ያለው ሰው ከአፍሪካ #ሴራሊዮን 🇸🇱 ነው።
●የሴራሊዮኑ #አብዱልከሪም_ባንጉራ (ዶ/ር) በምድር ላይ በጣም የተማረ ሰው ነው ተብሎ ይታሰባል። ዶ/ር አብዱልከሪም ደራሲ፣ የአካዳሚክ አስተዳዳሪ፣ ተመራማሪ እና ሳይንቲስት ናቸው።
● በአለም አቀፍ ጥናቶች ቢኤ ይዟል፣ በአለም አቀፍ ጉዳዮች ኤም.ኤ.፣ በሊንጉስቲክስ ኤም.ኤስ፣ በፖለቲካል ሳይንስ ፒኤች.ዲ፣ በልማት ኢኮኖሚክስ ፒኤች.ዲ፣ በሊንጉስቲክስ ፒኤች.ዲ ፣ በኮምፒውተር ሳይንስ ፒኤች.ዲ፣ እና በሂሳብ ፒኤች.ዲ ነው ያለው።
●ታላቁ ዶክተር 35 መጽሃፎችን እና ከ250 በላይ ምሁራዊ ጽሑፎችን አዘጋጅቷል ወይም አርትእ አድርጓል።
ዶክተሩ እንግሊዘኛ፣ ተምኔ፣ ሜንዴ፣ ክሪዮ፣ ፉላ፣ ኮኖ፣ ሊምባ፣ ሸርብሮ፣ ኪስዋሂሊ፣ ስፓኒሽ፣ ጣሊያንኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ አረብኛ፣ ዕብራይስጥ፣ ጀርመንኛ፣ ስዊድንኛ እና አቀላጥፎ የሚያውቅ ኪኩዩን ጨምሮ 19 ቋንቋዎችን መናገር ይችላል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
