ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 365 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 754,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 531

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 365 名订阅者。

根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 119,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.59%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.42% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 423 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 369
订阅者
+1924 小时
+677
+11930
帖子存档
photo_2021-10-21_11-41-38.jpg1.14 KB

photo_2021-10-21_11-42-04.jpg0.99 KB

photo_2021-10-21_11-42-41.jpg0.58 KB

photo_2021-10-21_11-43-31.jpg0.49 KB

የኤዶ - ሶሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ

ዲማ ራድ ብሪጅ

የሚረዝምው የጅግጅጋ-ገለለሽ ኮንትራት ሁለት እና ሶስት የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+4
የሚረዝምው የጅግጅጋ-ገለለሽ ኮንትራት ሁለት እና ሶስት የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

110 ኪሎ ሜትር የሚረዝምው የጅግጅጋ-ገለለሽ ኮንትራት ሁለት እና ሶስት የአስፋልት መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ ባሳለፍነው በጀት አመት የተጀመረው ይህው ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ ትንንሽና መካከለኛ ማፋሰሻዎችን እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎችን አካቶ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቤአይካ ጄኔራል ቢዝነስ ፒኤልሲ ነው። የግንባታዉ ሙሉ ወጪም (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃያስምንት ሚሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ አራት ሺህ ብር በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ አጠቃላይ ስራውን በሶስት ዓመት ተኩል ዉስጥ ለማጠናቀቅ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የስምምነት ውል የተፈራረመው ይህ የስራ ተቋራጭ ግንባታውን ቀድሞ በመጀመር አጠቃላይ አፈጻጸሙ በአሁኑ ሰዓት 20 በመቶ ላይ ደርሷል ። የመንገዱን የማማከርና የቁጥጥር ስራ ሲ ቴክ ኢንጂነሪንግ ፒኤልሲ (C Tech Enginnering P.L.C) እየሰራ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ በዞን ከተማ 21 ሜትር እና በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ መስመሩ ከሚያስተናግደው የተሸከርካሪ ብዛት፣ ማህበራዊና ኢኮኖማዊ ፋይዳ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ እድገት ጋር ታልሞ በአስፋልት ደረጃ እንዲገነባ እየተደረገ ነው። ግንባታው ሲጠናቀቅ የገለለሽ ፣ ደጋሃመድ እና እንሰግድ አካባቢዎችን ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጅጋ ከሚወስደው ዋና መንገድ ጋር በማስተሳሰር ከዚህ ቀደም በአካባቢው ይከሰት የነበረውን የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ ያስችላል፡፡ ከጅግጅጋ ወደ ደነን የሚወስድ ተለዋጭ መንገድ ስለሚኖረው የአካባቢዉን ማህበረሰብ አማራጭ የትራንስፖርት ተጠቃሚ እንዲሆን ያደርገዋል። በተጨማሪም የጤና ፣ የትምህርት እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲስፋፉ እና በአካባቢው የሚገኙ ትንንሽ ከተሞች እንዲያድጉ ከማድረግ አኳያ የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ነዉ፡፡ ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በማሳጠር በቂ የሆነ የትራንስፖርት ምልልስ እንዲኖር ያደርጋል።

በመቱ-ውጠቴ አውራ መንገድ ላይ ባጋጠመ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት ምክንያት የከባድ ተሸከርካሪዎች ጉዞን ተቋረጦ የነበረው መንገድ ተጠግኖ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የመሬት መንሸራተቱ ያጋጠ
በመቱ-ውጠቴ አውራ መንገድ ላይ ባጋጠመ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት ምክንያት የከባድ ተሸከርካሪዎች ጉዞን ተቋረጦ የነበረው መንገድ ተጠግኖ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የመሬት መንሸራተቱ ያጋጠመው በትላትናው እልት ውጠቴ ቀበሌ ኦዳ ዶጊ በመባል የሚታወቅ ስፍራ ላይ ነው። ይህን ተከትሎም በኢመባ የጅማ ዲስትሪክት ያጋጠመውን የመሬት መንሸራተት በአሰቸኳይ ጥግና በራስ ሀይል በመስራት መስመሩን ክፍት ማድረግ ተችሏል። በአሁኑ ሰአትም መደበኛ የትራንስፖርት ፍሰቱ ወደ ነበረበት ሙሉ ለሙሉ ተመልሷል አካባቢው የመሬት መንሸራተት የሚከሰተበት በመሆኑ ዘላቂ መፈትሄ ለመስጠትም ጥረቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ።

የዶጎሎ-ከለላ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+4
የዶጎሎ-ከለላ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የዶጎሎ ከለላ
+4
የዶጎሎ ከለላ

72 ኪ. ሜትር የሚረዝመው የዶጎሎ-ከለላ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው። እስካሁን ባለው አፈጻጸምም ከ40ኪ.ሜትር በላይ አስፋልት የማንጠፍ ስራ ተከናውኗል። እንዲሁም የአፈር ሙሌትና፣ ድልዳሎ፣የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ እና ድልድዮች ግንባታ ፣ የሰብ ቤዝ ስራ እንዲሁም የቤዝ ኮርስ ማምረት ፣ የአቃፊ ግንብ እና ሌሎች የግንባታ ስራዎች እየተሰሩ ነው በቀጣይ ቀሪ ስራዎች በያዝነው በጀት ዓመት ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። አንድ ቢሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሚሊየን ስምንት መቶ አርባ ስድስት ሺህ ብር ወጪ እየተደረገበት የሚገኘውን ይህን የመንገድ ፕሮጀክት የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ሀገር በቀሉ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ ግንባታውን እያከናወነው ሲሆን የማማከርና የቁጥር ሥራውን ደግሞ ቤዛ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ/ማ እያካሄደው ይገኛል። የዶጎሎ-ከለላ የመንገድ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በአስፋልት ደረጃ እንዲገነባ ሆኗል። መስመሩ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ ዞን ስር የሚገኝ ሲሆን የግንባታው መጠናቀቅ በዋነኝነት የጃማ ወረዳን እና የከለላ ወረዳን ምቹ በሆነ አስፋልት መንገድ ያስተሳስራል ። ግንባታው ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኘውን ከፍተኛ የግብርና ምርቶችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ አምራች እና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል። በተለይም የአባ ጊዮርጊስ ዘ-ጋስጫ ገዳም እና የሼህ ሁሴን መስጊድ በአካባቢው ስለሚገኙ የመንገዱ መገንባት ወደ ስፍራዉ የሚደረገውን ጉዞ ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች አመች ያደርገዋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ የጎን ስፋት በወረዳ 21. ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 8-1ዐ ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው የተገነባው።

የሞጆ - ሃዋሳ የፍጥነት መንገድ አካል የሆነውን የሞጆ - መቂ - ባቱ መዕራፍ አንድ /92 ኪሜ /ፈጣን መንገድ ዛሬ በይፍ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የምዕራፍ አንድ የሞጆ መቂ ባቱ መንገድ ከወራት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዳክተር አቢይ አህመድ መመረቁ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም የፍጥነት መንገዱንለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ በርካታ የማጠቃለያ ስራዎችን ሲከናወኑ ቆይተዋል። ከነዚህም መካከል የክፍያ ጣቢያዎች ግንባታ፣የትራፊክ ምልክቶች ተከላ ቴክኖሎጂን የማሞላት ስራዎችን ጨምሮ ሌሎች ተጓዳኘ ስራዎች ተጠናቀዋል። ይህን ተከትሎም ዛሬ በሞጆ የፈጣን መንገዱ መግቢያ ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት አገልግሎት የማስጀመር መርሃ ግብር ተካሂዷል። የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ዘመናዊና ፈጣን መንገዱ አገልግሎት መጀመሩ ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ ሚናን እንደሚያበረክት ተናግረዋል። የፍጥነት መንገዱ የግብርና ምርታማነትን በመስመሩ የሚገኙትን ሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለጎብኚዎች ተደራሽ በማድረግ እረገድ ዘርፈ ብዙ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል። በመንገዱ ክልል ውስጥ ያሉ ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ላሉ እና በቀጣይ ለመገንባት በታቀዱ ግዙፍ የኢንዱስትሪ እና የአግሮፕሮሰሲንግ ፓርኮች ደረጃቸውን የጠበቀ መንገዶችን በማቅረብ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ በሚደረገው ጥረት የፍጥነት መንገዱ ጉልህ ሚናን ያበረክታል ያሉት ደግሞ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ ናቸው። የሞጆ መቂ ባቱ የፍጥነት መንገድ ከነባሩ መንገድ ትይዩ በአዲስ መልክ ከእንስሳት እና ከሰዎች እንቅስቃሴ ነጻ በሆነ መልኩ የተገነባ እንደሆነም እና ከአዲስ አዳማ የፍጥነት መንገድ በመቀጠል ለአገራችን ሁለተኛው ፍጥነት መንገድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ይህ መንገድ ፍጻሜውን አግኝቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ላስቻሉ ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የምዕራፍ አንድ የሞጆ - መቂ - ባቱ የፍጥነት መንገድ በሁለት ኮንትራት የተከፈለ ሲሆን አሱም ሞጆ - መቂ 56 ኪሜ እና መቂ -ባቱ 36 ኪ.ሜ ናቸው ። ከሞጆ እስከ ባቱ በተዘረጋው 92 ኪሜ ውስጥ 6 ያህል ከነባሩ መንገድ ጋር የሚያገናኙ ማሳለጨዎች ተገንብቶለታል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለእግረኛ ከመንገድ በታች እና በላይ 45 መተላለፊያ አሉት ፡፡ በአጠቃላይ ሞጆ መቂ ባቱን ጨምሮ ሃዋሳ ድረስ የሚዘልቀው 202 ኪ .ሜ የፍጥነት መንገድ የጎን ስፋቱ 32 ሜትር ነው፡፡ የመንገድ አካፋዩ በዚህ ደረጃ እንዲሰፋ የተደረገው በተቃራኒ አቅጣጫ ያለን ተሸከርካሪን በመለየት አደጋን ለማስወገድ አልያም ለመቀንስ ነው፡፡ የመንገዱ አጠቃላይ ወሰን 90 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡ ይህም በቀጣይ ለሚኖረው የማስፋፋት ስራ በቂ ቦታ እንዲኖር የሚያስችል ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂን መሰረት ባደረገ መልኩ ችግኞች መተከል ተጀምረዋል፡፡ በፍጥነት መንገዱ ለመጠቀም የተቀመጠለት የፍጥነት ገደብ በሰአት ከ80 እስከ 120 ኪሜ ነው፡፡ የክፍያ መንገዶች ኢንተር ፕራይስ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙስጠፍ አባሲመል በበኩላቸው ግዙፍ የሀገር ሀብት የፈሰሰበትን መሰረተ ልማት መላው የመንገዱ ተጠቃሚ በባለቤትነት እንዲንከባከበው ጠይቀዋል። የመንገዱ ተጠቃሚዎችም ከአደጋ በጸዳ መልኩ አስፈላጋውን ጥንቃቄ ሁሉ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። ይህ ፈጣን መንገድ 10 ሺ ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ከግብጽ ካይሮ ተነስቶ ደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ድርስ የተዘረጋው የታላቁ የትራንስ አፍሪካን ሃይዌይ የመንገድ ትስስር አካል ነው ፡፡ የፍጥነት መንገዱ የአዲስ አበባ-ሞያሌ-ናይሮቢ-ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል ሲሆን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን በተሻለ ሁኔታ ለመጠቀም የሚያስች ነው። ቀሪ የመንገዱ ክፍል በተሻለ የግንባታ ፍጥነት ሂደት ላይ ይገኛል።

እንኳን ከዘመን ዘመን በጤና አሸጋገራችሁ! አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር እንዲሁም የብልጽግና እንዲሁንላችሁ እንመኛለን።

በከባድ የቋጥኝ ድንጋይ መንሸራተት ምክንያት ተዘግቶ የቀየው የአዲስ አበባ ጎጃም መንገድ በከፊል ተጠግኖ ከትላንት ምሽት ጀምሮ ለትራንስፖርት ክፍት ሆኗል። መንገዱ ክፍት መሆኑን ተከትሎም ምሽቱን እን
+4
በከባድ የቋጥኝ ድንጋይ መንሸራተት ምክንያት ተዘግቶ የቀየው የአዲስ አበባ ጎጃም መንገድ በከፊል ተጠግኖ ከትላንት ምሽት ጀምሮ ለትራንስፖርት ክፍት ሆኗል። መንገዱ ክፍት መሆኑን ተከትሎም ምሽቱን እንዲሁም በአሁኑ ሰዓትም ለቀናት ቆመው የነበሩ መኪኖች መተላለፍ የቻሉ ሲሆን የነበረው መጨናነቅም ወደ መደበኛ ሁኔታው ተመልሷል። በአንድ በኩል የሚያሳልፍ አማራጭ ተለዋጭ መንገድ መሰራቱም የነበረውን የትራፊክ ክምችት እንዲቀንስ አሰተዋጾ አበርክቷል። የአባይ በረሃ አካባቢ የሚንሸራተት ጠመዝማዛና ናዳ የሚበዛበት በመሆኑ እና በዚሁ ስፍራ ከወትሮ የተለየ ግዙፍ ናዳ መከሰቱ ስራውን እጅግ ማክበዱ ይታወሳል ። ሀገራዊ ወሳኝ መተላላፊያ የሆነውን ይህን መሰመር ለመክፈት ኢመባ ቀን ከለሊት ያለሰለስ ጥረት አድርጓል። የተንሸራተተው ናዳ በበርካታ ማሽነሪዎች ብቻ መሰባበር የሚቻል በለመሆኑ ከ160በላይ የድማሚት ፍንዳታዎችን በመጠቀም ቋጥኝ ድንጋዩን በመፈረካክስ ነው መንገዱን ለትራንስፖርት ክፍት ለማድረግ የተቻለው። በስፍራው የስራውን ክብደት ሲከታተሉ የነበሩ በርካታ አሽከርካሪዎች ይህን ከባድ ስራ በቀናት ወስጥ አጠናቆ ለትራንስፖርት ክፍት በማድረጉ ለኢመባ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በቀጣይ የመንገዱን ቀሪ ክፍል ከዘጋው ቋጥኘ ድንጋይ ነጻ ለማድረግና መስመሩን ሙሉ ለሙሉ ወደ ነበረበት ለመመለስ ሲባል ፤ የትራንስፖርት ፍሰቱን ለሰዓታት በመዝጋትና በመከፈት ቀሪ ስራዎቹ እንደሚከናወኑ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ገልጾል።