ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 365 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 754,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 531

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 365 名订阅者。

根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 119,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.59%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.42% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 423 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 369
订阅者
+1924 小时
+677
+11930
帖子存档
የአርብ ገበያ-ሰከላ-ቲሊሊ ክፍል ሁለት የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የግንባታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። 62 ኪ.ሜ የሚረዝመው ይህው ፕሮጀክት በመስክ የስራ ቅኝት ተጎበኘቷል። በዚህም ከእቅዱ ጋር ተጣጥሞ በመልካም የስራ ክንውን ላይ እንደሚገኝ ተመላክቷል። በእሰካሁኑ የሥራ እንቅስቃሴ የቅየሳ ስራ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የውሃ መተላለፊያ/መፋሰሻ ቱቦዎች ሥራ፣ የሰብ ቤዝ ሥራዎችን ጨምሮ በርካታ የስትራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ የአራት ድልድይ ግንባታ ሥራም በፕሮጀክቱ የተካተተ ሲሆን፣ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጀምረዋል። ለአሰፋልት ንጣፍ ስራው የሚያገለግሉ አሰፈላጊ ማሽነሪዎች በሙሉ ተተክለው ከወዲሁ ግብአት ማምረት ጀምረዋል። ፕሮጀከቱ በአካባቢው ለሚገኙ ሶስት መቶ ለሚደርሱ ወጣቶች በልዩ ልዩ ሙያ የስራ እድል ተጠቀሚ እንዲሆኑም አድርጓቸዋል። የመንገዱ መገንባት አካባቢውን በሰብል ምርት በደን እና በእንስሳት ሀብቱ ይብልጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ያደረጋል ፡ የጤና ፣ የትራንስፖርትና የሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ተደራሽነትን ያስፋፋል፡፡ በአካባቢው ማህበረሰብ ኑሮና በኢኮኖሚው እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣቱም ባለፈ የነዋሪውን የአመታት የትራንስፖርት እንግልት ያስቀራል፡፡ የግንባታው ሥፍራ(ግሽ አባይ) በተለይም የታላቁ አባይ ወንዝ መነሻ ከመሆኑም ባለፈ አካባቢው የበርካታ ታሪካዊ እና ጥንታዊ መስህቦች እንዲሁም የተለያዩ ገዳማት እና አብያተ-ክርስቲያናት መገኛ እንደመሆኑ ፀጋዎቹን ይበልጥ ለማውጣት ምቹ አጋጣሚን ይፈጥራል፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የሰከላ እና ቲሊሊ ወረዳዎችን እንዲሁም አቻኖ እና ጉንዲልን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ የገጠር ቀበሌዎችን በቅርበት ያገናኛል፡፡ የመንገድ ግንባታውን በአንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሰባ ሶስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺህ በሆነ ወጪ እያከናወነ የሚገኘው ዲ ኤም ሲ ኃላፊነቱ የተወሰነ አገር በቀል የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የግንባታው የሚጠይቀው ሙሉ ወጪም በኢትየጵያ መንግስት የእየተሸፈነ ነው፡፡ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ ፒዩር ኮንሰልቲንግ እና ሳውንድ ኢንጅነሪንግ ሶልሽን በጥምርት እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የዚሁ መንገድ ፐሮጀክት አካል የሆነው የጅጋ ቋሪት ክፍል አንድ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የቅድመ-ግንባታ ሥራዎችን አጠናቅቆ በቅርቡ የግንባታ ሥራ ይጀምራል፡

የቢላሎ-ቀርሳ-አርሲነገሌ 92 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+8
የቢላሎ-ቀርሳ-አርሲነገሌ 92 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የቢላሎ-ቀርሳ-አርሲነገሌ 92 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው። በፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ ዙሪያ የመስክ የሥራ ቅኝት ተካሂዷል ። በመስክ ቅኝቱም የፕሮጀክቱን አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ በጥሩ መልኩ እየተከናወነ መሆኑ ተመላክቷል። በእስከአሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ የዲዛይን ስራዎች፣የተለዋጭ መንገድ ግንባታ ፣የመሬት ጠረጋ እና የአፈር ሙሌት፣ የፍሳሽ ማስተላለፊያ እና በርካታ የስትራክቸር ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የአስር ድልድዮች ግንባታ ሥራም የተጀመረ ሲሆን አበዛኞቹም እየተጠናቀቁ ነው ። የሰብ ቤዝ / ለአስፋልን ንጣፍ ምቹ የማድረግ የግንባታ ክፍሎች / እየተሰሩ ናቸው በዚህም በቅርቡ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ለመጀመር ቅድመ ዝግጅቶች ተጀምረዋል ፡፡ መንገዱ የተለያዩ ከተሞች እና ወረዳዎችን በማስተሳሰር ማሕበራዊ ና ኢኮኖሚያዊ ግንኑነትን ያሳልጣል፡፡ በተጨማሪም ዋናውን የሞጆ-ባቱ-ሻሸመኔ እና አዳማ-አሰላ-ዶዶላ መንገዶችን በማገናኘት ሁነኛ አማራጭን ይፈጥራል፡፡ ለግንባታው የሚውልውን አንድ ቢሊየን አምስት መቶ ስልሳ አምስት ሚሊየን አራት መቶ ሺህ ብር በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ ግንባታውን ዓለም አቀፉ ቻይና ኮሚኒኬሽን ኮንስተራክሽን ካምፓኒ (CCCC) እየሰራ ይገኛል፡፡ የግንባታውን ጥራት በማማከር እና በመቆጣጠር በኩል ሼላዲያ አሾሺዬትስ እና አንሲራድ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ደግሞ በአማካሪነት እና በንዑስ አማካሪነት በጥምረት እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡

የቡልቡላ - አላጌ 30 ኪ.ሜ የዲዛይንና ግንባታ የመንገድ ፕሮጀክት
+8
የቡልቡላ - አላጌ 30 ኪ.ሜ የዲዛይንና ግንባታ የመንገድ ፕሮጀክት

የቡልቡላ - አላጌ 30 ኪ.ሜ የዲዛይንና ግንባታ የመንገድ ፕሮጀክት በመስክ የስራ ቅኝት ተጎበኘ። በመስክ ቅኝቱም በፕሮጀክቱ የተሰሩና አሁን ላይ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ለመመልከት ተችሏል፡፡ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የነበሩ ውስን ችግሮች አፋጣኝ መፍትሄንም እንዲያገኙ ከባቱ ወረዳ የስራ ሀላፊዎች እና አመራሮች ጋር ውይይት ተካሂዷል። በዚህም በፕሮጀከቱ ግንባታ ስፍራ ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶችን ለመድፈን የጋራ መገባባት ላይ ተደርሷል። ለመንገድ ፕሮጀክቱ መፋጠን ይበልጥ በጋራ ለመሰራት የሚያስችሉ እቅዶች ዙሪያም ውይይት ተካሂዷል። የመንገድ ግንባታው አሁናዊ የስራ አፈፃፀሙ 25በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህም በእቅዱ መሰረት መከናወኑ ተገምግሟል ። ቀጣይ የግንባታ ስራዎችንም በእቅዱ መሰረት በተያዘለት ጊዜ ለማከናወን እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ ከመንገዱ የግንባታ ስራም መካከል የዲዛይን ስራዎች፣የተለዋጭ መንገድ ግንባታ ፣የመሬት ጠረጋ እና የአፈር ሙሌት፣ የፍሳሽ ማስተላለፊያ ፣የአማካሪ መሀንዲስ ካምፕ እና ሌሎች የስትራክቸር ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም የተጎዳ የጠጠር መንገድ የነበረ ሲሆን ከሚኖረው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንፃርም በአስፋልት ኮንክሪት እንዲገነባ ነው በመንግስት የተወሰነው ። ለግንባታው ማስፈፀምያም የሚውለው 686,000,000 ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ ግንባታውን ኪቢሽ ኮንስትራክሽን የተባለ ሀገር በቀል የስራ ተቋራጭ እየሰራው የሚገኝ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራው በዩናይትድ አማካሪ መሀንዲሶች (ዩኒኮን) እየተከናወነ ነው፡፡ ከባቱ -ሀዋሳ ዋና መንገድ ተገንጥሎ እየተገነባ ያለው ይህው ፕሮጀክት ከቡልቡላ ተነስቶ አላጌ ላይ የሚጠናቀቅ ሲሆን በመሀል የሚገኙ አካባቢዎችን በማስተሳሰር ረገድም ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የፕሮጀከቱ ዕውን መሆን ሁለት መቶ ለሚደረሱ የአካባቢው ወጣቶች የስራ ዕድል ተጠቃሚም እንዲሆኑ አድርጓል ።

የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የመንገድ ግንባታ ስራ
+7
የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የመንገድ ግንባታ ስራ

የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የመንገድ ግንባታ ስራ በያዝነው በጀት አመት ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው። በፕሮጀከቱ ስፍራ በተካሄደው የመስክ ምልከታ ቅኝት ከጥቂት ስፈራ ውጪ አብዛኛው የመንገዱ የግንባታ ክፍል ተጠናቆ ለትራንስፖርት ክፍት ተደርጓል። በስፍራው ያነጋገርናቸው የመንገዱ ተጠቃሚዎች ፤ አሽከርካሪዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች በተለይም የክርምቱን መውጣት ተከትሎ በተደረገው ክፍተኛ የግንባታ ትኩረት አበዛኛው የመንገዱ ክፍል ተጠናቆ ክፍት በመደረጉ መቹ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ማሳለጥ መቻሉን ተናግረዋል ። የመንገዱ አሁናዊ የግንባታ አፈፃፀሙ 90 በመቶ የደረሰ ሲሆን አስፋልት ንጣፍ ስራውም በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። የሳንሱሲ- ታጠቅ - ኬላ 13.56 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታን ያካልላል። የግንባታው መዋለ-ንዋይ 820,802,402 ሚሊዮን ብር ወጪ እየተሸፈነ ያለው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ ያለው ሀገር በቀሉ ተቋራጩ አሰር ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው። ፎርተረስ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልቲንግ ከ አሶሼትስ Plc ጋራ በጣምራ የግንባታ ስራውን በአማካሪነት እያገለገሉ ይገኛሉ ፡፡ የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የቀድሞ መንገድ ገፅታ ከ7 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋትና በአገልግሎት ብዛት ሳብያ ለከፍተኛ ጉዳት ተዳርጎ የነበረ ነው። መስመሩ ከሚያሰተናገደው የተሸከርካሪ ብዛትና መጨናነቅ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ አድገት መነሻ ስፋቱ እንዲጨመር ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ፡፡ በአማካይ ከ20 እስከ 32 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደረጓል ፡፡ መንገዱ በዚህ ደረጃ መስፋቱ በግራና ቀኝ 4 ተሸከርካሪዎችን ማስተናገድ አስችሏል ፡፡ በተጨማሪም በውስጡ የመንገድ አካፋይ ፣ የእግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ ያካተተም ነው ፡፡ የመንገዱዕእውን መሆን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ይከሰት የነበረውን መጉላላት በማስቀረት የተሳለጠ እንዲሆን አስችሏል። የቡራዩ ከተማን ከአዲስ አበባ ጋር በማስተሳሰር እንደ ሳንሱሲ፣ታጠቅና ኬላ አካባቢ ያሉ ብዛት ያላቸው ነዋሪዎችም አመቺ እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተጠቃሚ አድርጓቸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል የወጪ ገቢ ንግድ ኮሪደር የሆነውን ከአዲስ አበባ - አምቦ - ነቀምት - አሶሳ ያለው ዋና መንገድ በአሸዋ ሜዳ ታጠቅ በኩል ይጠቀሙ የነበሩትን ብዛት ያላቸው ተሸከርካሪዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን መጨናናቅ አማራጭ በመፍጠር እና የነበረውን ችግር በመቅረፍ የሳንሱሲ - ታጠቅ - ኬላ መንገድ ሁነኛ አማራጭ ሆኖም ያገለግላል ፡፡

81 ኪ.ሜ የሚረዝመው የደብረማርቆስ- ደብረኤሊያስ- ተምጫ-ጭምት መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+4
81 ኪ.ሜ የሚረዝመው የደብረማርቆስ- ደብረኤሊያስ- ተምጫ-ጭምት መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

81 ኪ.ሜ የሚረዝመው የደብረማርቆስ- ደብረኤሊያስ- ተምጫ-ጭምት መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው፡፡ በቅርቡም የአሰፋልት ማንጠፍ ስራ ተጀምሯል። የአፈር ቆረጣና ሙሌት ሥራዎች ፣ የቤዝኮርስ የድልድይ እንዲሁም የውሃ መተላለፊያ ቱቦዎች እና በርካታ የስትራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። መንገዱ ተገንብቶ እስከሚጠናቀቅ የትራንስፖርት መስተጓጎል እንዳይፈጠር ለማስቻል ተለዋጭ መንገድ ተሰርቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ ፋል ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን የሚያካሂዱት ደግሞ ሆንግ አይኬ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልታንትስ ከልደት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በመተባበር ነው። ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው አንድ ቢሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ አራት ሺህ ብር ወጪ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ መንገዱን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ለስራ ተቋራጩ የሶስት ዓመት ከአራት ወራት የጊዜ ገደብ የተሰጠው ሲሆን ፣ ግንባታው በተገቢው የጥራት ደረጃ እና ፍጥነት እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የአካባቢው ህብረተሰብ መልካም ትብብር እያደረገ ይገኛል፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በደብረማርቆስና በደብረኤልያስ ከተሞች 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 16 ሜትር እና በገጠር ደግሞ 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ የዚህ አካባቢ ህብረተሰብ ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ ተጠቃሚ ያልነበረ በመሆኑ ምክንያት የተለያዩ ችግሮችን ሲያስተናግድ ቆይቷል፡፡ በአካባቢው ከፍተኛ የጤፍ ፣ ስንዴ እና ሌሎች የግብርና ምርቶችን ጨምሮ ማርና የአትክልት ምርታማነቱ ከፍተኛ ነው። መንገዱ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን እነዚህን የግብርና ምርቶችን ያለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ገበያ ለማቅረብ እና የአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴ ወደ ተሻለ ደረጀ እንዲያድግ ለማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም ለኢንዱስትሪ ዞኖች የትራንስፖርት ፍሰት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር ባለሃብቶች በአካባቢው የተለያዩ የኢንዱስትሪ ዞኖችን እንዲገነቡ ለማስቻል ከፍተኛ ተነሳሽነትን ይፈጥራል ተብሎ ታምኖበታል ፡፡

የአቦቦ-ሜጤ አቦቦ-ኪ.ሜ 76 ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ
+1
የአቦቦ-ሜጤ አቦቦ-ኪ.ሜ 76 ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ

የጋምቤላ እና የደቡብ ክልሎችን የሚያስተሳስረው የአቦቦ-ሜጤ አቦቦ-ኪ.ሜ 76 ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ ሥራ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ነው። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ግንባታ 98 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን መንገዱ ሙሉ ለሙሉ ለትራፊክ ክፍት ሆኖ አገልግሎት እየሰጠ ነው። የግንባታው ቀሪ ውስን ስራዎች ማለትም የእግረኛ መተላለፊያ ዜብራ ፣ የመንገድ ላይ የትራፊክ ቅቦች የማቅለም ሥራ እንዲሁም ሌሎች ከመንገድ ግንባታው ጋር የተያያዙ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። 960 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ፕሮጀክቱ ወጪው ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት ነው የተሸፈነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬይል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ የተባለ አለምአቀፍ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን ፤ ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ ሲቪል ወርክስ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ እየሠራ ይገኛል ፡፡ 74.65 ኪ.ሜ የሚረዝመው መንገዱ መነሻውን የ አኝዋ ዞን መቀመጫ ከሆነችው አቦቦ ወረዳ በማድረግ አልዌሮ ግድብ ሰፈራ ፤ ቴኒ ፤ ዱቦንግ ፤ ፖታለም እንዲሁም ኩኩሪ የተሰኙ ከተሞችን ያቆራኛል፡፡ በአካባቢው የሚመረቱ በቆሎ ፤ ሩዝ እና ፍራፍሬ እንዲሁም የቅባት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በስፋት እና በአነስተኛ ወጪ ለማድረስ የመንገዱ መገንባት ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው፡፡ በአልዌሮ ወንዝ ላይ የተገነባው ሰው ሰራሹ አልዌሮ ግድብ በውስጡ የሚገኘውን ከፍተኛ የዓሣ ሀብት ክምችት በ ዘመናዊ መልክ አልምቶ ወደ የተለያዩ ገበያዎች ተደራሽ ለ ማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመንገዱ እውን መሆን አስተዋፆው የጎላ ነው፡፡ ከዚህም ባለፈ ግድቡ እሰከ 10 ሺህ ሄክታር መሬት እንዲያለማ ታልሞ የተገነባ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ሰፋፊ ሜካናይዝድ እርሻ ስራ ላይ የሚሰማሩ ኢንቨስተሮችን በመሳብ ረገድ ፋይዳው ከፍተኛ ነው፡፡ ቀደም ሲል ከ አጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 52 ኪ.ሜትሩ በ ጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና የጎን ስፋቱ ከ 5-6 ሜትር ያልበለጠ እጅግ ጠባብ ሲሆን ቀሪው ክፍል ምንም አይነት ተሸከርካሪ የሚያልፍበት አልነበረም፡፡ አሁን ላይ ግንባታው በፍፃሜ ምዕራፍ ላይ የሚገኘው መንገዱ በዞን ከተማ 21.5 ሜትር ፤ በወረዳ (ቀበሌ) 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት አለው፡፡ በመሆኑም የመንገዱ መገንባት ለዘመናት በምቹ መንገድ እጦት ምክንያት ተራርቀው የነበሩትን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በቅርበት ያገናኛል፡፡ የነዋሪውን የአመታት እንግልት ከማስቀረቱም በላይ የጉዞ ጊዜ እና ወጪን በእጅጉ ያሳጥራል፡፡ የዚሁ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው ቁቢቶ ማዞሪያ-ሜጢ 82ኪሜ የአስፋልት መንገድ ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል።

የጉደር - ጌዶ 54 ኪሎሜትር ከባድ የጥገና ግንባታ ፕሮጀክት
+2
የጉደር - ጌዶ 54 ኪሎሜትር ከባድ የጥገና ግንባታ ፕሮጀክት

የአዲስ-አምቦ-ባኮ-ነቀምት-አሶሳ የመንገድ አካል የሆነው የጉደር-ጌዶ 54 ኪሎሜትር ከባድ የጥገና ግንባታ ፕሮጀክት በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ከመንገድ ፕሮጀክቱ 92 በመቶ የሚሆነው የከባድ ጥገና ስራው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል። ቀሪ የፕሮጀክቱ ክፍል በያዝነው በጀት አመት ይጠናቀቃል። መንገዱ በአገልግሎት መደራረብ ሳቢያ በእጅጉ የተጎዳ የነበረ በመሆኑና ከሚያስገኘውም ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲሁም በየጊዜው እየጨመረ ከመጣው ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ምክንያት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጎ ጥገናው ተገባዷል። ለመንገዱ ከባድ ጥገና (431,596,708.75)ከአራት መቶ ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ብር በላይ ከመንግስት በጀት ወጪ ተደርጎበታል፡፡ ከፍተኛ ጥገናውን እያካሄደ የሚገኘው አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ዞሆንግሚ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ ሊሚትድ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ስራዎች ኮርፖሬሽን ትራንስፖርት ዲዛይንና ቁጥጥር ስራዎች ዘርፍ እየሰራው ይገኛል፡፡ በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይም አነስተኛ የአፈር ቁፋሮና ሙሌት፣ የሰብቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ንጣፍ ስራ፣ከፍተኛ የሆነ የአስፋልት ኦቨርሌይ ንጣፍ የውሃ ማስተላለፊያና የአቃፊ ግንብ ስራዎች በዋናነት ተሰርተዋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ጉደር፣ ባቢች፣ ጎሮሶል እና ጌዶ ከተሞችን በቅርበት በማገናኘት የአካባቢውን ህብረተሰብ ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡ እንዲሁም ከአሶሳ፣ነቀምት እና ባኮ የሚመጡ የእምነበረድ ምርትንና የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን እንደ ቡና፣ሰሊጥ፣ገብስ፣ጤፍና በቆሎ ማስተላለፊያ ኮሪደር ሆኖ ያገለግላል፡፡ በተጨማሪም በግንባታ ላይ ለሚገኘው የወንጪ የቱሪዝም ማዕከል መዳረሻ ለመሄድ እንደ አማራጭ መንገድ በመሆኑ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡

የኤፌሶን - መሃልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+8
የኤፌሶን - መሃልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

61ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የኤፌሶን-መሀልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በያዝነው በጀት አመት ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል ። በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የግንባታው አፈጻጸም 95 ከመቶ ላይ ደርሷል ። ቀሪ የፕሮጀክቱን ክፍል ለመፈጸም በትኩረት እየተሰራ ነው። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው የንኮማድ ሀገር በቀል የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የቁጥጥርና የማማከሩን ስራ ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነሪንግ እየሰራ ነው ፡፡ ለግንባታው ስራው የተመደበው አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ ሃምሳ ሁሉት ሚሊየን ብር /1,352,642538.82 /የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የኤፌሶን-መሃልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በስፋት የአፈር ጥንካሬን መጨመር በሚያስችል (Mechanically Stabilized Earth Wall) ቴክኖሎጂን በመጠቀም ግንባታው የተከናወነ ሲሆን ይህም የመሬት መንሸራተትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመከላከል የሚያግዝ የግንባታ ሂደት ነው፡፡ ይህ የግንባታ ቴክኖሎጂ ከዚህ በፊት በተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ለመተግበር የተሞከረ ቢሆንም በዚህ ፕሮጀክት ላይ ግን በስፋት ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡ የመንገዱ ግንባታ የኤፌሶን ከተማን ከመሀል ሜዳ ከተማ ጋር ያስተሳስራል ። በኤፍራታ ግድም ወረዳ እና በመንዝ ወረዳዎች የሚመረቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ለማውጣት፣ የጎላ ሚናን ያበረክታል ። በአካባቢው የሚገኘውን ለጎጎ ጥብቅ የማህበረሰብ ፓርክ የቱሪስት ፍሰቱን ለመጨመር እንዲሁም የመንገድ ትስስርን ለማሳደግ ይጠቅማል ፡፡ የጤና፣ ትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማህበረሰቡ ተደራሸ በማድረግ በኩልም ላቅ ያለ ጠቀሜታ ያለው ነው።

የአሳይታ - አፈምቦ - ጅቡቲ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+3
የአሳይታ - አፈምቦ - ጅቡቲ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ጋር የሚያስተሳስረው የአሳይታ-አፈምቦ-ጅቡቲ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በመልካም እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ከነባሩ የሚሌ-ጋላፊ-ጅቡቲ መንገድ በተጨማሪነት የሚገነባው የአሳይታ-አፈምቦ-ጅቡቲ ጠረፍ መንገድ በጥሩ አፈፃፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 65 ከመቶ ላይ ደርሷል፡፡ 49ኪ.ሜ የሚረዝመው ፕሮጀክቱ በእስከ አሁን ሥራ የአፈር ሙሌት እና ቆረጣ ሥራ፣ የስትራክቸር ሥራ፣ የሰብ ቤዝ ሥራዎች ተከናውኗል፡፡ የሶስት ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ የተካተተ ሲሆን የአንድ ድልድይ ግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል፡፡ ፕሮጀክቱ ሁለቱን ሀገራት በቅርበት ከማገናኘቱም በተጨማሪ የሀገራችንን የገቢ እና ወጪ ንግድ በማቀላጠፍ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ የመንገድ መሰረተ ልማቱ በክልሉ በስፋት የሚገኘውን የጨው ምርት ገቢ በማሳደግ ረገድም ጉልህ ድርሻ ያበረክታል። በአካባቢው እያደገ የመጣውን የመስኖ ግብርና ሥራ በማሳለጥ ዘርፉን በማሳደግ አስተዋፆው ከፍተኛ ነው፡፡ የትምህርት፣ የጤና እንዲሁም የተለያዩ ማሕበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን ይጨምራል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በሥፍራው የሚገኙትን ትንንሽ መንደሮች ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ እድል ይፈጥራል፡፡ ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በማሳጠር በቂ የሆነ የትራንስፖርት ምልልስ እንዲኖር በማድረግም ሚናው የጎላ ነው፡፡ መንገዱን በ 1,691,940,084.78 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ዘጠና አንድ ሚሊየን ዘጠኝ መቶ አርባ ሺህ/ ብር ወጪ እየገነባ የሚገኘው አገር-በቀሉ አሰር ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡ የግንባታው ወጪ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንገስት ነው፡፡ ይዲዲያ ኮንስትራክሽን ግንባታውን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ እየሰራ ይገኛል።

የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ
+4
የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ

የኦሮሚያ ክልልን ከሲዳማ ክልል ጋር በማገናኘት ከማዕከላዊ የሀገራችን ክፍል ጋር የሚያስተሳስረው የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ በመልካም አፈጻጸም ላይ ይገኛል ። በአሁኑ ወቅትም ከ6 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዪብ በላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራን በማገዳደብ ለአስፋልን ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ ተከናውኗል። የመሬት ድልዳሎ፣ የቱቦ ቀበራ፣ የሰብ ቤዝ ጨምሮ አስቸጋሪ የሚባሉ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ስራ በጥሩ መልኩ እየተሰሩ ይገኛል። የዚህ መንገድ ግንባታ 6 ድልድዮችን ያካተተ ሲሆን የሶስቱ ድልድዮች ስራም ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹም በግንባታ ሂድት ላይ ናቸው። 74 ኪሜ የሚረዝመው የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ አጠቃላይ አፈፃፀሙ በጥሩ ደረጃ ላይ ሲሆን በቅርቡ ወደ አሰፋልን ጥጣፍ ስራ ይሸጋገራል። በያዝነው በጀት አመት መጨረሻ ድረሰም 35ኪሎሜትሩ ሙሉ ለሙሉ በአሰፋልት ለመሸፍን በትኩረት እየተሰራ ነው። የአካባቢው ህብረተሰብ ለመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ የሚያደረገው ቀና ትብብርና ድጋፍ ለግንባታው መፋጠን የጎላ አስተዋጾ አብርክቷል። መንገዱን እየገነባ የሚገኘው ሀገር በቀሉ አለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ጎንድዋና ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነ ይገኛል። ለዚህ መንገድ ግንባታ የተመደበው 1,687,343,877.00 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሰማኒያ ሰባት ሚሊዮን ሶስት መቶ አርባ ሶስት ሺህ ብር ሲሆን የግንባታ ወጪውም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በወረዳ 12 ሜትር በገጠር ከ8-10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ አካባቢዎቹ በግብርና ምርታማነት በተለይም በስንዴ፣ገብስ እና ለሀገራችን የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ረገድ ዋነኛ የሆነው የጫካ ቡናም በስፋት ይመረትበታል ። ይህ የመንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ፍሰትን ምቹ በማድረግ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል በተጨማሪም የጤና፣ የትምህርት እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲስፋፉ እና በአካባቢው የሚገኙ ትንንሽ ከተሞች እንዲያድጉ ከማድረግ አኳያ የሚኖረው ፋይዳም ከፍተኛ ነዉ፡፡ ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በማሳጠር በቂ የሆነ የትራንስፖርት ምልልስ እንዲኖር በማድረግም ሚናው የጎላ ነው።

photo_2021-10-21_11-41-25.jpg0.80 KB