uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 593 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 743-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 495-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 593 obunachiga ega bo‘ldi.

10 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 303 ga, so‘nggi 24 soatda esa 16 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 36.75% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.14% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 995 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 058 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 11 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 593
Obunachilar
+1624 soatlar
+677 kunlar
+30330 kunlar
Postlar arxiv
በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ኢትዮጵያን ከኤርትራ ጋር የሚገናኘው የአሰብ ኮሪደር (ሜሎዶኒ መገንጠያ -ማንዳ-ቡሬ) የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ 71 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና በመንግሥት በተመደበ 2,085,985,162.61 (ሁለት ቢሊዮን ሰማንያ አምስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሁለት ብር ከስልሳ አንድ ሳንቲም) በአስፋልት ኮንክሪት እና በሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ደረጃ እየተገነባ ነው። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በሀገራዊ እና ቀጠናዊ ትስስሩ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት መልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ ሜዳማ ፣ ዳገታማ እና ተራራማ ሲሆን ፤ ከአዲስ አበባ 787 ኪሜ ርቀት ላይ ከኤሊ ዳር ከተማ 16 ኪሜ በኃላ ጀምሮ ኢትዮ ኤርትራ ድንበር ላይ ያበቃል፡፡ የአሰብ ኮሪደር (ሜሎዶኒ መገንጠያ ማንዳ ቡሬ) የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመካሄድ ላይ የሚገኘው ሻንዶንግ ሉሽያዎ ግሩፕ ካምፓኒ ሊሚትድ በተባለ የውጭ ሀገር የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ደግሞ ስሜክ ኢንተርናሽናል ፕራይቬት ሊሚትድ እና ቫልዩ ኢንጅነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በንኡስ አማካሪነት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በገጠር፡- 10 ሜትር እና በቀበሌ ከተሞች ደግሞ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በከፊል በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ይኸው መንገድ ፤ በአሁኑ ወቅት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ኮንክሪት እና በሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ደረጃ እየተገነባ ነው። ፕሮጀክቱ የአፈር ጠረጋ ፤ ቆረጣ እና ሙሌት ፤ ሰብቤዝ ፤ ቤዝ ኮርስ ፤ የአስፋልት ንጣፍ ፤ የሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ፤ የአራት ድልድዮች ግንባታ ፤ እንደ ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች ያሉ የውሃ ማስተንፈሻ ስራዎችን እንዲሁም የመንገድ ምልክቶችን መትከል እና የመንገድ ቀለም መቀባት የመሳሰሉ ሌሎች ልዩ ልዩ ተግባራትን ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ አስካሁን 35 ኪሎ ሜትር (50%) የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፤ 18 ኪሎ ሜትር (26%) የሳብቤዝ ስራውም አልቋል። ከዚህም ባሻገር 5 ኪ.ሜ (7%) የቤዝ ኮርስ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፤ የአስፋልት እና የሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ስራ ለመጀመር የሚያስችል የዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡ በተጨማሪም የአራት ድልድዮች የዲዛይን ስራ የተጠናቀቀ ከመሆኑም ባሻር ፤ 27% እንደ ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች የመሳሰሉ የውሃ ማስተንፈሻ ስራዎች ተከናውነዋል። በዚህም መሰረት ግንባታው በመጪው ሀምሌ ወር 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይታመናል፡፡ ባለፉት ጊዜያት እንደሀገር የተከሰተው ከፍተኛ የሲሚንቶ እጥረት፤ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት የግንባታ ግብአቶችን ወደ ሳይት ማስገባት አለመቻል እና በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ተቀብረው ያልመከኑ ፈንጂዎች መኖር በግንባታ ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ ቢያሳድሩም ፤ እነዚህን ችግሮች በመቋቋም ግንባታው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ህዝቦችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር በማጠናከሩ ረገድ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል፡፡ በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች የትምህርት ፣ የጤና እንዲሁም መሰል ግልጋሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ቢሾፍቱ፣ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ ለትግራይ ክልል መንገዶች ባለስልጣን እና የበኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለየአዲግራት ዲስትሪክት ሠራተኞች እና የ
+3
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ቢሾፍቱ፣ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ ለትግራይ ክልል መንገዶች ባለስልጣን እና የበኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለየአዲግራት ዲስትሪክት ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በዋናነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት የነበረውን አለመረጋጋት ታሳቢ ያደረገ የሥነ ልቦና ዝግጅት እንዲኖር ማስቻል ነው፡፡ የሥራ ኃላፊዎቹና ሰራተኞቹ በሰሜኑ የሀገራችን አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተጎዱና ከአገልግሎት ውጪ የነበሩ መንገዶችና ድልድዮች ወደ ቀድሞ አገልግሎታቸው ለመመለስ በሚደረገው ጥረት አስፈላጊውን የስነልቦና ዝግጅት ማድረግ የሚገባቸው መሆኑንም በመድረኩ ተገልጿል፡፡ ቀጣይነት እንደሚኖረው በተገለጸው በዚህ የመጀመሪያ የስልጠና መድረክ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ኢ / ር ወንድሙ ሴታ ፣ የትግራይ ክልል የገጠር መንገድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር አርአያ ግርማይና የኢመአ አመራር አካላት ተገኝተዋል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው የአሳይታ-አፋምቦ-ጅቡቲ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው። የአሳይታ - አፋምቦ - ጅቡቲ ድንበር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 49 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና በመንግሥት በተመደበ 1,676,348,103.83 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሰባ ስድስት ሚሊዮን ሶስት መቶ አርባ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ሶስት ብር ከሰማንያ ሶስት ሳንቲም ) በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በሀገራዊ እና ቀጠናዊ ትስስሩ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት መልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ ሜዳማ ፣ ሸንተራራማ እና ተራራማ ሲሆን ፤ ከአዲስ አበባ በ663 ኪሎ ሜትር ርቀት አሳይታ ከተማ ላይ ጀምሮ ኢትዮ ጅቡቲ ድንበር ላይ ያበቃል፡፡ የአሳይታ-አፋምቦ-ጅቡቲ ድንበር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመካሄድ ላይ የሚገኘው አሰር ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር በተባለ ሀገር በቀል ድርጅት ነው። የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ደግሞ ይዲዲያ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በአማካሪነት በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በገጠር፡- 10 ሜትር ፣ በዞን፡- 21.5 ሜትር ፣ በወረዳ ደግሞ 19 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል ፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም በከፊል በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ የአፈር ጠረጋን ፣ ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የሰብቤዝ ፣የቤዝ ኮርስ ፣የአስፋልት፣የሶስት ድልድዮች ፣ የውሃ ማስተንፈሻ (ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች) ስራዎችን እንዲሁም የጎርፍ መከላከያ እና ልዩ ልዩ ግንባታዎችን (የመንገድ ምልክቶችን መትከል፣መንገድ ቀለም መቀባት) ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ አስካሁን 48 ኪሎ ሜትር (98%) የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ 47 ኪሎሜትር (97%) የሳብቤዝ ስራውም አልቋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የፕሮጀክቱ 20 ኪሎሜትር (41%) የቤዝ ኮርስ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ 95% የሶስት ድልድዮች ስራ እና 73% የውሃ ማስተንፈሻ (ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች) ስራዎች ከመጠናቀቃቸው ባሻገር የአስፋልት ግንባታ ስራም ተጀምሯል ። በዚህም መሰረት የፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም 40 ኪሎሜትር ወይም 82% በመቶ ተከናውኗል፡፡ ግንባታው በመጪው መስከረም ወር 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይታመናል፡፡ የስራ ተቋራጩ በቀሪ ጊዜያት ውስጥ 27% የውሃ ማፋሰሻ ስራዎችን ፣ ሙሉውን የአስፋልት ስራ እና ሌሎች ልዩ ልዩ ስራዎችን (የትራፊክ ምልክቶች መትከል እና መንገዱን ቀለም የመቀባት ስራ) ለማከናወን አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ባለፉት ጊዜያት እንደሀገር የተከሰተው ከፍተኛ የሲሚንቶ እጥረት ፤ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት የግንባታ ግብአቶችን ወደ ሳይት ማስገባት አለመቻል ፤ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ችግሮች መኖራቸው እና አንዳንድ የአካባቢው ግለሰቦች ከመንገድ ስራው ጋር ባልተያያዘ ምክንያት ተደጋጋሚ የስራ ማስቆም አዝማሚያዎች የነበሩ ቢሆንም እነዚህን ችግሮች በመቋቋም ግንባታው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በአካባቢው የአዋሽ ተፋሰስን ተከትሎ የአሳይታ እና አፋምቦ ወረዳዎች ለመስኖ ግብርና እጅግ አመቺ በመሆናቸው የሚመረቱትን የግብርና ውጤቶች በቀላሉ በጅቡቲ በኩል ወደ ውጪ ለመላክ የመንገዱ መገንባት አይነተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ማምረት ከሚቻለው ምርት በከፊል እንደ ስኳር ፣ ስንዴ ፣ ሰሊጥ ፣ ጥጥ ፣ ቴምር እና መሰል የግብርና ምርት ለማከናወን አመቺ ሲሆን ፣ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር ይህንኑ ታሳቢ ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በጅቡቲ በኩል የሚገነባው ቀጣይ የመንገድ ክፍል ሲጠናቀቅ ከዴቼቶ-ጋላፊ በተጨማሪ ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ጋር በየብስ የሚያገናኝ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። በአካባቢው የአዋሽ ተፋሰስን ተከትሎ የአፋምቦ ሀይቅ የሚገኝ ሲሆን ፤ ለቱሪስት መዳረሻነትም ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የመካነ-እየሱስ/እስቴ-ስማዳ 50 ነጥብ 5 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በፍፃሜ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። አዲስ አበባ፣ ግንቦት 04፣ 2015(ኢመአ):- በደቡብ ጎንደር ዞን የመካነ-እየሱስ/እስቴ-ስማዳ 50 ነጥብ 5 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በፍፃሜ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። አሁን ላይ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 86 በመቶው ተከናውኗል። ቀሪ ሥራዎቹን በሚቀጥሉት አምስት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው። ከጠቅላላው የመንገዱ ክፍል 47 ኪሎ ሜትሩን አስፋልት ማልበስ ተችሏል። በተጨማሪም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ፣ የሾልደር፣ የውኃ መፋሰሻ፣ የድልድይ እንዲሁም የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተሠሩ ነው፡፡ ግንባታውን ዓለም አቀፉ 'ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ' እያከናወነ ይገኛል። ለግንባታው የሚውለው 1,925,451, 264.41 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ አምስት ሚሊዮን አራት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ) ብር በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው። 'ፕሮሚናንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽንስ' ግንባታውን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ እየሠራ ይገኛል። አካባቢው ካለው በርካታ አገራዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው፡፡  በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል ላይ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የተፈጠረው ችግር በግንባታ ሥራው ላይ እክል ፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፥ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከወረዳ የመስተዳድር አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን መፍታት ተችሏል፡፡  ከዚህም ባለፈ የአካባቢው አስቸጋሪ የመልካ-ምድራዊ አቀማመጥ እንዲሁም የግንባታ ዕቃዎች የግብዓት ዕጥረት እና የዋጋ መናር በግንባታው ወቅት የገጠሙ ተግዳሮቶች ናቸው፡፡ የእስቴ-ስማዳ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ 657 ኪ.ሜ ርቀት እስቴ ከተማ ላይ ጀምሮ ወገዳ ከተማ ድረስ ይዘልቃል፡፡ ፕሮጀክቱ ዕውን ሲሆን በሥፍራው የሚገኙትን ትንንሽ መንደሮች ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማገናኘት ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን በማሳለጥም የተለያዩ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮችን ያጠናክራል፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ሽንብራ፣ ኑግ፣ ባቄላ፣ ጓያ፣ ድንች እና መሰል የግብርና ምርቶች ገበያ በፍጥነት እና በጥራት ማድረስ ያስችላል፡፡

ሞባይል ሚዛን ጣቢያ ከስሙ ለመረዳት እንደሚቻለው ተንቀሳቃሽ የቁጥጥር መተግበሪያ መሳሪያ ሲሆን አስካሁን ባለው ሁኔታ ያሉን ተንቀሳቃሽ ሚዛኖች ስድስት ብቻ በመሆናቸው በ ዋናው መ/ቤት በመዕከል ደረጃ በቻ የሚገኙ ሲሆን ለድጋፍ እና ቁጥጥር ስራ በቂየሆነ ተሸከርካሪ አንዲሁም የሰው ሀይል ባለመኖሩ በተገቢው ደረጃ ቁጥጥር ማድረግ አስቸጋሪ ቢሆንም ቋሚ ሚዛኖቸ የሌለባቸውን መንገዶቸ አየመረጥን ድንገተኛ ቁጥጥር ስራን እንዲሁም ከዲዛይን ዳይሬክቶሬት ለሚጠየቁ ለዲዛይን ግብአት የሚሆኑ መረጃዎችን በመሰብሰብ የድጋፍ ስራ አያከናወን የምንገኝ ሲሆን በጣም ለረጅም አመታት ሲያገለግሉ የቆዩ ነገር ግን ከከዚብዛት ተደጋጋሚ ብልሽት እየገጠማቸውን ተንቀሳቃስ ሚዛኖች ለመተካት የተጨማሪ (20) ሚዛኖቸ ግዚ ጥያቄ ለማቅረገብ ቅድም ዝግጅት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ 8. የተሸከርካሪ ክብደት ቁጥጥርን ከማዘመን አንፃር እስካሁን የተሰሩ ስራዎች እና በቀጣይ ሊተገበሩ የታሰቡ ተግባራት ላለፉት ከ30 አመታት በላይ ስንጠቀምባቸው የነበሩ የመመዘኛ ማሽኖች ሙሉ በሙሉ በማንዋል ወይም በቀጥታ የእጅ ንክኪ ይተገበሩ የነበሩ ናቸው፡፡ ከአምስት አመታት በፊት ተቋማችን ይህን አሠራራ ለመቀየር በነበረው ፍላጎት እና ይህንንም የጃፓን መንግስት (Jica ) ተገንዝቦ ድጋፍ ለማድረግ የጋራ መግባባት ላይ በተደረሰው ስመምምነት መሠረት አዲስ ዲጅታላይዝድ ማሽን ገጥመውልን በነባሩ አዋጅ መሠረት በኮምፒውተር የታገዘና ከእጅ ንኪኪ ነፃ የሆነ ስራ መተግበር ተችሏል፡፡ ነገር ግን ከአዲሱ ደንብ ጋር በተያያዘ በእርዳታ የተገኙት መመዘኛዎች ወጥ የሆኑ እና የጥንድ እና ባለሶስት አክስል ለየብቻ መለካት የማይችሉ ሲሆን ፣ ይህም በአዲሱ ደንብ መሰረት ወደ ስራ ለመግባት አስቸጋሪ ቢሆንም ፤ ይህን ችግር ከ(jica ) ጋር በመነጋገር መመዘኛ መሳሪያዎች ላይ እንዲደረጉ ማሻሻያዎችን ጠይቀናል፡፡ እንዲሁም በአሁኑ ወቅት በመመዘኛ ጣያቢያዎች ላይ በሚታየው የኤሌትሪክ ሀይል መቆራረጥ እና ከፍተኛ ሀይል መጨመር ምክንያት የሚደርሰውን የሀይል እጥረት እና የማሽኖችን ብልሽት ለመቅረፍ የባለ ብዙ ሀይል አማራጭ ሲሰተም ለመዘርጋት የፓወር ሀውስ ግንባታ እና የጀነሬተር ሶላር ፓኔል የባትሪ እና ኢንቨርተር ግዥ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ የሚዛን ጣያዎችን የአሰራር ስርአት የተቀናጀ አሰራር እና የቁጥጥር ስርአቱን ለማዘመን የፕሮጀክት ቀረጻ ስራ እያካሄድን እንገኛለን፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የመንገድ ግንባታ ለዘላቂ ልማት የኢኮኖሚ ልማትና የማህበራዊ ኑሮ እድገት ለማምጣት በሚደረግ ሀገራዊ ጥረት የመንገድ ዘርፍ የሚገኝበት ደረጃ እና የተሰጠው ትኩረት ወሳኝ ድርሻ አለው፡፡ ለዚህም ነው መንግስት በየበጀት ዓመቱ ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ በመመደብ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የተለያዩ የመንገድ ግንባታ ሥራዎችን በማከናወን ላይ የሚገኘው፡፡ ይኸው ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ የሚፈስበት የመንገድ ሃብት የሚጠበቅበትን አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል፡፡ በዚህም ረገድ የተሸከርካሪዎች የክብደት መጠን ቁጥጥር በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ አንዱ ማሳያ ነው፡፡ 1. የሚዛን ጣቢያዎች የቋቋሙበት ዓላማ፡- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአዋጅ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ በመንግስት እና በህዝብ የተጣለበትን ሀላፊነት ለመወጣት በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች ለህዝብ እና ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ማህበራዊ ጠቀሜታ የሚሰጡ መንገዶችን የመገንባት የማስተዳደር እና ዲዛይን ለተደረጉበት የአገልግሎት ጊዜ ሳይበላሹ አንዲያገለግሉ የተለያዩ የቁጥጥር ስራዎቸን እያከናወነ ይገኛል:: ከነዚህ የቁጥጥር መንገዶቸ አንዱ በህግ ከተፈቀደላቸው የመጫን አቅም በላይ ከፍተኛ ጭነት በሚጭኑ የጭነት ተሸከርካሪዎች ምክንያት በመንገዶች እና በድልድዮች ላይ የሚደርስውን ከፍትኛ ጉዳት ለመቆጣጠር እና ለመንገድ ጥገና የሚወጡ ከፍተኛ ወጪዎችን ለመቀነስ ሲባል በአጠቃላይ በሀገሪቱ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የክብደት እና መጠን መቆጣጠሪያ ሚዛን ጣቢያዎቸን በመትከል የቁጥጥር ስራዎቸን እያከናወነ ይገኛል:: የተሽከርካሪዎችን ክብደት የመቆጣጠር ዋና አላማ በመንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸዉ የአክስል ክብደት መጠን በላይ ጭነት ጭነዉ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የመንገድ አዉታሮች ላይ ጉዳት እንዳያደረስ የመከላከል እንዲሁም መንገዶች እና ድልድዮች ሳይበላሹ ለረዥም ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ማድረግ ነዉ፡፡ 2. በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የሚዛን ጣቢያዎች እና መገኛ ቦታቸው፡- እስካሁንም 14 ሚዛን ጣቢያዎቸን በተለያዩ ቦታዎቸ ተቋቁመው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን ፣ መገኛ አካባቢያቸውም፡- ሞጆ ፣ ሆሎታ ፣ ሱሉልታ ፣ ሠንዳፋ ፣ ዲማ (ሰበታ) ፣ ጂማ ፣ ሻሸመኔ አዋሽ ፣ ሠመራ ፣ደንገጎ ፣ ኮምቦልቻ ፣ ጢቅ(ደጅን )፣ ወረታ ፣ ዮሓ (መቀሌ ) ናቸው ። 3. የተሸከርካሪዎችን የክብደት መጠን ለመወሰንና ለመቆጣጠር በወጣን የሚኒስትሮች ምክርቤት ደንብ ቁጥር 491/2022 ውስጥ ዋና ዋና የድንጋጌ ነጥቦችን የተፈጻሚነት ወሰን - በማንኛዉም የኢትዮጵያ መንገዶች የሚጠቀሙ ጠቅላላ ክብደታቸዉ ከ3,500 ኪሎ ግራም በላይ በሆኑ ተሸከርካሪዎች ፣ የተጣመሩ ተሸከርካሪዎች እና ተሳቢዎች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በእሳት አደጋ ተሸከርካሪዎች ፣ የተፈጥሮ አደጋ መከላከል ስራ ላይ በተሰማሩ ተሸከርካሪዎች ፣ በድንገተኛ አደጋ የወደሙ መሰረተ-ልማቶችን በመገንባት ሥራ ላይ በተሰማሩ ተሸከርካሪዎች ፣ ኢትዮጵያ በተፈራረመቻቸዉ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች መነሻነት የሚጓዙ ተሸከርካሪዎች ፣ የግንባታ ስራ በሚከናወንበት አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የግንባታ ተሸከርካሪዎች እና በልዩ ወታደራዊ ተሸከርካሪዎች ላይ የዚህ መመሪያ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ አይሆንም፡፡ በደንቡ የተወሰነው ከፍተኛዉ የተሸከርካሪ ክብደት 56ቶን (560 ኩንታል) ሲሆን ፣ ይህም ድልድዮችን ከጉዳት ለመጠበቅ ሲባል የተቀመተጠ ከፍተኛ ገደብ ነው፡፡ በእያንዳንዱ የትርፍ ጭነት የሚደርሰውን የመንገድ ሀብት ጉዳት መጠን ተመጣጣኝ የቅጣት ተመን በዝርዝር በደንቡ ላይ መቀመጡ ፣ እንዲሁም በትርፍ ጭነት ምክንያት የሚደርሰውን ጉዳት ለመጠገን የሚያስፈልገውን ወጪ ከቅጣቱ የተገኘውን ገንዘብ መልሶ ለጥገና ለማዋል እንዲመች የቅጣት ገንዘቡ በሮድ ፈንድ አማካኝነት ወደ ኢመአ እንዲገባ በማድረግ መልሶ ለመንገድ ጥገና አገልግሎት እንዲውል ማድረግ ማስቻሉ፡፡ የትርፍ ጭነት ቅጣት ለሶስት የተከፈለ ሲሆን ፣ በዚሁም መሰረት አሽከርካሪው የጭነት ባለቤቱ እና የተሸከርካሪው ባለንበረት እንደ ቅጣቱ አይነት እና መጠን እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡ 4. ለእያንዳንዱ አክስል የሚፈቀድ የክብደት መጠን I. የነጠላ አክስል (Axle) ሁለት ወይም ሶስት ጎማዎች የተገጠሙለት ተሽከርካሪ የፊት እና የኋላ የአክስል (Axle) ክፍሎች ጠቅላላ የክብደት መጠን የሚከተለዉ ነዉ፡- ሀ) የፊት አክስል (የመሪ አክስል) Steering Axle የማይፈቀድ የክብደት መጠን ከ7.7 ቶን (77 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ፤ ወይም (9 ለ1) ለ) ከመሪዉ አክስል (Steering Axle) ዉጪ ሆኖ ነጠላ ጎማ የተገጠመለት ተሸከርካሪ ከሆነ ጠቅላላ ክብደቱ ከ8 ቶን (80 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡ (9 ለ2) ሐ) የ ኃላዉ የአክስል ክፍል አራት ጎማዎች የተገጠሙለት ከሆነ የአክስል ክብደቱ ከ10 ቶን (100 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡ (9 ሐ) II. የተሸከርካሪዉ የአክስል ክፍል ባለ ሁለት (Tandem Axle Unit) ወይም ባለሶስት (Tri-dem axle) ሲሆን ፣ ለተሸከርካሪዉ የማይፈቀድ የአክስል (Axle) የክብደት መጠን እንደሚከተለዉ ነዉ፡- ሀ) የጥንድ አክስል (Steering Tandem Axle) ክብደት ሳይጨምር ጠቅላላ የኋላ የአክስል ክብደቱ በአንድ ላይ ተደምሮ ከ18 ቶን (180 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡ ለ) ሶስት አክስሎች (Tri-dem axle) ከሆነ የሚፈቀደዉ ከፍተኛ ክብደት መጠን ከ24 ቶን (240 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡ 5. የተደነገገውን ህግ ተላልፎ በሚገኝ ተሽከርካሪ ላይ የሚደረግ የቅጣት ሁኔታ በአዲሱ ደንብ መሰረት የቅጣት መጠን የመንገዶችን የጉዳት ልክ የሚመጥን እና ለመንገዶች ጥገና የሚውለውን ወጪ ያማከለ ሲሆን ፣ ለነጠላ ጥንድ ወይም ለባለሶስት አክስል እርስ በእርስ ሳደማመሩ በዝርዝር የተቀመጠው አነስተኛው ቅጣት መጠን 603 ብር ሲሆን ፣ ከፍኛው ደግሞ 70520 ብር ነው፡፡ 6. አንድ ተሽከርካሪ ከወደብ ወይም ከጫነበት ቦታ ሲነሳ የጫነው የክብደት መጠን ተመዝኖ እንዲንቀሳቀስ ለማስቻል እየተከናወነ ያለ ቅድመ ሁኔታን በተመለከተ እስካሁን ባለው ሁኔታ ጭነቶች ከመነሻቸው መቆጣጠር አስፈላጊ ቢሆንም ሚዛን ጣቢያን ለመትከል ከፍተኛ ገንዘብ የሚያስፈልግ በመሆኑ በየአያንዳንዱ የሀገሪቱ መግቢያ እና መውጫዎቸ እንዲሁም የጭነት መነሻ ስፍራዎች ላይ የጭነት መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች መትከል አቅም ስለማይፈቅድ ተግባራዊ ሳይደረግ ቆይቷል፡፡ ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት በአሁኑ ሰአት ያሉት ሚዛኖች በዋና አገናኝ መንገዶች እና ከፍተኛ ገቢና ወጪ ያለባቸውን መንገዶች ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተተከሉ ሲሆን ፣ ለወደፊቱ ለማቋቋም የቦታ መረጣና ተገቢው የቅድመ ሁኔታ ጥናት እንዲሁም የፕሮጀክት ድጋፍ ለመፈለግ አስፈላጊው ሰነድ በመዘጋጀት ላይ ነው፡፡ 7. ተንቀሳቃሽ (ሞባይል) የሚዛን ጣቢያዎችን በተመለከተ

የቡልቡላ - አላጌ - ባራ - ሚቶ መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ነው ። 39 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው የቡልቡላ - አላጌ - ባራ - ሚቶ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ  77 በመቶ ስራው ተጠናቋል። ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ኪቢሽ የተባለ ሀገር  በቀል የስራ ተቋራጭ ሲሆን ፣ United Consulting Engineers plc ( UNICON ) ደግሞ የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን በማካሄድ ላይ ይገኛል። ለፕሮጀክቱ የተመደበው 878,514,732.42 (ስምንት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን አምስት መቶ አስራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት ብር ከአርባ ሁለት ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። ከቡልቡላ ዋና ከተማ 2 . 5 ኪ . ሜ ርቀት ላይ መነሻውን ያደረገው ይህ የመንገድ ፕሮጀክት የኦሮምያን ክልል ከደቡብ ክልል ጋር ያስተሳስራል።  አካባቢው እንደ በቆሎ ፣ ስንዴ ፣ ቦሎቄና በርበሬ  ያሉ የተለያዩ የግብርና ምርቶች የሚመረቱበት መሆኑ የመንገዱን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ጉልህ ያደርገዋል። በአሁኑ ወቅት የመንገዱ 31 ኪ . ሜ ወይም 81 በመቶ የሰብ ቤዝ ስራው የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ 33 ኪ . ሜ ወይም 85 በመቶ የሰብ ግሬድ ስራውም ተከናውኗል። ከዚህም ባሻገር የስላብና ፓይፕ ካልቨርት ስራዎችም በመጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ ። በቅርቡም የአስፋልት ንጣፍ ስራም እንደሚጀመር ታውቋል ። አጠቃላይ የመንገዱ አፈፃፀም በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣  በተገቢው ጥራትና ጊዜ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስፈላጊውን ቁጥጥር እና ድጋፍ ያደርጋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የገበታ ለሀገር ሐላላ ኬላ ሪዞርት

የመንገድ ፈንድ ለመንገዶች ጥገና አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። አዲስ አበባ፣ ሚዚያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የመንገድ ፈንድ ለመንገዶች ጥገና በጀት ምንጭ በመሆን አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ መንገዶች ተገቢውን ጥገና በወቅቱ እንዲያገኙ እና ለመንገድና ትራፊክ ደህንነት ሥራዎች ማስፈፀሚያ በቂና የማያቋርጥ የገንዘብ ፈሰስ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ገቢን ለማሰበሰብና ለማስተዳደር የመንገድ ፈንድ በአዋጅ ቁጥር 66/89 ተቋቋመ። የመንገድ ፈንድ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በአዋጁ ከተፈቀዱ የገቢ ምንጮች ማለትም ከነዳጅ (ታሪፍ)፣ ከቅባትና ዘይት (ታሪፍ)፣ ከመንገድ ጠቀሜታና በክብደት ላይ ከተመሰረተ ዓመታዊ የፈቃድ ማደሻ ክፍያ ገቢ በማሰባሰብና ለፌዴራል፣ ለክልል እና ለተለያዩ ከተማ መንገድ ኤጀንሲዎች በመመደብ ከ550,000 ኪ.ሜ (ከአምስት መቶ ሃምሳ ሺህ ኪሎ ሜትር) በላይ መንገዶች የጥገና ሥራ እንዲከናወን የበጀት ድጋፍ በማድረግ ለመንገድ ዘርፉ የማይናቅ አስተዋፅኦ ስያበረክት ቆይቷል፡፡ በ2015 በጀት ዓመትም ለመንገድ ጥገና የሚውል ብር 510,950,000.00 (አምስት መቶ አስር ሚሊዮን፣ ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) የመንገድ ፈንድ ገቢ ተሰበስቧል፡፡ ገቢው የተሰበሰበው በነዳጅ ላይ ከተጣለ ታሪፍ ብር 304,660,000፣ ከተሸከርካሪ ዘይትና ቅባት ብር 2,590,000.00፣ ከመንገድ ጠቀሜታ ክፍያ ብር 1,670,000.00 እና በክብደት ላይ የተመሰረተ የተሸከርካሪ ፈቃድ ማደሻ ብር 207,740,000.00 ነው፡፡ የተሰበሰበውን ገቢ ለመንገድ ጥገና ከማዋል አንፃርም በዘጠኝ ወራት ጊዜ ውስጥ ለኢመአ የመንገድ ጥገና እና የአማካሪ ድርጅቶች ክፍያ ብር 1,637,020,000.00 ፣ለክልል ገጠር መንገዶች 317,530,000.00 ፣ ለከተማ መንገድ ኤጀንሲዎች 102,160,000.00፣ ለድጋፍ ሰጪ ለክልልና ከተሞች ብር 16,960,000 እንዲሁም ለመልሶ ግንባታ ብር 109,510,000 በድምሩ ብር 2,727.53 ክፊያ ተፈጽሟል፡፡ በመስክ ምልከታ Value for money ከማረጋገጥ አንጻርም ከመንገድ ኤጀንሲዎች በሚቀርቡ የአፈጻጸም ሪፖርቶችን መገምገምና ግብረመልስ መስጠት፣ የመስክ ክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን መስራትና የቴክኒካል ኦዲት የማድረግ ሥራ ተሰርቷል፡፡ በዘጠኝ ወራት የክትትልና ግምገማ ከተሰራባቸው የመንገድ ኤጀንሲዎች መካከል፣ 1. የባህር ዳር ከተማ መንገዶች ባለስልጣን 2. የሲዳማ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 3. ቤንሻንጉል ክልል መንገድና ትራንስፖርት ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 4. በአሶሳ ማዘጋጃ ቤት 5. በደቡብ መንገዶች ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 6. በኦሮሚያ መንገዶችና ሎጂስቲክስ ቢሮ ም/ሸዋ ዲስትሪክት ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች 7. በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ስር በሚገኙ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቶች ይገኙበታል፡፡ የመስክ ምልከታ ሥራ የተሰሩ ሲሆን በተደረገዉ ምልከታም ፡- 1. መሬት ላይ ያለዉ ሥራ እና እቅዳቸዉ እንዲናበብ የምክር አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡ 2. በክፍያ ሰርተፊኬት ክፍያ የተጠየቀባቸዉ ነገር ግን ያልተከናወኑ ሥራዎች ከክፍያ ሰረተፊኬት እንዲቀነሱ ተደርጓል፡፡ 3. ክፍያዎች ሲጠየቅ ስቴሽን እና ዳይሜንሽን ሳይቱ ላይ ባለው መረጃ መሰረት ባለመቅረቡ እንዲስተካከል ተጠይቋል፡፡ 4. ለሁሉም የኳሪ ሳይቶች ላብራቶሪ ፍተሻ እንዲደረግ አቅጣጫ ተሰቷል፡፡ በሳይት ምልከታ ወቅት የተስተዋሉ የመንገድ ኤጀንሲዎች የአቅም ውስንነት በስልጠና የማብቃት ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ በመሆኑም የመንገድ ፈንድ በጀት ለታለመለት ዓላማ መዋል አለመዋሉን በመስክ ምልከታ ወቅት የመዳሰስ ሥራ ተሰርቷል፡፡ በመጨረሻም የመንገድ ጠቀሜታ ክፊያም በጦርነት ምክንያት በሑመራ እና በሱዳን ድንበር ተሸከርካሪ ስለማይገባ ሽያጭ ባለመኖሩ በበጀት ዓመቱ ገቢ አሰባሰብ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ነበረው፡፡ ከሃምሌ/2015 ጀምሮ ነዳጅ ላይ ከተጣለ ታሪፍ ይሰበሰብ የነበረውም ገቢ በመቆሙ ገቢ አሰባሰቡ ለካይ ከፍተኛ ጫፋ ያሳደረ ቢሆንም ችግሩ ከሚያዝያ/2015 ጀምሮ ወደ ነበረበት እንዲመለስ በገንዘብ ሚኒስቴር ተወስኗዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የአምቦ ወሊሶ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው እና 63 ኪሎሜትር ርዝማኔ የሚሸፍነው የአምቦ ወሊሶ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነዉ፡፡ የመንገድ ግንባታዉ ከዚህም ቀደም በነበረው የሥራ ተቋራጭ አቅም ውስንነት ፣ በወሰን ማስከበር ችግር በተለይም በአፈር እና የድንጋይ ማውጫ ቦታዎች ተደጋጋሚ የስራ ማስቆም እንቅስቃሴ የነበረ በመሆኑ እንዲሁም በሲሚንቶ እጥረት እና በሰላም እና ፀጥታ ችግሮች ምክንያት በተያዘለት ጊዜ እንዳይጠናቀቅ እክል ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በኢመአ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካለት ጋር በተደረገው ጥረት መሻሻል በመታየቱ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል፡፡ በእስከአሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ የተሰሩ ስራዎች 315,754.41 ሜትር ኪዩብ የአፈር ቆረጣ ስራ ፣ 212,591.31 ሜትር ኪዩብ የአፈር ሙሌት ስራ ፣ 25.62 ኪሎ ሜትር የሰብ ቤዝ ስራዎች ፣ 17.63 ኪሎ ሜትር የቤዝ ኮርስ ስራ ፣ 15 ፓይፕ ከልቨርት ፣ 4 ሰላብ ከልቨርት እና 5 የድልድይ ግንባታ ስራዎች ተከናዉነዋል፡፡ በተጨማሪም የአስፓልት ማንጣፍ ስራም ተጀምሯል፡፡ የመንገድ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ሲሆን ፣ የማማከር እና ቁጥጥር ስራውን ደግሞ ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላ.የተ.የግል ማህበር ከ ጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ጋር በጣምራ እያከወኑት ይገኛሉ፡፡ ግንባታውን ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው ገንዘብ 1,264,907,396.11 ብር ሲሆን ፣ የሚሸፈነዉም በኢትዮጵያ መንግስት ነዉ፡፡ ቀደም ሲል የነበረዉ የመንገዱ ሆኔታ በጥርጊያ ደረጃ ላይ የነበር ሲሆን ፣ ለትራንስፕረት በጣም አስቸጋሪ እና ጠባብ መንገድ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት የእግረኛ መንገድን ጨምሮ በገጠር 7 ሜትር እና በከተማ ደግሞ 21 ሜትር ተጨማሪ የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በ125 ኪ.ሜ ርቀት ከምትገኘዉ አምቦ ከተማ መነሻዉን በማድረግ ወሊሶ ከተማ ላይ ያበቃል፡፡ ይህ ፕሮጀክት ምዕራብ ሸዋ(አምቦ) እና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ(ወሊሶ) ከተሞችን የሚያገናኘ ሲሆን ፣ በዉስጡም፡- ጭቱ ወረዳን ጨምሮ ዳርያን ፣አልቱፋ ሰንኮሌ ቀበሌዎችን በቅርበት ያስተሳስራል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል እና ለመደገፍ እንዲቻል በተቋሙ በቅርቡ ከተከፈቱት የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማጅመንት ፅ/ቤቶች አንዱ የሆነዉ የአምቦ እና አካባቢዉ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ፅ/ቤት የዚህን መንገድ ግንባታን ጨምሮ በስሩ የሚገኙትን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች በጥራትና በተያዘላቸዉ የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ለማስቻል አስፈላጊውን ክትትልል እና ድጋፍ ያደርጋል፡፡ የዚህ መንገድ መገንባት የህብረተሰቡን የትራንስፖርት ችግር ከመቅረፍ ባሻገር በአካባቢዉ የሚመረቱ እንደ ጤፍ ፣ እንሰት ፣ ገብስ እና በቆሎ የመሳሰሉ የአዝዕርት ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገቢያ በማድረስ አምራችና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በተጨማሪም ትልቁ የቱሪዝም መዳረሻ ‘’የወንጪ ሃይቅ’’ በፕሮጀክቱ አጋማሽ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ የመንገዱ መገንባት ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ትልቅ አበርክቶት ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ዒድ ሙባረክ! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 444ኛው ዓመተ-ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆን
ዒድ ሙባረክ! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 444ኛው ዓመተ-ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ይመኛል!! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et