ch
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

前往频道在 Telegram
1 740
订阅者
-124 小时
无数据7
-630
帖子存档
የ2018 የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና የመግቢያ ነጥብ መሰረት በአስተዳደሩ ባሉ ሰባት የግልና የመንግስት ኮሌጆች ሰልጣኞችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሞያ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በሰጡት መግለጫ የ2018 የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና የመግቢያ ነጥብ ይፋ መሆኑን ተከትሎ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለጹ ። ሀላፊዋ እንደገለጹት በ5 የግል ኮሌጆች እና በሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ከ4 ሺ በላይ አዳዲስ ተማሪዎችን ለማሰልጠን ዝግጅት ተጠናቋል ብለዋል:: ምዝገባውም ከጥቅምት 12 ጀምሮ ይካሄዳል። በመንግስት ኮሌጆች የሚገቡት በሁለቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የሳይኮ ሜትሪክ ምዘና እና የባዮ ሜትሪክ ምዝገባ በማድረግ ሲሆን በተመሳሳይ ወደ ግል ኮሌጆች ለመግባት ደግሞ በወረዳ አንድ ማዕከላት የባዮ ሜትሪክ ምዝገባ በማድረግ የሌበር መታወቂያ በመያዝ መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቅሰዋል ። በ2017 ዓ.ም አስራ ሁለተኛ ክፍል ያጠናቀቁና ከዚህ በፊት 12ተኛ ክፍል አጠናቀው ወደ ኮሌጅ ያልገቡ ተማሪዎች በቴክኒክና ሞያ የመግቢያ ነጥብ መስፈርት መሰረት መግባት እንደሚችሉም በመግለጫው ተጠቅሷል። የትምህርትና ስልጠናው በመንግሥት ኮሌጆች ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 እንዲሁም በደረጃ 6 ዲግሪ ፕሮግራም የሚሰጥ ሲሆን በግል ኮሌጆች ደግሞ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 4 ድረስ ይሰጣል። ኃላፊዋ አክለው እንደገለጹትም አስተዳደሩ ከአጎራባች ክልሎች ሰልጣኝ ተማሪዎችን እንደሚቀብሉም ጠቁመዋል። ©️ DireTvአማርኛ | ጥቅምት 11፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ትግበራ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ:: በቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ስራ ሂደት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ክፍል ስር ለሚሰሩ ነባር እና በአዲስ ለተመቡ አሰልጣኝ መ/ራን በትግበራው አፈፃፀምና በቀጣይ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የግብዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊና ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በ2017 በጀት ዓመት በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ትግበራው በብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ አመርቂ ስራ ለሰሩት ነባር ባለሙያዎች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን አክለውም በ2018 በጀት ዓመት ለሚኖረው የኢ/ኤ/አ ትግበራ በቅንጅት በጥራት ለማከናውን እንዲረዳን ይህን የግንዛቤ መድረክ ማዘጋጀት ማስፈለጉንም ገልፀዋል:: የግንዛቤ ስልጠናውን የኢዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ኬዝቲም ሀላፊ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም የ4ቱ የትግበራ ማእቀፎች አተገባበርን በተመለከት ሰፋ ያለ ግንዛቤ መስጠት የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም በ2018 በጀት ዓመት የኢ/ኤ/አ እቅድን በተመለከተ ከፈፃሚዎች ጋር መወያየት ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 06/2/2018 ዓ.ም

በድሬዳዋ የአድራ ኢትዮጵያ (ADRA Ethiopia)ፕሮጀክት የግሪን ኢነርጂ እስትሪም ኮሚቴ ስራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለፀ:: የአረንጓዴ ኢነርጂ አስተባባሪ ኮሚቴ ልኡክ በድሬዳዋ አስተዳደር በአድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት የተሰሩ ስራዎች ላይ የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሂዷል። ልኡኩ በድሬዳዋ በአድራ ኢትዮጵያ (ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ላይ የልምድ ልውውጥ መድረክ ያካሄደ ሲሆን በSolar PV Instalation & Maintenance የተመረቁ ሰልጣኞች የስራ ምችችት ላይ እንዲሁም በአጠቃላይ በፕሮጀክቱ የተሰሩ ስራዎች ላይ ውይይት አድርጓል። በዚህም በመድረኩ የተገኙት ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ የአድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ድሬዳዋ መተግበር ከጀመረ 3 አመታት ማስቆጠሩን ገልፀው፤ በፕሮጀክቱ በተሰሩት ስራዎች በርካታ ወጣቶችን የስራ ባለቤት ማድረግ እየተቻለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። አቶ ታደለ አያይዘውም በሶላር ፒቪ እና ኢኒስታሌሽን ዘርፍ የተመረቁ ወጣቶችን ወደ ስራ የማስገባቱ ተግባር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የADRA ፕሮጀክት ፕሮግራም ኮርዲኔተር አቶ ብስራት አበራ በበኩላቸው በድሬዳዋ በአድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት የግሪን ኢነርጂ እስትሪም ኮሚቴ ስራዎች አበረታች መሆናቸው ገልፀዋል። አቶ ብስራት አያይዘውም በተለይም በፕሮጀክቱ በድሬዳዋ በሚገኙ የገጠር አካባቢዎች የተሰሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው ጠቁመዋል። የአድራ ኢትዮጰያ ፕሮጀክት የድሬዳዋ ፊልድ ኦፊስ ፕሮጀክት ማናጀር የሆኑት አቶ ሀብታሙ በየነ በአስተዳደሩ በሶላር ኢነርጂ ዘርፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ገልፀው ይህም በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። DGC ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም

"ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፤ ለብሔራዊ አንድነታችን፤ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ" የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት 18ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ አላማ ቀን በዓል በኮሌጁ በደማቅ ሁኔታ ተከብራል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና /"የቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ለወጣቶች አዳዲስ እና በገበያው ላይ ተፈላጊ የሆኑ የሙያ ዘርፎችን በማሰልጠን ወጣቶችን የሙያ ባለቤት እያረጉ ይገኛሉ"- የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር #DGC ጥቅምት 1/2018 የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠኑአቸውን 1042 ሰልጣኞችን በድምቀት እያስመረቁ ይገኛል። በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ለተመራቂ ሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ በሙያዊ ክህሎትና ሥነ-ምግባር የታነፀ፣ ለሥራ ፍቅርና ተነሳሽነት ያለው እንዲሁም ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሠራሮች ጋር ተዋህዶ መሥራት የሚችል የሰው ኃይል በብዛት እና በጥራት በማሰልጠን ረገድ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ጉል ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል። በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ የቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ለወጣቶች አዳዲስ እና በገበያው ላይ ተፈላጊ የሆኑ የሙያ ዘርፎችን በማሰልጠን ወጣቶችን የሙያ ባለቤት እያረጉ እንደሚገኙም ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገልፀዋል። ከንቲባ ከድር አያይዘውም ለቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ትኩረት ሰጥተው የሰሩ ሀገሮች ዛሬ ላይ የደረሱብት የኢኮኖሚያዊ እመርታ እና የቴክኖሎጂ የበላይነትን ላይ እንዲደርሱ እንዳስቻላቸው ጠቁመው፤ በሀገራችንም ዋነኛ ተግዳሮት የሆነውን ስራ አጥነትን ለማስወገድና ለሀገራችን ዘላቂ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የድሬዳዋ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች በቴክኖሎጂ ታግዘው እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል። በመጨረሻም ከንቲባ ከድር ተመራቂ ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት ያሳዩትን የሙያ ፍቅር እና ዲሲፒሊን በስራው ዓለምም በማስቀጠል በተለይም በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና እና በሌሎችም በተፈጠሩት የኢንደስትሪ ማዕከላት በመሰማራት ድሬዳዋን ብሎም ሀገርን የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ©️ DGC

#ዜና |የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና በገበያ ተፈላጊ በሆነ ሞያና ክህሎት የበቁ ዜጎችን በማፍራት ብዙዎች ተጠቃሚ እነሆኑ ነው ። #DireTvአማርኛ | መስከረም 27፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ የሞያና ክህሎት ስልጠና ያለውን ጠቀሜታ በመገንዘብ በኩልም የህብረተሰቡ ንቃት መዳበሩ ይነገራል። በዚህ ዙሪያ የድሬዳዋ መገናኛ ብዙኃን ድርጅት ከቴክኒክና ሞያ ሰልጥነው ስራ ላይ ከተሰማሩ ነዋሪዎች ጋር ቆይታ አድርጓል። ነጃት ተገኔ እንደሚከተለው አዘጋጅታዋለች

ለፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የተዘጋጀ በተግባር የተደገፈ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ፡፡ ይህ የአቅም ግንባታ መድረክ የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ሙያዊ ብቃታቸውን ከማሳደግ ባሻገር በየሙያ መስኩ በየኢንዱስትሪው ተግባራዊ ዕውቀትና ክህሎት የሚያገኙበት ሆኖ መሰናዳቱና የተሻለ ልምድና ተሞክሮዎችን ከአቻዎቻቸው የሚቀስሙበትን ዕድል የሚፈጥር መድረክ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው ሰልጣኞች ስልጠናውን በንቃት እንዲሳተፉ እና ስልጠናውን አጠናቀው ሲጨርሱ በማሰልጠን የስልጠና ጥራትን ለማሻሻልና የሥራ ገበያውን ፍላጎት ለመመለስ በሚደረገው ሁሉን አቀፍ ርብርብ ውስጥ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ለማበርከት ከወዲሁ እንዲዘጋጁ አሳስበዋል፡፡ በዚህ የአቅም ግንባታ ስልጠና የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ተሳታፊ ሲሆኑ ገበያው የሚፈልገውን ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ ለማፍራት የአሰልጣኞችን ብቃት ተከታታይነት ባለው መልኩ ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይም ትኩረት እንደሚሰጠውም በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች በዛሬው  እለት “ከጂኦስትራቴጂ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና እና ወደ ተሻለ ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የመንግስት ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ ዓመታት የትኩረት መስኮች ላይ የሚመክር የውይይት መድረክ  አካሄደዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት ሰራተኞች በሀገራዊ ቀጣይ የእድገት ጉዞ ላይ የጠራ ግንዛቤን እንዲጨብጡና ለሀገራዊ ለውጡ በሁሉም መስክ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አቅም የሚፈጥርላቸው ይሆናል። መድረኩም የድሬዳዋን እድገትና ተምሳሌትነት እንዲሁም የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በቀጣይም የመንግስትን አሻጋሪ ዕሳቤዎች በቁርጠኝነት ለመፈፀምና ለማስፈፀም ተግባቦት የፈጠረ መሆኑን ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ