1 740
订阅者
无数据24 小时
+17 天
-630 天
帖子存档
የTVT ሴክተሩ ከአመለካከት ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የሆነ ችግር የሚታይበት ዘርፍ በመሆኑ ከሚድያ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ ተግለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ::
የግንዛቤ መስጫ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በንግግራቸው በአስተዳደሩ የሚገኙ የሚዲያ ተቋማት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያሉ እንቅስቃሴዎች ላይ የሚሰሯቸው ስራንዎችና ለዘርፉ የሚሰጡትን የአየር ሰዓት በማሻሻል ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንደሚገባቸው ገልፀው በተጨማሪም የሚዲያ ባለሙያዎች ስለዘርፉ በጥልቀት ለመገንዘብ እንዲረዳ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ አንድ የሙያ ክህሎት እንዲሰለጥኑ ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል::
ማህበረሰቡ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያለው አመለካከት በጣም ዝቅተኛ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በዘርፉ ተገቢውን ግንዛቤ ለመፍጠር የሚዲያ አካላት በተለያየ አጋጣሚ በሚያደርጏቸው እንቅስቃሴዎች ውስጥ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በህብረተሰቡ ውስጥ ሰርፇ ዋና ኢላማውን እንዲመታ እንዲሁም የተሻለ የስራ እድል ተፈጥሮ የወጣቱን ብሎም የማህበረሰቡን ህይወት መቀየር እንዲቻል የሚታየውን የተዛባ አመለካከትን መቀያር አስፈላጊ በመሆኑ ለዚህም የሚዲያ አካላት የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወስዱ አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ተቋሙ በቀጣይ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የሚዲያ ተቋማት ጋር በርካታና ዘላቂነት ያላቸው ስራዎችን በቅንጅት ለመስራት በእቅድ መያዙን ገልፀው ለዚህም እንዲረዳ የሚዲያ አካላት ከተቋሙ ጋር በጋራ ሊሰሩባቸው የሚችሉ ሀሳቦችንም ይዘው ቢመጡ ኮሌጁ በየትኛውም መንገድ በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል::
በእዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፓሊሲ ዙሪያ ለተሳታፊዎች ግንዛቤ የሰጡት በስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ት/ት ስልጠና የሰልጣኞች ልማት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ምንልክያለው ወርቅነህ ሲሆን በዚህም ነባሩ ፖሊሲ ላይ የነበሩ ክፍተቶችን ጨምሮ በአዲሱ ፖሊሲ የተካተቱ የለውጥ ሀሳቦችን በዝርዝር ለተሳተፊዎች አቅርበዋል::
በመድረኩ ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5አመት ትግበራ ምን ሊሰራ እንዳቀደ ለሚዲያ አካላት በዝርዝር የቀርበ ሲሆን ከመድረኩ በቀረቡ ሃሳቦች ላይ እንዲሁም በቀጣይ ስለሚኖረው የጋራ እንቅስቃሴ ዙሪያ ሰፊ ውይይትም ተካሂዷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት በተቋሙ አገልግሎት ዘርፍ ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ::
ኮሌጁ በEASE(Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት አማካኝነት ያዘጋጀው ይህን የአቅም ግንባታ ስልጠና Work Ethics & Service Delivery ላይ መሰረት ያደረገ ስልጠና ሲሆን በአስተዳደር ከሚገኘው የስራ አመራር ኢኒስቲትዩት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑም ተገልፇል::
ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፋት መልዕክት "ይህ ስልጠና ሲዘጋጅ በተቋሙ ጥናት ተደርጎበትና አስፈላጊነቱም በማኔጅመንቱ ታምኖበት የተዘጋጀ ስልጠና በመሆኑ ሰልጣኞች እዚህ በሚኖራችሁ የ5ቀን ቆይታ የሚሰጠውን ስልጠና በአግባቡና በሀላፊነት ሰልጥናችሁ ወደ ኮሌጁ ስትመለሱ በየምትሰሩበት የስራ ክፍል ላይ በተግባር የሚታይ ለውጥ ማሳየት ይጠበቅባችኃል ያሉ ሲሆን ይህም ስልጠና እንደ ማስጀመርያ መሆኑን እና ተቋሙ በቀጣይ ያቀዳቸውና በየክፍሉ በተለዩ የስልጠና ፍላጎቶች ላይ ተመርኩዞ ክፍተቶችን በስልጠናዎች የሚሞላ መሆኑንም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ተቋሙ በዚህ አመት በርካታ አሳይመንቶች እንዳሉበትና አንደኛውም የISO ጉዳይ መሆኑን አስታውሰው ISO በዋናነት ሚያተኩረው Costomer Focus ላይ ነው ያሉ ሲሆን አሁን ያለንበት የCostomer satisfaction survey ከኛ ብዙ እንደሚጠበቅ አመላካች በመሆኑና ይህንንም ለመፈፀም የስራ ስነ-ምግባር ወሳኝነት ያለው በመሆኑ ምክንያት ይህንን ስልጠና ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ አጊኝተነዋልም ብለዋል::
የአቅም ግንባታው ስልጠናው በኢንቲትዩቱ አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን ስልጠናው በሁለት ዙር ተከፍሎ ሲሰጥ ይህ የመጀመርያ ዙር ስልጠና ለቀጣዮቹ 5ቀናትም የሚቆይ ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 15/2017 ዓ.ም
የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላቸው ግንዛቤ ከሚፈለገው እኳያ ዝቅተኛ መሆኑ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕሰ መምህራንና የተማሪ ተወካዮችን የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሂዷል::
ፕሮጀክቱ በቀጣይ በሚኖረው የ5 አመት ትግበራ በኮሌጅ የሚሰጡ የሞያ ስልጠናዎች በእስተዳደሩ የሚገኙትን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችን ማእከል ያደረገ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም ለአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕሰ መምህራንና የተማሪ ተወካዮች ስለ ዘርፉ በቂ ግንዛቤ መፍጠር ተቀዳሚው ተግባር በመሆኑ ይህ መድረክ መዘጋጀቱም ተገልፇል::
በመድረኩ ለተሳታፊዎች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ላይ ስለ ቴክኒክና ሙያ በቂ ግንዛቤ ባለመፈጠሩ ምክንያት ወጣቶቹ በዘርፉ የሚኖራቸውን ተጠቃሚነት ባለመገንዘብ ህይወታቸውን በማይለውጡ የትምህርት መስኮች ላይ እድሜያቸውን እያባከኑ እንደሚገኙ ገልፀው በስተመጨረሻም የተማሩትን ዲግሪ አስቀምጠው ሌሎች ስልጠናዎችን ለመውሰድ ወደ ኮሌጁ እንደሚመጡም አስታውሰዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በአስተዳደሩ የሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከኮሌጁ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎቹ ላይ ተገቢውን የግንዛቤ የመፍጠር ስራ በመስራትና ተማሪዎቻቸው የ12 ክፍል መልቀቂ ፈተና ከመውስዳቸው አስቀድሞ ተማሪዎቹን በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እሳቤ መቅረፅ የሁላችንም ድርሻ መሆን እንደሚግባውም አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል::
በኢንዱስትሪው ዘርፍ ሰፊ የክህሎት ክፍተት እንዳለ የተጠቀሰ ሲሆን በየፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሰሩ ወጣቶችም ዝቅተኛ ክህሎቶች(Low skills) ላይ አየሰሩ ያሉ መሆናቸውም ተመላክቷል::
በመድረኩ የSTEM(Science,Technology, Engineering,Mathematics)ፅንሰ ሃሳብና ምንነት ዙሪያ በኮሌጁ ምክትል ዲን እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ በኩል ለመድረኩ ተሳታፊዎች ቀርቧል::
የመድረኩ ተሳታፊዎች
በበኩላቸው በዘርፉ በሚፈለገው ልክ ውጤት እንዳይመጣ ተግዳሮት ሆነዋል ያሏቸውን ምክንያቶች በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን በቀጣይም ከኮሌጁ ጋር በቅንጅትና በባለቤትነት ለመስራት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እንደሆኑና የሚታዩ ክፍተቶችንም በዘላቂነት መፈታት እንደሚሹ ሀሳብ አስተያየታቸውን ሰተዋል::
ኮሌጁ በቀጣይ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር የጋራ መግባብያ ሰነድ በመፈራረም ወደ ትግበራ እንደሚገባም በመድረኩ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ የOSH( Occupational Safety & Health) የሙያ ደህንነት ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ጀመረ::
ኮሌጁ እየሰጠ የሚገኘው ይህ የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ በኢንጂነሪንግ እና በጤናው ዘርፍ የመጀመርያ ዲግሪ ተመርቀው ስራ ያልያዙ ወጣቶችን ትኩረት ያደረገ ሲሆን በመስፈርቱ መሰረት ተመልምለው የመጡ ወጣቶችንም ለማሰልጠንና ወደ ኢንዱስትሪው ለማሰማራት በማሰብ በመጀመርያ ዙር 31 ሰልጣኞችን ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ ይገኛል::
ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው የLife skills ስልጠናን ጨምሮ በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን በመለየት እና በመቆጣጠር የሰውን ህይወት እንዲሁም ንብረትን ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችሉትን የተግባር፣የንድፍ ሃሳብን ጨምሮ ኢንዱስትሪዎች ላይ የትብብር ስልጠናዎችን የሚወስዱ መሆኑም ተግልፇል::
የOSH( Occupational Safety & Health) ስልጠናው በአጫጭር ስልጠና መደብ የሚሰጥ ሲሆን ለቀጣዮቹ አንድ ወራትም የሚቆይ ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም
በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የሚሰጡ የሞያ ስልጠናዎች በሀገር ውጥ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ማእከል ማድረግ እንዳለበት ተገለፀ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ጋር የምክክር መድረክ አካሔደ።
እንደ ሀገር አቀፍ ያለውን የስራ እጥ ችግርን ለመቅረፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በዚህ የቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች ደሞ ያላቸው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም።
ይሁን እንጂ የሙያ ኮሌጆች የሚሰጡት ስልጠና ክህሎትን ከስራ ቅጥር ጋር ያገናኘ ባለመሆኑ ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች የሚወጡ ሰልጣኞች በስራ እጦት ሲቸገሩ ይስተዋላል። የድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት በሚቻልባቸው የስልጠናና የትምህርት መስኮች ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የሚሰጡ የሙያ ስልጠናዎች በሀገር ውጥ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ማእከል ማድረግ እንዳለበት የገለፁትና የኢንዱስትሪዎች ፍላጎት ተለይቶ ስራ እጥነትን መቅረፍ ያስችላል፣ ለዚህም ኢንዱስትሪዎች በራሳቸው የሚሰጡትን ስልጠና በማቆም ለኮሌጆች ሀላፊነቱን መስጠት አለባቸው ሲሉ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ ተናግረዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በአስተዳደሩ ባሉ ሁለት የሙያ ኮሌጆች የሚያሰለጥኑት ኢንዱስትሪ መር ስልጠናዎች ውጤት እያመጡ በመሆኑ ኢንዱስትሪዎች ከኮሌጆች ጋር በፈቃደኝነት ተቀራርበው መስራት አለባቸው ሲሉ ገልፀዋል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE (Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት
ኮሌጁ የኢንዱስትሪዎች ፍላጎትን በማጤን ከውጪ የሚመጡ ባለሞያዎችን በመተካት የኮሌጁ ምሁራንን በማብቃት ምሁራን ብቁ የሆኑ ሰልጣኞችን በማውጣት የተሻለ አፈፃፀም ማምጣት ያስችለናል ሲሉ ገልፀውልናል።
በመድረኩ የተገኙት ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተወጣጡና ባለድርሻ አካላት ውይይት አካሒደዋል።
ይህ EASE(Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት ከአለም ባንክ በተገኘ 6.7 ሚሊየን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የ5አመት የስልጠና መርሀግብር መሆኑ ተገልፇል።
#Diretv አማርኛ ታህሳስ 3/2017
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች "ከወጣቶች ጋር በመተባበር ሙስናን መከላከል የነገ ስብዕናን ለመቅረፅ" በሚል መሪ ቃል የፀረ-ሙስና ቀንን አከበሩ::
በአለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ የተከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አስመልክቶ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ቀኑን በፓናል ውይይት እንዲሁም በግንዛቤ መስጫ ስልጠና አክብረዋል፡፡
በመድረኩ ለሰራተኛው መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በመልዕክታቸው ሙስና የጋራ ጠላታችን መሆኑን ጠቅሰው በጋራ የማንታገለው ከሆነ እንደ ኮሌጅ ብሎም እንደ ሀገር ለማስመዝገብ ለምናስበው እድገት እንቅፉት መሆኑና ወደ ኃላ የሚያስቀረን ካንሰር መሆኑን ጠቅሰው የተቋሙ ሰራተኛ በየትኛውም የስራ እንቅስቃሴው ሁሉ ሙስናን የሚጠይፍ ማህበረሰብ መሆን እንደሚገባውም አሳስበዋል::
መድረኩ ቀጥሎም በአለም አቀፍ እንዲሁም በሀገራችን ደረጃ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ የሚዳስስ ሰነድ በአቶ አድማሱ ዳምጤ አማካኝነት ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎችም ሙስና በጋራ ለመታገል ቃል በመግባት መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ህዳር 30/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
