ch
Feedback
AASTU-ECSF

AASTU-ECSF

前往频道在 Telegram

Evangelical Christian Students' Fellowship at AASTU CBE: 1000656422959 Daniel Kebede and/or Samuel Tesfaye Telebirr: 0931106178 Daniel Kebede Stay tuned via: @galleryaastuecsfBot @souceoflifeBot @AASTU_Anony_Counseling_bot @i4u_contact_bot

显示更多
4 472
订阅者
+524 小时
+27
+3130
帖子存档
መልካም አዳር fams 🥰

#Last_Message
ምሳሌ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌዎች፤ ² ጥበብንና ተግሣጽን ለማወቅ፥ የእውቀትንም ቃል ለማስተዋል፥ ³ የጥበብን ትምህርት ጽድቅንና ፍርድን ቅንነትንም ለመቀበል፥ ⁴ ብልሃትን ለአላዋቂዎች ይሰጥ ዘንድ ለጐበዛዝትም እውቀትንና ጥንቃቄን፥ ⁵ ጠቢብ እነዚህን ከመስማት ጥበብን ይጨምራል፥ አስተዋይም መልካም ምክርን ገንዘቡ ያደርጋል። ⁶ ምሳሌንና ትርጓሜን የጠቢባንን ቃልና የተሸሸገውን ነገር ለማስተዋል። ⁷ የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ።
ለአላዋቂው ዕውቀትን ፣ ለዳኛው ልከኛ ፍርድን ፣ ለመምህሩ የተቃና አስተምሕሮ ፣ ለጠቢብም ተጨማሪ ጥበብ ሊሰጥ የሚቻለው የእግዚያብሔር ቃል ነው። በየትኛውም መደብ ለሚገኙ ሰዎች መልዕክት ያለው አፊዮተ እግዚያብሔር ያለበት ቅዱስ ቃሉ ነው።በክፍት ልብ ላነበበው ለማንም መልዕክት አለው። የሕይወት ምህዳሩ ለጠፋበት መንገድን የሚቀይስ ፣ በመከራ ለሚንገላወደው ልብን የሚያረጋው በሰላም ዓለም ውስ ውስጥ የሚከተው ይህ በመንፈስ የተለወሰ ቅዱሱ የእግዚያብሔር ቃል ነው። ስለዚህ ይህንን ሳምንት ለእግዚያብሔር ቃል አክብሮትን በመስጠት ከእግዚያብሔር አንዳች ደብዳቤ እንደተጻፈለት ሰው ከቅዱስ ቃሉ ጋር የምናሳልፍበት እንዲሆን መሻታችን ነው። ይህን ቅዱስ ቃል ከፍተን ባነበብነው ቁጥር አምላክ ለእኛ ማለት የፈለገውን ይናገረናል። ከዚህም የተነሳ ቢያንስ ከዚህች ጊዜ ጀምሮ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ያቆማችሁ ወደ ጥናታችሁ እንድትመለሱ ፣ ያልጀመራችሁ ደግሞ ከትንሽ እንድትጀምሩ፣ ከየት መጀመር እንዳለባችሁ ግራ የገባችሁ ደግሞ ቅድም በማስታወቅያ እንደተነገረው ከእኛ ጋር አንደኛ ሳሙኤልን በዚህ ሳምንት እንድታነቡ ይሁን። በእግዚያብሔር ቃል ፍቅር ጥፍት የምንልበት ጊዜ። አንብቡ እግዚያብሔርንም እወቁ! እንወዳችኋለን 🥰 ተባርኩ መልካም ሳምንት 🙌🏻 #እግዚአብሔርን_መፈለግ #በመመለስ #በፅድቅ_ኑሮ #በመታመን Follow AASTU ECSF On : Telegram | YouTube | Instagram | TikTok | CounselingBot | I4UBot

እንዲህ እንዲያ እያለን መረሃ ግብራችንን ወደ ማገባደድ ደርሰናል። እስካሁን አብራችሁን በመረሃ ግብሮች በሙሉ ስጻተፉ የነበራችሁ በሙሉ ተባረኩ 🙌🏻

#ማስታወቅያ 📌በዚህ ክረምት ሁላችንም በየፊናችን የምንወጥነው የየራሳችን ዕቅድ እንዳለን ይታወቃል። እንዲሁም ደግሞ እንደፌሎሺፕ በዚህ ክረምት ማለትም ሐምሌን እና ነሐሴን ጌታ ቢፈቅድ እና ብንኖር 1ኛ እና 2ተኛ ሳሙኤልን እንድናነብ አስበናል። በአጠቃላይ 55 ምዕራፎች ያሏቸው እነኚህ መጻሕፍትን በ60 ቀን ውስጥ ለመጨረስ ስላቀድን ኹላችሁም የዚህ Challenge ተካፋይ እንድትሆኑ በጌታ ፍቅር እናሳስባችኋለን። ታድያ ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የምናወጣቸውንም ጥያቄዎችን ሳይቀር ከዚሁ መጽሐፍ የምናወጣ ሲሆን ለቀጣይ ሳምንት ከ1ኛ ሳሙኤል ምዕራፍ 1~7 አንብበን እንድንገናኝ በጌታ ፍቅር እናሳስባችኋለን። 📌የInternshipአችሁንአስራት እያስገባችሁ ያላችሁ ልጆች ጌታ አብዝቶ ይባርካችሁ አሁንም ደግሞ ያላስገባችሁ ልጆች ጊዜ አልረፈደም እና አስገቡ ልንላችሁ እንወዳለን። 😁 📌በየሳምንቱ ለሚለቀቁት ላልተደረሱ የህዝቦች ክፍል መጸለያችሁን እንዳትዘነጉ። የምትጸልዩም ደግሞ ጌታ አምላክ ይባርካችሁ። 📌በመጨረሻም የትኛውም ዓይነት የጸሎት ርዕስ ያላችሁ ሰዎች በሙሉ ከስር ባለው Fellowshipኡ የTelegram Account መላክ ትችላላችሁ። @aastuecsfcontact #እግዚአብሔርን_መፈለግ #በመመለስ #በፅድቅ_ኑሮ #በመታመን Follow AASTU ECSF On : Telegram | YouTube | Instagram | TikTok | CounselingBot | I4UBot

👉🏼ሳልነግራችሁ የረሳሁት ደግሞ ቁጥሩ የሚሰራው ከጀርባ ወደፊት ሲሞላ ነው 😁 የሞላችሁ ምልክት ስጡን 🙏🏻

እስካሁን አብራችሁን ለነበራችሁ ስጦታ ስለሚገባችሁ ስጦታው እነሆ #Card_Number 10793997006243

#Winners 🥇 Eyosiyas Melkamu 1st year Engineering 🥈 Mintesnot Achaw 1st Year Engineering 🥉 Ezra Simon 5th Year Electromecha
#Winners 🥇 Eyosiyas Melkamu 1st year Engineering 🥈 Mintesnot Achaw 1st Year Engineering 🥉 Ezra Simon 5th Year Electromechanical 📌የመጀመሪያ ዓመቶች አልተቻላችሁም መሪነቱ ተቆናጣችሁታል😁። 📌የተሳተፋችሁትን በሙሉ ግን ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ 🙌🏻 #እግዚአብሔርን_መፈለግ #በመመለስ #በፅድቅ_ኑሮ #በመታመን Follow AASTU ECSF On : Telegram | YouTube | Instagram | TikTok | CounselingBot | I4UBot

#Book_Club 📚 📕 Don't Waste Your Life ✍️ John Piper
"What would it mean to waste my life? That was a burning question. Or, more positively, what would it mean to live well— not to waste life, but to . . . ? How to finish that sentence was the question. I was not even sure how to put the question into words, let alone what the answer might be. What was the opposite of not wasting my life? “To be successful in a career”? Or “to be maximally happy”? Or “to accomplish something great?” Or “to find the deepest meaning and significance”? Or “to help as many people as possible”? Or “to serve Christ to the full”? Or “to glorify God in all I do”? Or was there a point, a purpose, a focus, an essence to life that would fulfill every one of those dreams?" (Page 13)
IT IS BETTER TO LOSE OUR LIFE THAN TO WASTE IT! - (John Piper)
ጆን ፓይፐር በዚህ መፅሀፍ ውስጥ ለአማኝ ትልቁ አሳዛኝ ነገር ስጋዊ ሞት ሳይሆን፣ ሁሉን የሚያስጥል የክርስቶስ ፍቅር ግለት ሳይኖር የሚደረግ ኑሮ ነው ይለናል። ይህ መፅሐፍ አንባቢውን ምቾትንና ቸልተኝነትን ጥሎ ዘላለማዊ ዋጋ ላለው ዘላለማዊ ኑሮ እያንዳንዱን ቀን በማስተዋል እንዲኖር ይሞግታል። መልካም ንባብ

ውጤት እየሰራን ስለሆነ ከዚህ በኋላ እናሳውቅችኋለን

አሁን ደግሞ ከዚህ ቀደም እንደምናደርደው ለክረምት ንባባችን የሚሆን ቆንጆ መጽሐፍ የምንሰጥበት ሰዓት ነው የሚሆነው።

መልስ 1. ሐ ማቴ 17 2. ሀ ዘጸ 18፥3-4 3. ሐ 4. ለ መሳ 3 5. መ ሐዋ 11፥26 6. ለ ራዕ 3 7. ለ ዘጸ 31፥1-5 8. ሐ 9. መ ዘሌ 16፥8 #እግዚአብሔርን_መፈለግ #በመመለስ #በፅድቅ_ኑሮ #በመታመን Follow AASTU ECSF On : Telegram | YouTube | Instagram | TikTok | CounselingBot | I4UBot

photo content

ጥያቄ 1.በደብረ ታቦር(በመለወጥ) ተራራ ላይ ከኢየሱስ ጋር አብረው የታዩ የብሉይ ኪዳን ሰዎች እነማን ናቸው? ሀ.ኤርሚያስ እና ሙሴ ለ.ኤልያስ እና ኤልሳዕ ሐ.ኤልያስ እና ሙሴ መ.ኤልያስ እና ኤርሚያስ 2. ሙሴ በምድያም ምድር ሳለ ከሚስቱ ከሲፓራ የወለዳቸው ሁለት ልጆች፡ ሀ.ጌርሳም እና ኤልዔዘር ለ.መህሎን እና ኬሎን ሐ.አፍኒን እና ፍንሐስ መ. ናዳብ እና አብዩድ 3.ስለ በለዓምና ስለተናገረችው አህያ ዝርዝር ታሪክ የሚያትተው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል፡ ሀ.ዘጸዓት ለ.ዘለዋዊያን ሐ.ዘኁልቁ መ.ዘዳግም 4. በግራ እጁ የሚዋጋ፤ ንጉሥ ኤግሎምን የገደለው መስፍን፡ ሀ.ጌዴዎን ለ.ናዖድ ሐ.ሶምሶን መ.ሰሜጋር 5.አማኞች ለመጀመሪያ ጊዜ "ክርስቲያን" ተብለው የተጠሩበት ከተማ፡ ሀ.ሮሜ ለ.ኤፌ ሐ.ተሰሎንቄ መ.አንጾኪያ 6. በዮሐንስ ራእይ መጽሐፍ "ለብ ያልህ" (ትኩስ ወይም ቀዝቃዛ) ያልሆንክ የተባለችው ቤ/ክ፡ ሀ.ፊላደልፍያ ለ. ሎዶቂያ ሐ.ኤፌሶን መ.ሰርመኔስ 7. እስራኤላውያን በምድረበዳ ድንኳኑን በሠሩ ጊዜ ጥበባዊ ስራዎችን ለመስራት በእግዚአብሔር መንፈስ የተሞላው ዋናው የእጅ ጥበብ ባለሙያ ፡ ሀ.ሐር ለ.ባስልኤል ሐ.ኤልያብ መ.ናባል 8.ከሚከተሉት የብሉይ ኪዳን ነብያት አንዱ ለሕዝቡ በመስበክ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ጋር በመከራከር ይታወቃል ፡ ሀ.ሐጌ ለ.ሚልክያስ ሐ.ዕምባቆም መ.ሶፎኒያስ 9.በስርየት ቀን (yom kappur) ሕግ መሠረት ሁለት ፍየሎች ይቀርባሉ። አንደኛው ለእግዚአብሔር ይሰዋል፤ሁለተኛው ግን የእስራኤል ኃጢያት ተናዞበት ወደምድረበዳ ይለቀቃል። የሁለተኛው ፍየል መጠሪያ ስም፡ ሀ.ኡሪም ለ.ቁርባን ሐ.ኤፉድ መ.አዛዜል 10. ከዛሬው ቃለ እግዚያብሔር የተማራችሁትን በአጭሩ ግለጹ? #እግዚአብሔርን_መፈለግ #በመመለስ #በፅድቅ_ኑሮ #በመታመን Follow AASTU ECSF On : Telegram | YouTube | Instagram | TikTok | CounselingBot | I4UBot

1️⃣

2️⃣

3️⃣

ለመጀመር

በመቀጠል ሁላችንም በጉጉት ወደምንጠብቀው እና ወደሚያሸልመው የጥያቄ እና መልስ ውድድር ነው የምንሄደው 🤩 ነገር ግን የተወሰኑ የጨዋታ ህግጋት ይኖሩናል 1) መቼም ቢሆን የምትልኩትን መልስ Edit ማድረግ በፍጹም አይቻልም።🙅🏻 2)መልሳችሁን የምትልኩት @aastuecsfcontact ላይ ብቻ ሲሆን ከዚያ ውጪ Group ላይም ሆነ በሌላ ስፍራ መላክ ከጨዋታው ውጪ ያደርጋል። 3)Time Up ከተባለ በኋላ መልስ መላክ ዋጋ የለውም። 4) ጥያቄዎቹ ትንሽ ጠጠር ስለሚሉ በፍጥነት ተመልሰው ሊሆን ይችላል በሚል ምክኒያት ተስፋ መቁረጥ አይቻልም።😁 5) ያላችሁ 20 ደቂቃ ብቻ መሆኑን እንድትረዱት እናሳስባለን። መልካም እድል ተመኘንላችሁ 🙌🏻 Telegram | YouTube | Instagram | TikTok | CounselingBot | I4UBot

photo content

እሺ ቤተሰቦቻችን Cardኡ ተሞልቷል 😁 ነገር ግን በመሃል ሌላም ሊኖር ስለሚችል በትጋት እስከመጨረሻው ድረስ ተከታተሉ 🥰