ch
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

前往频道在 Telegram
1 741
订阅者
+224 小时
+37
-730
帖子存档
ከሶማሌ ክልል (ጂግጂጋ) ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተውጣጣ ልኡካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ አደረገ:: በዛሬው እለት በትቋማችን የስራ ጉብኝት በማድረግ ልምድ የተለዋወጠው ልኡክ ከሶማሌ ክልል (ጂግጂጋ) ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ የስራ ክፍል እና ዲፖርትመንት ኃላፊዎችን ያካተተ ሲሆን ለልኡካን ቡድኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ያደረጉት የኮሌጃችን ዲኖች በመቀጠልም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከምስረታው ጀምሮ አሁን እስከደረሰበት በኮሌጁ ዲን ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: በመቀጠል ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ወርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን ይህን ካዩ በኀላም ሁሉም በሚመለከታቸው ዲፓርትመንቶች እና የስራ ሂደቶች በመከፋፈል በኮሌጁ ያለውን አሰራርና ልምድ ተመልክትዋል:: በመጨረሻም ልኡካኑ ባዩት ነገር መደሰታቸውና ተቋሙ ካሰቡት በላይ ትልቅ ተቋም መሆኑን በመጠቆም ለመጡበት አላማም በርከት ያሉ ግብአቶችን እንዳገኙ በመግለፅና ለተቋሙ ምስጋናቸውን በማቅረብ በኮሌጁ የነበራቸውን ፕሮግራም አጠናቀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መስከረም 08/1/2016 ዓ.ም

Repost from N/a
photo content
+5

Repost from N/a
photo content
+8

Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ አነስተኛ ገቢ ኖሯቸው ልጆቻቸውን ለሚያስተምሩ ሰራተኞቹ ለልጆቻቸው ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ:: በድጋፍ ፕሮግራሙ ላይ የኮሌጁ አመራሮችና የማኔጅመንት አባላት ተገኝተው የትምህርት መርጃ ድጋፉን ያስረከቡ ሲሆን በርክክቡ ወቅት የኮሌጁ ዲን ባደረጉት ንግግርም "ከዚህ ቀደም እንዲህ ያሉ ድጋፎች ከተቋሙ ውጪ ብቻ ያተኮረ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ግን ያለው ሁኔታ በተቋሙ ውስጥ ያሉትንም መለስ ብለን እንድናይ ያስገደደ ነውም ብለዋል:: ሀላፊው በተጨማሪም ተቋሙ ሰራተኞችን በዘላቂነት ራሳቸውን ሚደጉሙበትን አሰራር ለመዘርጋት በሂደት ላይ መሆኑን ገልፀው ሰራተኛውም ለዚህ ትግበራ መሳካት የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል:: የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድግፍ የተደረገላች የተቋሙ ሰራተኞች በበኩላቸው የኮሌጁ አመራሮችና ማኔጅመንቱ በዚህ አዲስ የትምህርት ዘመን በሚጀምርበት ወቅት ይህን አስባችሁ ድጋፍ ማድረጋችሁ ለኛ ትልቅ ትርጉም አለው በማለት ምስጋናም እቅርበዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መስከረም 05/1/2016 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪም ለምትገኙ ኢትዮጲያውያንና ትውልደ ኢትዮጲያውያን በሙሉ እንኳን ለ2016 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በአል በሰላም አደረሳችሁ ይላል። #መልካም_አዲስ_አመት

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የADRA,Ethiopia VQEP/Green Energy TVET Project Phase II በድሬደዋ ከተማ እና በአጎራባች የገጠር ቀበሌዎች ያለውን የሶላር መስመር ዝርጋታ እና የሶላር እቃዋች ጥገና ያለበትን ሁኔታ እና ፍላጎት ለማወቅ የሚያስችል የገበያ ዳሰሳ ጥናት (labour market study) በማካሄድ ለስትሪንግ ኮሚቴ አቅርቧል።     በመድረኩ የቀረበው ጥናት ዋና አላማ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከDRA(Adventist Development Relief Ajency)Ethiopia ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ እየተሰጠ ላለው የሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና (PSolar PV Insta ation and Maintenance) የስልጠና ዘርፍ አዋጭነት እና አስፈላጊነት ለማሳየት እና የሶላር ዘርፉ ያለበትን ዋና ዋና ተግዳሮቶች ነቅሶ በማውጣት የሶላር ፒቪ ሲስተም ዘርፍ ትኩረት እንዲያገኝ ለማስቻል እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ለመጠቆም የተዘጋጀ መሆኑም ተገልጿል።    በተጨማሪም ጥናቱ በቀጣይ ለሚሰጠው የsolar pv installation & maintenance ስልጠና አዋጭነት ትልቅ ግብአት የሚሆንና በገበያ ላይ ያለውን የስራ እድሎች የሚያሳይ በመሆኑ ለፕሮጀክቱም መሳካት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተመላክቷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ነሃሴ 29/12/2015 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት እስትሪም ኮሚቴ አባላት በGreen TVET policy and strategy የሚመክር መድረክ አካሄዱ። በመድረኩ በአድራ ኢትዮጵያ እየተሰራ ላለው green energy (solar) ፕሮጀክት ስኬት የሚሆኑ የተለያዩ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በቀጣይም የግሪን ቲቬትን አፕሮች በኮሌጁ ውስጥ ለመተግበር እና ከባለድርሻ አካላት የጋራ ስራ ለመስራት አዲሱን የቲቬት ስትራቴጂ ለባለድርሻ አካላት የማሳወቅ ስራ ተሰርቷል።

በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ሚኒስቴር ዴኤታ በክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የተመራ ልኡክ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ጉብኝት አካሄደ።     በሚኒስቴር ዴኤታው የተመራው ልኡክ በኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጁ አመራሮች አቀባበል የተረገለት ሲሆን በዕለቱ በነበራቸው ጉብኝትም በተቋሙ ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥባቸውን ዲፓርትመንቶችና ዎርክ ሾፖች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።    ልኡኩ በተጨማሪም ኮሌጁ ትምህርትና ስልጠና አሰጣጡን በዲጂታል ለማዘመን ከ ICT ዲፓርትመንት ጋር በመተባበር ተግባራዊ እያደረገ ሚገኘውን የ E-LERNING ፕሮግራም የተመለከቱ ሲሆን ትግበራው ያለበትን ደረጃ እንዲሁም ያሉበትን ውስንነቶች በዲፓርትመንት ሀላፊው ሰፋ ያለ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።   በመጨረሻም የADRA PROJECT ከተቋሙ ጋር በመተባበር በ Solar System ላይ እየሰራ ሚገኘውን  ፕሮጀክት የጎበኙ ሲሆን በፕሮጀክቱ አስተባባሪም ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል።    ሚኒስቴር ዴኤታው ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በዕለቱ በነበራቸው ጉብኝት  በኮሌጁ የሚያስደንቁ ስራዎችን እንደተመለከቱ ገልፀው እነዚህ ተግባሮችም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ በስፋት እየሰራባቸው ከሚገኙት ተግራት ውስጥ መሆናቸውን በመግለፅ በትግበራዎቹ አፈጻጸም ላይ እንዲሁም በአቅም ግንባታ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በቀጣይ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ  አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግላቸው አፅንኦት ሰተው ገልጸዋል፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ነሃሴ 13/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

በ2015 ዓ.ም የተቋማት ውድድር 5ኛ ጨዋታውን ከዳሽን ባንክ ጋር ያደረገው ጤና ብድናችን ጨዋታውን 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ኢትዮ-ጣሊያን 2-1 ዳሽን ባንክ በቃሉ አዳነ⚽️ ሳላዲን አብደላ⚽️

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የግዢና ፈፋይናንስ ስራ ሂደት በስሩ የሚገኙ ኬዝ ቲሞችና ፈፃሚዎችን የ2015 ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የግምገማ መድረክ እያካሄደ ሲሆን መድረኩ በቀጣይ ቀናትም የሚቀጥል ይሆናል።