ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 361 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 755,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 361 名订阅者。

根据 18 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 91,过去 24 小时变化为 11,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.44% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 491 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 351
订阅者
+1124 小时
+477
+9130
帖子存档
የገበታ ለሀገር ሐላላ ኬላ ሪዞርት

የመንገድ ፈንድ ለመንገዶች ጥገና አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። አዲስ አበባ፣ ሚዚያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የመንገድ ፈንድ ለመንገዶች ጥገና በጀት ምንጭ በመሆን አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ መንገዶች ተገቢውን ጥገና በወቅቱ እንዲያገኙ እና ለመንገድና ትራፊክ ደህንነት ሥራዎች ማስፈፀሚያ በቂና የማያቋርጥ የገንዘብ ፈሰስ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ገቢን ለማሰበሰብና ለማስተዳደር የመንገድ ፈንድ በአዋጅ ቁጥር 66/89 ተቋቋመ። የመንገድ ፈንድ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በአዋጁ ከተፈቀዱ የገቢ ምንጮች ማለትም ከነዳጅ (ታሪፍ)፣ ከቅባትና ዘይት (ታሪፍ)፣ ከመንገድ ጠቀሜታና በክብደት ላይ ከተመሰረተ ዓመታዊ የፈቃድ ማደሻ ክፍያ ገቢ በማሰባሰብና ለፌዴራል፣ ለክልል እና ለተለያዩ ከተማ መንገድ ኤጀንሲዎች በመመደብ ከ550,000 ኪ.ሜ (ከአምስት መቶ ሃምሳ ሺህ ኪሎ ሜትር) በላይ መንገዶች የጥገና ሥራ እንዲከናወን የበጀት ድጋፍ በማድረግ ለመንገድ ዘርፉ የማይናቅ አስተዋፅኦ ስያበረክት ቆይቷል፡፡ በ2015 በጀት ዓመትም ለመንገድ ጥገና የሚውል ብር 510,950,000.00 (አምስት መቶ አስር ሚሊዮን፣ ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) የመንገድ ፈንድ ገቢ ተሰበስቧል፡፡ ገቢው የተሰበሰበው በነዳጅ ላይ ከተጣለ ታሪፍ ብር 304,660,000፣ ከተሸከርካሪ ዘይትና ቅባት ብር 2,590,000.00፣ ከመንገድ ጠቀሜታ ክፍያ ብር 1,670,000.00 እና በክብደት ላይ የተመሰረተ የተሸከርካሪ ፈቃድ ማደሻ ብር 207,740,000.00 ነው፡፡ የተሰበሰበውን ገቢ ለመንገድ ጥገና ከማዋል አንፃርም በዘጠኝ ወራት ጊዜ ውስጥ ለኢመአ የመንገድ ጥገና እና የአማካሪ ድርጅቶች ክፍያ ብር 1,637,020,000.00 ፣ለክልል ገጠር መንገዶች 317,530,000.00 ፣ ለከተማ መንገድ ኤጀንሲዎች 102,160,000.00፣ ለድጋፍ ሰጪ ለክልልና ከተሞች ብር 16,960,000 እንዲሁም ለመልሶ ግንባታ ብር 109,510,000 በድምሩ ብር 2,727.53 ክፊያ ተፈጽሟል፡፡ በመስክ ምልከታ Value for money ከማረጋገጥ አንጻርም ከመንገድ ኤጀንሲዎች በሚቀርቡ የአፈጻጸም ሪፖርቶችን መገምገምና ግብረመልስ መስጠት፣ የመስክ ክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን መስራትና የቴክኒካል ኦዲት የማድረግ ሥራ ተሰርቷል፡፡ በዘጠኝ ወራት የክትትልና ግምገማ ከተሰራባቸው የመንገድ ኤጀንሲዎች መካከል፣ 1. የባህር ዳር ከተማ መንገዶች ባለስልጣን 2. የሲዳማ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 3. ቤንሻንጉል ክልል መንገድና ትራንስፖርት ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 4. በአሶሳ ማዘጋጃ ቤት 5. በደቡብ መንገዶች ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 6. በኦሮሚያ መንገዶችና ሎጂስቲክስ ቢሮ ም/ሸዋ ዲስትሪክት ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 7. በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች ይገኙበታል፡፡ የመስክ ምልከታ ሥራ የተሰሩ ሲሆን በተደረገዉ ምልከታም ፡- 1. መሬት ላይ ያለዉ ሥራ እና እቅዳቸዉ እንዲናበብ የምክር አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡ 2. በክፍያ ሰርተፊኬት ክፍያ የተጠየቀባቸዉ ነገር ግን ያልተከናወኑ ሥራዎች ከክፍያ ሰረተፊኬት እንዲቀነሱ ተደርጓል፡፡ 3. ክፍያዎች ሲጠየቅ ስቴሽን እና ዳይሜንሽን ሳይቱ ላይ ባለው መረጃ መሰረት ባለመቅረቡ እንዲስተካከል ተጠይቋል፡፡ 4. ለሁሉም የኳሪ ሳይቶች ላብራቶሪ ፍተሻ እንዲደረግ አቅጣጫ ተሰቷል፡፡ በሳይት ምልከታ ወቅት የተስተዋሉ የመንገድ ኤጀንሲዎች የአቅም ውስንነት በስልጠና የማብቃት ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ በመሆኑም የመንገድ ፈንድ በጀት ለታለመለት ዓላማ መዋል አለመዋሉን በመስክ ምልከታ ወቅት የመዳሰስ ሥራ ተሰርቷል፡፡ በመጨረሻም የመንገድ ጠቀሜታ ክፊያም በጦርነት ምክንያት በሑመራ እና በሱዳን ድንበር ተሸከርካሪ ስለማይገባ ሽያጭ ባለመኖሩ በበጀት ዓመቱ ገቢ አሰባሰብ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ነበረው፡፡ ከሃምሌ/2015 ጀምሮ ነዳጅ ላይ ከተጣለ ታሪፍ ይሰበሰብ የነበረውም ገቢ በመቆሙ ገቢ አሰባሰቡ ለካይ ከፍተኛ ጫፋ ያሳደረ ቢሆንም ችግሩ ከሚያዝያ/2015 ጀምሮ ወደ ነበረበት እንዲመለስ በገንዘብ ሚኒስቴር ተወስኗዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የአምቦ ወሊሶ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው እና 63 ኪሎሜትር ርዝማኔ የሚሸፍነው የአምቦ ወሊሶ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነዉ፡፡ የመንገድ ግንባታዉ ከዚህም ቀደም በነበረው የሥራ ተቋራጭ አቅም ውስንነት ፣ በወሰን ማስከበር ችግር በተለይም በአፈር እና የድንጋይ ማውጫ ቦታዎች ተደጋጋሚ የስራ ማስቆም እንቅስቃሴ የነበረ በመሆኑ እንዲሁም በሲሚንቶ እጥረት እና በሰላም እና ፀጥታ ችግሮች ምክንያት በተያዘለት ጊዜ እንዳይጠናቀቅ እክል ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በኢመአ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካለት ጋር በተደረገው ጥረት መሻሻል በመታየቱ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል፡፡ በእስከአሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ የተሰሩ ስራዎች 315,754.41 ሜትር ኪዩብ የአፈር ቆረጣ ስራ ፣ 212,591.31 ሜትር ኪዩብ የአፈር ሙሌት ስራ ፣ 25.62 ኪሎ ሜትር የሰብ ቤዝ ስራዎች ፣ 17.63 ኪሎ ሜትር የቤዝ ኮርስ ስራ ፣ 15 ፓይፕ ከልቨርት ፣ 4 ሰላብ ከልቨርት እና 5 የድልድይ ግንባታ ስራዎች ተከናዉነዋል፡፡ በተጨማሪም የአስፓልት ማንጣፍ ስራም ተጀምሯል፡፡ የመንገድ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ሲሆን ፣ የማማከር እና ቁጥጥር ስራውን ደግሞ ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላ.የተ.የግል ማህበር ከ ጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ጋር በጣምራ እያከወኑት ይገኛሉ፡፡ ግንባታውን ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው ገንዘብ 1,264,907,396.11 ብር ሲሆን ፣ የሚሸፈነዉም በኢትዮጵያ መንግስት ነዉ፡፡ ቀደም ሲል የነበረዉ የመንገዱ ሆኔታ በጥርጊያ ደረጃ ላይ የነበር ሲሆን ፣ ለትራንስፕረት በጣም አስቸጋሪ እና ጠባብ መንገድ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት የእግረኛ መንገድን ጨምሮ በገጠር 7 ሜትር እና በከተማ ደግሞ 21 ሜትር ተጨማሪ የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በ125 ኪ.ሜ ርቀት ከምትገኘዉ አምቦ ከተማ መነሻዉን በማድረግ ወሊሶ ከተማ ላይ ያበቃል፡፡ ይህ ፕሮጀክት ምዕራብ ሸዋ(አምቦ) እና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ(ወሊሶ) ከተሞችን የሚያገናኘ ሲሆን ፣ በዉስጡም፡- ጭቱ ወረዳን ጨምሮ ዳርያን ፣አልቱፋ ሰንኮሌ ቀበሌዎችን በቅርበት ያስተሳስራል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል እና ለመደገፍ እንዲቻል በተቋሙ በቅርቡ ከተከፈቱት የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማጅመንት ፅ/ቤቶች አንዱ የሆነዉ የአምቦ እና አካባቢዉ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ፅ/ቤት የዚህን መንገድ ግንባታን ጨምሮ በስሩ የሚገኙትን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች በጥራትና በተያዘላቸዉ የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ለማስቻል አስፈላጊውን ክትትልል እና ድጋፍ ያደርጋል፡፡ የዚህ መንገድ መገንባት የህብረተሰቡን የትራንስፖርት ችግር ከመቅረፍ ባሻገር በአካባቢዉ የሚመረቱ እንደ ጤፍ ፣ እንሰት ፣ ገብስ እና በቆሎ የመሳሰሉ የአዝዕርት ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገቢያ በማድረስ አምራችና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በተጨማሪም ትልቁ የቱሪዝም መዳረሻ ‘’የወንጪ ሃይቅ’’ በፕሮጀክቱ አጋማሽ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ የመንገዱ መገንባት ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ትልቅ አበርክቶት ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ዒድ ሙባረክ! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 444ኛው ዓመተ-ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆን
ዒድ ሙባረክ! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 444ኛው ዓመተ-ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ይመኛል!! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ8 ሺህ 300 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች የጥገና ሥራ ተከናወነላቸው። አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 12፣ 2015 (ኢመአ):- በ 2015 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ8 ሺህ 300 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች የጥገና ሥራ ተከናወነላቸው። የመንገድ ፕሮጀክቶቹ የተጠገኑት በራስ-ኃይል የመንገድ ጥገና ዲስትሪክቶች ፣ በመንግስትና በግል የሥራ ተቋራጮች አማካኝነት ነው። በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጠሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን ፥በእቅድ በመያዝ ነው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ ያደረገው ። ከቅድመ-ጥንቃቄ ሥራዎች አንስቶ የመደበኛ፣ ወቅታዊ፣ የከባድ እና የድንገተኛ ጥገናዎች ናቸው እየተከናወኑ የሚገኙት። በዚህም መሠረት በመደበኛው 7 ሺህ 9 መቶ 40 ኪ.ሜ እንዲሁም በ ወቅታዊ 3 መቶ 97 ኪ.ሜ ርዝመት ባላቸው መንገዶች ላይ የጥገና ሥራ ተሠርቷል፡፡ የከባድ እና ኦቨርሌይ ጥገና እየተከናወነላቸው ከሚገኙ ፕሮጀክቶቸ መካከል የሚሌ-ጋላፊ፣ የወልዲያ-ፍላቂት እንዲሁም የአዋሽ-ቁልቢ-ድሬዳዋ/ሐረር አስፋልት ኦቨርሌይ ኮንትራት 1እና 2 ፕሮጀክቶች ይጠቀሳሉ፡፡ ተቋሙ፣ ይህን የጥገና ሥራ አጠናክሮ በመቀጠል በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ከ 13 ሺህ 400 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው መንገዶችን ለመጠገን ነው አቅዶ እየሠራ የሚገኘው። በቀጣይም የመንገድ ጥገና ሥራውን ቀልጣፋ እና ተደራሽ ለማድረግ እንዲቻል ኢ.መ.አ በቅርቡ የተለያዩ የግንባታ ማሽነሪዎችን ግዢ በመፈጸም ለሁሉም የጥገና ዲስትሪክቶች እንዲሰራጩ አድርጓል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

መልካም የትንሳኤ በዓል! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵ
መልካም የትንሳኤ በዓል! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ይመኛል!!

የመንገድ ዘርፍ ንዑሳን ፕሮግራሞች የመንገድ ዘርፍ የአስር ዓመት መሪ እቅድ ሲዘጋጅ የመንገድ ሀብት ማኔጅመንት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡ በተለይም የፌዴራል መንገዶች ከሚያስታናግዱት የትራፊክ መጠንና ከሚኖራቸው ፋይዳ አኳያ ራሱን የቻለ የመንገድ ሀብት ማኔጅመንት ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲዘጋጅ ተደርጓል፡፡ የዚህ ፕሮግራም ዓላማ ባለፉት ዓመታት በሀገራችን በተለያዩ ጊዜያቶች በከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የተገነቡ የመንገድ ሀብቶቻችንን ለታሰበላቸው ጊዜ በአስተማማኝ ሁኔታ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ነው፡፡ በተመሳሳይ የተለያዩ የጥገና ዘዴዎችን በመጠቀም የወረዳ /URRAP/ መንገዶችን የመንከባከብ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡ በአስር ዓመቱ የመንገድ ልማት መሪ እቅድ ከዚህ ቀደም በነበሩት የመንገድ ዘርፍ ፕሮግራሞች ከተለመዱ ፕሮጀክቶች ባለፈ ሀገሪቱ አሁን የደረሰችበትን የእድገት ደረጃ መሰረት በማድረግ የሚከተሉት ተጨማሪ ሀሳቦች እና ንዑስ ፕሮግራሞች ተካተዋል፡፡ - የአገሪቱን የረጅም ጊዜ (የ30 ዓመት) የመንገድ ትስስር ታሳቢ ያደረጉ የፍጥነት እና ቀለበት መንገዶች /Expressways and Ring – Roads/ አካል የሆኑ መንገዶች ይገነባሉ፡፡ - በአንጻራዊነት ትላልቅ በሆኑ (ዋና ዋና) ከተሞች ተለዋጭ መንገዶችን /Bypass Roads/ እና የቀለበት መንገዶችን /Ring – Roads/ በመስራት በግንባታ ወቅት በከተሞች አካባቢ የሚያጋጥመውን የወሰን ማስከበር ችግር እና የተፈጠረን ሀብትና መሠረተ ልማት የማፍረስ ጥሩ ያልሆነ ተሞክሮ በማስቀረት ተጨማሪ መሠረተ ልማት የመገንባት እንዲሁም የተደራሽነት እና የእንቅስቃሴ ፍላጎቶችን /Accessibility and Mobility Functions/ አመጣጥኖ እና አቀናጅቶ በመሥራት የመንገድ ደህንነት ችግር መሠረታዊ በሆነ መልኩ ለመቅረፍ ይሰራል፡፡ - የሚገነቡት መንገዶች አገሪቱን ከተለያዩ ወደቦች፣ ከጎረቤት አገራት እንዲሁም በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ህዝቦችን የማስተሳሰር፣ እምቅ አቅም ያላቸውን ቦታዎች የመክፈት፣ ሌሎች ክፍላተ-ኢኮኖሚዎችን በተጨባጭ የመደገፍ እና የተመጣጠነ እድገትን የማሳለጥ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ - የክልል መንገድ ባለስልጣናት ከተለመደው የጠጠር እና የከተማ የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶች ባለፈ የተለያዩ አካባቢዎችን የሚያገናኙ አስፋልት መንገዶችን ይገነባሉ/ያስገነባሉ፡፡ - በወረዳ ደረጃ ከሚሰሩ የገጠር መንገዶች በተጨማሪ በአርብቶ እና ከፊል አርሶ አደር እንዲሁም የመሬት አቀማመጣቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች የመንገድ ተደራሽነትን ለማሻሻል በአነስተኛ ወጪ የሚገነቡ ስትራክቸሮችን (ፎርዶችን፣ ልዩ ልዩ ከልቨርቶችን፣ ተንጠልጣይ የእግረኛና እንስሳት መሻገሪያ ድልድዮችን፣ ወ.ዘ.ተ.) በተመረጡ አካባቢዎች ላይ እንዲገነቡ ይደረጋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በጀማ ወንዝ ላይ ጊዜያዊ መሸጋገሪያ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። አለም ከተማ ፣ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የጀማ ወንዝ የብረት ድልድይ ወደነበረበት እስኪመለስ በተሰራው ጊዜያዊ
+2
በጀማ ወንዝ ላይ ጊዜያዊ መሸጋገሪያ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። አለም ከተማ ፣ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የጀማ ወንዝ የብረት ድልድይ ወደነበረበት እስኪመለስ በተሰራው ጊዜያዊ መሸጋገሪያ ተሽከርካሪዎች መጓዝ ጀምረዋል፡፡ የጀማ ወንዝ የብረት ድልድይን ወደነበረበት ለመመለስ የ24 ሰዓት የጥገና ሥራ እየተካሄደ መሆኑን መግለጻችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ቆመው የነበሩ ተሽከርካሪዎች በጊዜያዊነት የሚተላለፉበት መሸጋገሪያ ተሰርቶ በአሁኑ ወቅት ተሽከርካሪዎች በመሻገር ላይ ይገኛሉ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዋናውን የብረት ድልድይ ወደነበረበት ለመመለስ እየተደረገ ያለው ርብርብም እንደቀጠለ ሲሆን ድልድዩን መልሶ በመገጣጠም ለትራፊክ ክፍት እስኪሆን ሕብረተሰቡ በትዕግስት እንዲጠብቅና ጊዜያዊ መሸጋገሪያውን በጥንቃቄ እንዲጠቀም በድጋሚ በታላቅ ትህትና እናስታውቃለን፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የደባርቅ እና ጃናሞራ ወረዳዎችን የሚያገናኘው የበለስ-መካነ ብርሃን 39 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ 60 በመቶ ደርሷል:: ጎንደር፣ መጋቢት 29፣ 2015(ኢ መ አ):- በሰሜን ጎንደር ዞን የደባርቅ እና ጃናሞራ ወረዳዎችን የሚያገናኘው የበለስ-መካነ ብርሃን 39 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ግንባታ 60 በመቶ ደርሷል። ግንባታውን 'መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ' ከፌደራል መንግስት በተመደበ 1,018,952,362.90 (አንድ ቢሊዮን አስራስምንት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺ) ብር ወጪ በማከናወን ላይ ይገኛል። 'በለስ ኮንሰልቲን ኃ/የተ/የግ/ድ' የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ይሠራል። ከግንባታው ክንውኖች መካከልም የሰብቤዝ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ማምረት እና የበርካታ ቆረጣ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በተጨማሪም የስምንት ከፍተኛ ድልድዮች ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ሁለቱ በግንባታ ላይ ይገኛሉ። የአካባቢውን አስቸጋሪ መልካዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ተከትሎ ለግንባታው አስፈላጊ የሆኑ በርከት ያሉ ማሽነሪዎች መሰማራታቸውን በተደረገው የመስክ ቅኝት መመልከት ተችሏል። ለግንባታው መዘግየት በምክንያትነት የተቀመጡት የጸጥታ ችግር፣ የግብዓት እጥረት እና የሥራ ተቋራጩ የአፈጻጸም ውስንነቶች፣ በኢመአ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ጥረት መሻሻል በማሳየታቸው፣ ፕሮጀክቱ አሁን በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል። በቀጣይም ፕሮጀክቱ በማኅበረሰቡ ጥያቄ መሠረት እንዲሁም ካለው በርካታ አገራዊ ፍይዳ አንፃር፣ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲያድግ በመንግስት ተወስኖ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። ፕሮጀክቱ ለ600 ያህል ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ የዕውቀት እና የልምድ ሽግግር እንዲፈጠር አስችሏል። መንገዱ ዕውን ሲሆን፥ በዋናነት የደባርቅ እና ጃናሞራ ወረዳዎችን በቅርበት ያገናኛል። በተለይም ለዘመናት በመንገድ መሠረተ-ልማት እጦት ተራርቀው የነበሩትን የሁለቱን ወረዳ ነዋሪዎች ደረጃውን በጠበቀ መንገድ የሚያገናኝ ነው። የጤና፣ የትምህርት እና መሰል ማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነት ያሰፋል። በሥፍራው የሚመረቱትን የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የሰብል ምርቶች በስፋት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ የአርሶ-አደሩን ተጠቃሚነት ያሳድጋል። ከዚህም ባሻገር የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ እንደመሆኑ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት ረገድ የጎላ ሚና አለው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጀማ ወንዝ የብረት ድልድይን ወደነበረበት ለመመለስ የ24 ሰዓት የጥገና ሥራ እየተካሄደ ነው፡፡ አለም ከተማ ፣ መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ የመደርመስ አደጋ የደረሰበትን የጀማ ወንዝ የብረት ድልድይ ቀድሞ ወደነበረበት በመመለስ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል የ24 ሰዓት የጥገና ሥራ እየተካሄደ ነው፡፡ አንድ መቶ ሜትር ርዝማኔ ያለው የብረት ድልድይ ላይ አደጋው የደረሰው መጋቢት 27 ቀን ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ነበር። የአደጋው ምክንያት ተከታትለው ይጓዙ የነበሩት ከባድ የጭነት መኪኖች በአንድ ጊዜ ደልድዩ ላይ መገኘታቸው ነበር። ይህንን ችግር ለመቅረፍ የኮከብ መስክ አለም ከተማ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን የሚያካሂደው “CSCEC፦China state construction engineering company” የተባለው ተቋራጭ አስፈላጊውን የጥገና ሥራውን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የመንገድ ተጠቃሚው ሕብረተሰብም ድልድዩ በአጭር ጊዜ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት እስኪጀምር በትዕግስት እንዲጠብቅ ኢመአ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ለድልድዩ መደርመስ ዋናው ምክንያት ከአቅም በላይ ክብደት መጫን በመሆኑ ከተፈቀደ የክብደት በላይ መጫን በመንገድ ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከግምት ውስጥ በማስገባት መንገዶችን ከብልሽት ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት የመንገድ ተጠቃሚዎች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉም እንጠይቃለን፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያበቃውን የISO 9001፡2015ን የኳሊቲ ማኔጅመንት ስታንዳርድ ሰርተፊኬት ባለቤት ሊሆን ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዓለማቀፋዊ ብቃት እና ምርጥ መንገዶች ለበለጸገች ኢትዮጵያ በ2022 የሚለውን ራዕዩን ለማሳካት በርካታ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ከእነዚህም እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ ተቋሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያበቃውን ISO 9001፡2015ን የጥራት ማኔጅመንት ስታንዳርድን ሰርቲፋይድ ማስደረግ ነው ፡፡ የ ISO 9001: 2015 ሰርተፊኬት ተጠቃሚ መሆን ደንበኞቻችን ጥራት ያለው አገልግሎት ማግኘታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል እና የተቀላጠፈ አሰራር ለማስፈንና እና ብክነትን ለመቀነስ እንዲሁም የተሻለ እና ወጥ ቁጥጥር ለማካሄድ ያስችላል፡፡ ኢመአ የዚህ ሰርተፊኬት ባለቤት ለመሆን የሚያስችለውን ተግባር ለማከናወን ይቻል ዘንድ ኳሊቲ ግሮውዝ ሰርቪስ ሃ.የተ.የግ ኩባንያ የተባለ የሕንድ ኩባንያ እና ቢልባስ ኢንተግሬድ ማኔጅመንት ኮንሰልታንትስ አማካሪዎች ቅጥር በማከናወን ሥራው ተጀምሯል፡፡ አማካሪ ድርጅቱ የ ISO 9001: 2015 የቅሬታ ማኔጅመንት ሥርዓት (compliant management system) እና የጥራት ማኔጅመንት ሥርዓት (quality management system) የጥናቱን የመጀመሪያ ሪፖርት መጋቢት 19 ቀን 2015 አቅርቧል፡፡ በእለቱ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች የተወጣጡ ዳይሬክተሮች፣አማካሪዎች እንዲሁም የዲስትሪክት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በቀረበው ሪፖርት ላይ የ ISO (compliant management system)እና (quality management system) ምንነት፣ አስፈላጊነት ፣ፕሮጀክቱ የሚገኝበትን አሁናዊ እንቅስቃሴና አካሄድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ተጨባጭ በሆነ መልኩ ተግባር ላይ በሚውልበት ጊዜ ኢመአ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከማስቻሉም ባለፈ ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ዘላቂና ወጥ በሆነ መንገድ ለመተግበር የሚያስችለው መሆኑ ተገልጿል፡፡ በተያያዘም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተቋማዊ ራዕዩንና ተልዕኮውን ዕውን የማድረግ እንቅስቃሴ በማጎልበት የISO የጥራት ማረጋገጫ መስፈርቶችን፣ውጤታማ የሆነ የአመራር መመዘኛዎችን በሟሟላት የሚሰጣቸውን ግልጋሎት አስተማማኝና ወጥነትን ለማረጋገጥ የሚያግዘዉ መሆኑ ተጠቅሷል:: ይህ ፕሮጀክት ተቋሙ የጥራት ደረጃውን የጠበቀ የአሰራርና የውሳኔ ስርዓት እንዲኖር ከማገዙ ጎን ለጎን የተጣለበትን ኃላፊነት በተገቢው መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ ያስችለዋል:: በማጠቃለያውም የፕሮጀክት ሪፖርቱን አስመልክቶ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በአማካሪ ድርጅቱ በኩል ምላሽ ተሰጥቶበታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et