1 740
订阅者
+124 小时
+37 天
-530 天
帖子存档
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
🛑 ድንበርና ወሰን የማይገድበው ሰው መሆን ይቻላል! ✨
🤔 እንዴት? የዓለም ቋንቋ የሆነውን ክህሎት ባለቤት ሲሆኑ፤
📚 ወቅቱ የሚፈልገውን እውቀትና ክህሎት ሲታጠቁ ድንበርም ወሰንም እርስዎን አያገድብም፡፡ ይልቁንም ዓለም እርስዎን ይፈልጋል!
የክህሎት ባለቤት በመሆን፦
✅ አለም አቀፋዊ ተፈላጊነት ይፍጠሩ!
✅ ድንበር የለሽ የስራ እድሎችን ያግኙ!
🏫 አቅራቢያዎ በሚገኝ የቴክኒክና ሙያ ተቋም ዛሬውኑ የክህሎት ስልጠና ይጀምሩ!
🚀 ክህሎት - የዓለም ቋንቋ! 🌐
መስከረም 21/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ በሚል መርሃግብር የክረምት የሙያ ክህሎት ስልጠናን ሲከታተሉ የነበሩ ከ250 በላይ ወጣቶች ተመረቁ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ዜጎች ቢያንሰ የአንድ ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ ለማድረግ "አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ" በሚል መሪ ቃል በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የክረምት ስልጠናን ሲከታተሉ የነበሩ 270 ወጣቶችን አስመርቋል።
በኹነቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ያለፉትን 3 ወራት በ14 ዘርፎች የተሰጠውን ክህሎት መር ስልጠና የእረፍት ጊዜያቸውን በመሰዋት ወስደው የተመረቁት ወጣቶች ህብረተሰቡ ለዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት በመቀየር በኩል የተጣለባቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
የአንድን ሀገር እድገትን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ቢያነስ የአንድ ሙያ ባለቤት የሆነ የሰለጠነ ዜጋ ማፍራት አስፈለጊ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው በክረምት አጫጭር ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች ስራን በራሳቸው በመፍጠር በኩል አይነተኛ ክህሎት መቅሰማቸውን ገልፀዋል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው ተቋሙ ባለፉት ሁለት አመታት በዘርፉ በረካታ ወጣቶችን የሙያ እና የክህሎት ባለቤት ማድረጉን ጠቅሰው ስልጠናው ወጣቶች ያላቸውን ዝንባሌ በጊዜ አውቀው ክህሎታቸውን እንዲያሳደጉ ያገዘ እንደሆነ አሰታውቀዋል።
ሰልጣኞች በበኩላቸው የወሰዱት የክህሎት ስልጠና የወደፊት ህይወታቸውን የተቃና በማድረግ በተለይም የራሳቸውን ሞያ ተጠቅመው ሥራ እንዲፈጥሩ አይነተኛ ድጋፍ እንደሚደርግላቸው ገልፀዋል።
©️ DGC
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
🔑 ቴክኒክና ሙያ: የስኬት ቁልፍ
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና የመጨረሻው ግብ በክብር የሚያስቀምጡት የምስክር ወረቀት አይደለም። ይልቁንም ነገዎን ከዕድልና እጣ ፈንታ እንዲሁም ከጥገኝነት ነፃ አውጥተው በራስዎ መሻት እንዲቀርጹ የሚያስችልዎትን አቅም በእጅዎ ማድረጉ ነው።
ሙያ የሚያጎናፅፍዎ ሦስቱ ነፃነቶች፦
💸 የገንዘብ ነጻነት: ሰርቶ ለማትረፍ፣ አትርፎ ለመቆጠብ እና ቆጥቦ ኢንቨስት በማድረግ ለቤተሰብ/ለህብረተሰብ/ለሀገር የተሻለ ነገር ለመፍጠር የሚያስችል ⚡ ኃይል፣
🛠️ የሙያ ነጻነት: በራስ መንገድ መሄድ፣ የሚወዱትን የሙያ መስክ የመምረጥ እና የራስዎ አለቃ የመሆን በራስ የመተማመን አቅም፣
🚀 የሕይወት ነጻነት: በዕድልና እጣ ፈንታ አለፍ ሲልም በሰዎች በጎ ፍቃድ ሳይሆን በራስዎ ፍላጎት የሚመራ ሕይወት የመኖር ብቃት
👉 ታዲያ ምን ይጠብቃሉ! አሁኑኑ አቅራቢያ ወደሚገኝ የቴክኒክና ሙያ በመሄድ እውነተኛ ነፃነትዎን የሚያጎናፅፍዎትን ቁልፍ መቅረፅ ይጀምሩ።
መስከረም 17/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
✨ እንደ እንቁ የሚፈለጉ የሙያተኛ እጆች ✨
🔍 ዙሪያችንን በትኩረት እናስተውል
🏛 በግርማ ሞገሳቸው የሚያስደምሙን ህንፃዎች
🛋 አስደማሚ የቤት ቁሳቁሶች
⚙️ ህይወታችንን የሚያቀሉ ማምረቻ ማሽኖች
👗👞 በውበታቸው የሚያማልሉ አልባሳትና መጫሚያዎች
💍 የመዋቢያ ጌጣጌጦች………..
✋🎨 እነዚህ በጥበበኛ እጅ የሚሠሩ፣ የሚቀረፁ፣ የሚዋቡና የሚዘጋጁ ቁሶች ሁሉ የሙያተኛ እጆች በእጅጉ ይፈልጋሉ
💡 የዕለት ፍላጎታቸውን ለመሙላት፣ ሕይወታቸውን የተሻለ ለማድረግ፣ ጥበብና ውበት የሚለግሰውን ደስታ ለማጣጣም የሚሹ መላ የሰው ዘሮች ፍላጎት ምላሽ የሚያገኘው በጥበበኛ✋ባለእጆች ነው።
• 📚 ሙያ ይሰልጥኑ፣
• 🎭 ጥበብን ይቅሰሙ፣
•🚀 ድንበርና ወሰን ሳያግድዎት እንደ እንቁ ተፈላጊ ይሁኑ!
መስከረም 14/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
"የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድሉ ለኛ ብቻ ሳይሆን ለተቀሩት የአፍሪካ ወንድሞቻችን የኢኮኖሚ ነጻነት ማረጋገጥ እንደሚቻል ብርሀን ያሳየ ነው"። ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ የኮሌጃችን አመራሮችና ስራተኞች የተሳተፉበትና በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል እስታድየም የተካሄደው ታላቅ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በፎቶ📸
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
"የሚደገም ድል፣ የሚጨበጥ ብስራት፣ ህዳሴ ግድብ!"
"ግድባችን ተጠናቅቋል፣ የጠላቶቻችን ሴራ በኢትዮጵያዊ አርበኝነት እሳት ተቃጥሎ ከስሟል!"
ዛሬ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አጠቃላይ ሰራተኞች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ የድጋፍና ደስታቸውን የገለጡበትን ሰልፍ አካሄዱ።
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
🎉 #የሙያ_ባለቤት_ሆነው_ነገገዎን_ብሩህ_ለማድረግ_አቅደዋል? ✨
በአዲሱ የስልጠና ዘመን በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ነባርና አዳዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል። 🚀
ይህም ለወጣቶች፣ ለሙያ ስልጠና ፈላጊዎች እና ወቅቱ በሚፈልጋቸው ሙያዎች ተክነው ነጋቸውን ብሩህ ለማድረግ ላቀዱ ባለራዕዮች ወርቃማ ዕድል ነው።🌟
🌟 #የሙያ_ስልጠና_ለምን?
📚 ለሥራው ዓለም የሚያዘጋጁዎትን የንድፈ ሀሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ ስልጠና ሙሉና ተፈላጊ ሆነው መውጣት ስለሚያስችልዎ፣
📚 የሥራ ገበያውና ወቅቱ ከሚፈልገው ሙያ ጋር የተጣጣመ እና በከፍተኛ ደረጃ ተፈላጊ የሚያደርግዎትን ስልጠና ስለሚያገኙ፣
📚 ተቀጣሪ ሳሆን ቀጣሪ የመሆን ዕድል ስለሚያጎናጽፍዎ፤
📌 #ማን_ሊሰልጥን_ይችላል?
🎓 ሙያ ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንም ሆነ ሀገራቸውን መቀየሪያ ዋነኛው መሳሪያ እንደሆነ የገባቸው እና ሙያን ምርጫቸው ያደረጉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት አጠናቃቂዎች፣
🎓 ሙያ ሰልጥነው የራሳቸውን ሥራ ለመጀመር የወሰኑ ሥራ ፈጣሪዎችና የመጪው ዘመን ባለሀብቶች እንዲሁም
🎓 ተጨማሪ ሙያና ክህሎት አግኝተው ሥራቸውን ለማሳደግ፣ ገቢያቸውን ለማስፋት እና መጪውን ዘመን እየዋጁ ራሳቸውን መቀየር ያቀዱ ዜጎች በተለያዩ መርሃ ግብሮች መሰልጠን ይችላሉ፡፡
👉 #ዕድሉ_እንዳያመልጥዎ!
🌠በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ጎራ ይበሉ!በአዲሱ የስለጠና ዘመን መጪውን ዘመን በሙያ ለመዋጀት ቀድመው ይመዝገቡ!
መስከረም 11/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የአፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 በጀት አመት መሪ እቅድ ለተቋሙ ሰራተኞች ቀርቦ ውይይት ተካሄደ::
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት በቅድሚያ ለ2018 ዓ.ም የስራ ዘመን እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን ይህ የተዘጋጀው የሪፖርትና እቅድ መድረክ ኮሌጁ ባሳለፍነው በጀት አመት የነበረውን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ለሰራተኛው ቀርቦ እንዲገመገም ለማድረግ ሲሆን በተጨማሪም የ2018 በጀት አመት የተቋሙን መሪ እቅድ ለአጠቃላይ ሰራተኛው ለማስተዋወቅና ሁሉም ፈፃሚ ከተቋሙ መሪ እቅድ አኳያ ተግባርና ሀላፊበቱን እዲከውን ለማስቻል እንደሆነም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በቀጣይ የዝግጁነት ምዕራፍ ቀናት የተቋሙ መሪ እቅድ ወደታች እስከ ፈፃሚዎች ድረስ ካስኬድ የሚደረግ መሆኑን ገልፀው መሪ እቅዱ አንዴ ተዘጋጅቶ የሚቀመጥ ሳይሆን እንደ አስፈላጊቱ ማሻሻዎች የሚደረጉበት አግባቡ እንደሚኖርም ጠቅሰዋል::
የተቋሙ የአፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የ2018 በጀት አመት መሪ እቅዱን ለሰራተኛው ያቀረቡት የኮሌጁ የእቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ስራ ክፍል ሀላፊ አቶ አለማየሁ ብርሃኑ ሲሆኑ ባሳለፍነው በጀት አመት በኮሌጁ በእቅድ ተይዘው የተከናወኑ ቁልፍ ቁልፍ ተግባራትን ለመድረኩ ተሳታፊዎች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም በ2018 በጀት አመት ኮሌጁ አዲሱን የዘርፉ እሳቤን ጨምሮ ነባራዊ ሁኔታዎችን መነሻ በማድረግ ያዘጋጀውን መሪ እቅድ ለተቋሙ ሰራተኞች አስተዋውቀዋል::
በመድረኩ በቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርትና መሪ እቅድ ላይ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በቀጣይ እንደ ተቋም ለሚኖረው እንቅስቃሴ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች የተኘበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
መስከረም 9/2018 ዓ.ም
"የህዳሴ ግድባችን! የመቻል ማሳያ፣ የብልፅግናችን አሻራ፣ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ምልክት"
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃን አስመልክቶ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ "እምርታና ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የኮሌጁ አመራርና ሰራተኞች የተሳተፉበት የፖናል ውይይት ተካሄደ::
የፖናል ውይይቱን የመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት የዘመናት የኛ የኢትዮጵያውያን ቁጭት የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ባሳለፍነው ጷጉሜ 4/2017 ዓ.ም መመረቁን አስታውሰው ግድቡ ከሀይል ማመንጫነት በዘለለ ዘርፈ ብዙ ትርጉም ያለውና የኢትዮጵያ የማንሰራራት ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ የመቻላችን ማሳያ ነውም ያሉ ሲሆን ለዚህም እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን ብለዋል::
በመድረኩ ለፖናል ውይይቱ የተዘጋጀው ሰነድ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሰነድም ታላቁ የህዳሴ ግድብ እንደ ሀገር የፈጠረውን ከፍተኛ አቅም እንዲሁም በቀጣይ ግድቡ የሚያጎናፅፈን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታን አስመልክቶ በዝርዝር ለሰራተኛው ግንዛቤ በመስጠትም ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
መስከረም 9/2018 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
