ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 348 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 755 في فئة النقل والمرتبة 2 537 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 348 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 18 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 91، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 11، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 41.16‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.44‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 491 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 060 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 348
المشتركون
+1124 ساعات
+477 أيام
+9130 أيام
أرشيف المشاركات
በጅማ-ጭዳ መንገድ ግንባታ ሂደት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው። ጅማ ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ)፥ የኦሮሚያ እና የደቡብ ምዕራብ ክልሎችን በዋናነት የሚያስተሳስረው የጅማ-ጭዳ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። መንገዱ በስራ ተቋሯጩ የፕሮጄክት አስተዳደር ችግር እና ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዙ ጉዳዮች በእቅዱ መሰረት ማከናወን ያልተቻለበት ሁኔታዎች ተፈጥረዉ ነበር። የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር የፕሮጄክቱን ግንባታ ከሚያካሂደው ስራተቋራጭ ጋር በመቀናጀት እና ተገቢዉን ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ አሁን ላይ በፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት ላይ አዎንታዊ ለዉጦች መመዝገብ ጅምረዋል። የመንገዱ አጠቃላይ ርዝመት 80 ኪሎ ሜትሮችን የሚሸፍን ሲሆን ፣ በገጠር 10 ፣ በከተማ ደግሞ ከ12.4 እስከ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት የሚገኘው። ግንባታው ቻይና ቲሲጁ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ በተባለ የቻይና ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ የጃፓኑ ኩዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ ከኦሬንታል ኮንሰልቲንግ ግሎባል እና ከኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ጋር በጋራ በመሆን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ለመንገዱ ግንባታ ወጪ የሚሆነው 2,422,629,267 ብር ሲሆን ፣ የዚህ ግንባታ ሙሉ ወጪም በአፍሪካ ልማት ፈንድ (African Development Fund) እና በአለም አቀፍ የጃፓን ትብብር ኤጀንሲ (Japan International Cooperation Agency) የተሸፈነ ነው፡፡ መንገዱ ሲጠናቀቅ በኦሮሚያ እና ደበቡብ ምዕራብ ክልሎች የሚገኙ የጅማ ፣ ዋሮ ፣ ኮሎቦ ፣ ኦፎሌ ፣ ዴዶ ፣ ሚጤሶ ፣ ደልቢ ፣ ቂራራ ፣ በቲቲበዱዳ ፣ ንቲቲጎላ እና ጭዳ ከተሞችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ይበልጥ ያጠናክራል። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ተደራሽነቱን በማስፋት በህብረተሰቡ ላይ የሚከሰተውን የትራንስፖርት አገልግሎት መጉላላት ይቀንሳል ተብሎ ይታመናል። በተጨማሪም አካባቢው የቅይጥ ግብርና እና የእንስሳት እርባታ የሚከናወንበት በመሆኑ የመንገዱ ግንባታ መጠናቀቅ እነዚህን የግብርና ውጤቶች ሳይበላሹ በጥራትና በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል፡፡ ከዚህም ባሻገር መንገዱ የኮይሻ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ግድብ ግንባታ ፣ የሃላላ ኬላ ሎጅ እና የኮይሻ ገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ( ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ) መዳረሻ በመሆኑ ግንባታው ሲጠናቀቅ የአካባቢውን የቱሪዝም ዘርፍ ከማሳደግ አኳያም ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት" እንኳን ለ116ኛው የሠራዊት ቀን አደረሳችሁ
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት" እንኳን ለ116ኛው የሠራዊት ቀን አደረሳችሁ

በመንገድ ደህንነት ኦዲተርና ኢንስፔክተርነት ላይ ያተኮረ ስልጠና በኢትዮጵያ ሆቴል እየተሰጠ ነዉ በመንገድ ደህንነት ኦዲተርና ኢንስፔክተርነት የመጀመሪያ ደረጃ የሙያ ማረጋገጫ ስልጠና ከጥቅምት 05/02/16 ዓ.ም ጀምሮ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተወጣጡ መሀንዲሶች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ስልጠናውን ያስጀመሩት የመንገድ ሀብት ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር አለማየሁ አየለ ስልጠናው ኢመአ ከሚገነባቸውና ከሚያስተዳድራቸው መንገዶች የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ደህንነት እና የአደጋ ቅነሳ ጋር በተገናኘ የሚስተዋሉ ችግሮችን ላይ መፍትሄ ለማምጣት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም የመንገድ ደህንነት ቅድሚያ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር መሆኑን ጠቁመው ሰልጣኞች በንቃት መከታተልና ራሳቸውን ለበለጠ ውጤት ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውና ለአምስት ቀናት የሚቆየው የሰርተፊኬሽን ስልጠና በሁለት ዙሮች ተከፍሎ 50 የተቋሙ መሀንዲሶችን ብቁ ለማድረግ የሚያግዝ ነው፡፡ በመሆኑም ስልጠናው በተለያዩ መንገዶች ላይ በትራፊክ አደጋ ምክንያት የሚከሰቱ የሞትና የንብረት አደጋ መንስኤዎችን ለይቶ በማውጣት ችግሩን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎችን ለመስራትና መፍትሄ ለማምጣት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ በመንገድ ደህንነት ኦዲተርና ኢንስፔክተርነት ያተኮረው ስልጠና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በዘርፉ ልምድ ካለው (ስዊሮድ) የስዊድን ብሔራዊ የመንገድ አማካሪ (Sweroad) Swedish National Road Consulting ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የባሌ ጎባ-በርበሬ-ዶሎመና ሎት-1 የ133 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ በመከናወን ላይ ነው አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 06፣ 2016 (ኢ መ አ):-በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ባሌ ዞን የጎባ-ዶሎመና-ነገሌ ቦረና/ ቢታታ ፕሮጀክት አካል የሆነው የባሌ ጎባ-በርበሬ-ዶሎመና 133 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ በመከናወን ላይ ነው፡፡ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ዓለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ሲሆን፥ አሁን ላይ የዲዛይን፣ የቅየሳ፣ የካምፕ ግንባታ እንዲሁም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ሥራዎችን በመሥራት ላይ ይገኛል። ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ ይሠራል። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና በአገልግሎት ብዛት በእጅጉ የተጎዳ በመሆኑ፣ ብሎም ካለው በርካታ ሀገራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጠቀሜታ አንፃር በአስፋልት ደረጃ ነው የሚገነባው። ይህ ፕሮጀክት፣ ከአዲስ አበባ - በሻሸመኔ - አዳባ - ባሌ ሮቤ የሚዘልቀው ዋና መንገድ ላይ ከባሌ ሮቤ ተገንጥሎ ወደ ጎባ - ዶሎመና የሚወስደው መንገድ አካል ነው፡፡ የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ፣ በምዕራብ ባሌ ዞን የጎባ ከተማ እንዲሁም የጎባ፣ በርበሬ፣ ዶሎመና ወረዳዎችን እና በርካታ ቀበሌዎችን በቅርበት ያገናኛል። በሥፍራው የሚገኘውን የሳነቴ ፓርክ ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ በኩልም የጎላ አስተዋጾዖ ያበረክታል። በዞኑ በስፋት የሚገኘውን የማር እንዲሁም የስንዴ፣ገብስ ጤፍ እና መሰል ምርት ውጤቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ በጥራት እና ፍጥነት ማድረስ ያስችላል። የመንገድ ፕሮጀክቱ አነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች፣ ከልቨርቶች እንዲሁም የ14 ድልድዮች ግንባታ ሥራ ያካትታል፡፡ መንገዱ፣ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 8-10 ሜትር ስፋት ሲኖረው፣ በቀበሌ የእግረኛ መንገድና የመኪና ማረፊያ ጨምሮ 17 ሜትር እንዲሁም በወረዳ የመንገድ አካፋይ፣ የእግረኛ መንገድና የመኪና ማረፊያ ጨምሮ 22.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጒ ነው የሚገነባው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በወሰን ማስከበርበ ችግር የተጓተተው የአሳይታ - አፋምቦ - ጅቡቲ ድንበር መንገድ Etv በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et