ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 373 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 753,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 530

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 373 名订阅者。

根据 20 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 129,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.47%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 143 次浏览,首日通常累积 2 037 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 373
订阅者
+824 小时
+697
+12930
帖子存档
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሀኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሠላም በጤና አደረሳችሁ:: በዓሉን ስናከብር እራሣችንንና የምንወዳቸውን ሠዎች ከኮሮና
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሀኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሠላም በጤና አደረሳችሁ:: በዓሉን ስናከብር እራሣችንንና የምንወዳቸውን ሠዎች ከኮሮና /ኮፊድ 19/ በመጠበቅ እና የጤና ባለሙያዎች የሚሉትን በማድረግ እንዲሁም አቅመ ደካሞችን በመርዳት እንዲሆን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ይመኛል:: #በዓሉን_በቤታችን

በግንባታው ዘረፍ በአማካሪ ድርጅትነት የተሰማሩ ተቋማት /አማካሪ መሃንዲሶች/ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያግዝ 2 ሚሊየን 358ሺብር ድጋፍ አበረከቱ ፡፡ በዛሬው እለት በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የአማካሪ ድርጅቶቹ የድጋፍ አስተባባሪ ኢንጂነር ተስፍዬ ወርቅነህ ድርጅቶቹን በመወከል የብር ስጦታውን ለተቋቋመው የብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባል እና ለኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ አስረክበዋል። ድርጅቶቹ ወቅታዊው ወረርሽኝ በህይወት፣ በጤና፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ ይበልጥ ሀገራዊ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል ከመንግስት ጎን በመቆም በራሳችን ተነሳሽነት ድጋፍ በማድረጋችን ደስተኞች ነን ብለዋል ። በቀጣይም ይህን መሰሉ ድጋፍ በገንዘብም በሞያዊ አበርክቶትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በተያያዘ ዜና በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩ ሶስት ሀገር በቀል ድርጅቶች የ3ሚሊየን አንድ መቶ ሺ ብር ድጋፍ አድርገዋል። የገንዘብ ድጋፋን ያበረከቱት ማክሮ ሀገር በቀል የግንባታ ተቋራጭ 2 ሚሊየን ብር አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን አንድ ሚሊየን ብሩን አበርክተዋል። ባለሃብቶቹ ለወገኖቻቸው ያበረከቱትን የገንዘብ ድጋፍ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም የብሔራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተረክበዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኘ የተከሰተውን አስከፊ ወረርሽኝ ለመከላከል በሚደረገው ሂደት ባለሃብቶቹ እና አማካሪ ድርጅቶቹ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ እንዲሁም ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን በመወጣት ለወገኖቻቸው ላሳዩት አለኝታነት ያላቻውን ምስጋና እና አድናቆት በመግለጽ በቀጣይም አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል:: በቅርቡ በተከናወነ የድጋፍ ማሰባሰብ መሰል መርሃ ግብር በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩ የደረጃ አንድ ሀገር በቀል ተቋራጮች 15ነጥብ 3ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ በመንገድ ስራ ተቋራጭነት የተሰማሩ 12 ባለሃብቶች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያግዝ 15 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር አበረከቱ ፡፡ በዛሬው እለት በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው በዚሁ መርሃ ግብር ላይ አስራ ሁለት አገር በቀል የመንገድ ግንባታ ስራ ተቋራጮች ናቸው የ15.3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ያደረጉት ፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይም የሰንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ኮንስትራክሽን ባለቤት የክብር ዶ/ር ሳሙኤል ታፈሰ ተቋራጮችን በመወከል የብር ስጦታውን ለተቋቋመው የብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባላት አስረክበዋል፡፡ በመድረኩ ላይም እኛ በመንገድ ግንባታ ዘርፍ እየተሳተፍን ያለን የደረጃ አንድ ተቋራጮች ወቅታዊው ወረርሽኝ በህይወት፣ በጤና፣በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ ይበልጥ ሀገራዊ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል ከመንግስት ጎን በመቆም በራሳችን ተነሳሽነት ድጋፍ በማድረጋችን ደስተኞች ነን ብለዋል ፡፡ በቀጣይም ይህን መሰሉ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡ ባለሃብቶቹ ለወጎኖቻቸው ያበረከቱትን የገንዘብ ድጋፍ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም የብሔራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ እና የንግድ እና ኢንደስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋናው አርጋው ተረክበዋል ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኘ የተከሰተውን አስከፊ ወረርሽኝ ለመከላከል በሚደረገው ሂደት ባለሃብቶቹ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ የብሔራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ እና የንግድ እና ኢንደስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋናው አርጋው በበኩላቸው ባለሃብቶቹ ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን በመወጣት ለወገኖቻቸው ላሳዩት አለኝታነት ያላቻውን ምስጋና እና አድናቆት ገልጸዋል:: የገንዘብ ድጋፉን ያበረከቱት ድርጅቶች እና የገንዘብ መጠን ተ.ቁ የተቋራጭ ስም የገንዘብ መጠን 1 ሰንሻይን ኮንስትራክሽን 2 ሚሊዮን ብር 2 አለማየሁ ከተማ 2 ሚሊዮን ብር 3 ኤን ኬ ኤች ኮንስትራክሽን 2 ሚሊዮን ብር 4 ተክለብርሃን አምባዪ ኮንስትራክሽን 2 ሚሊዮን ብር 5 ዮቴክ ኮንስትራክሽን 2 ሚሊዮን ብር 6 ራማ ኮንስትራክሽን 1 ሚሊዮን ብር 7 ሜልኮን ኮንስትራክሽን 1 ሚሊዮን ብር 8 እንይ ኮንስትራክሽ 1 ሚሊዮን ብር 9 ማርካን ኮንስትራክሽን 1 ሚሊዮን ብር 10 ፓወርኮን ኮንስትራክሽን 500 ሺብር 11 ዮንአብ ኮንስትራክሽን 500 ሺ ብር 12 ራባ እና ሶን ኃ /የተ/ የግ/ማ 300 ሺብር ድምር 15 ሚሊዮን 300 ሺ ብር

በቻይና ከተከሰተው የኮሮና ወረርሽን የተረፉ ሰዎች የሰጧቸው ዋና ዋና ጠቃሚ ምክሮች:- #1. ሁለት አይነት ጫማ ይኑርዎት። አንዱ ከቤት ውጪ የሚጠቀሙበት ሲሆን ሌላኛው ቤት ውስጥ የሚጠቀሙበት ይሆናል። ከቤት ውጪ የሚጠቀሙበትን በፍጹም ወደ ቤት ውስጥ አያስገቡ። ቤት ውስጥ የሚጠቀሙበትን በፍጹም ወደ ውጪ አያውጡ። #2. አንድ የተለየ ጠረጴዛ ይኑርዎት። ከውጪ የሚገዟቸውን እቃዎች ለማኖር የሚያገለግል አንድ የተለየ ጠረጴዛ ይኑርዎት። ከውጪ የሚገዟቸውን እቃዎች በሙሉ ለምሳሌ እንደ መድሐኒት: መጠጦች: አትክልቶች እና ሌሎችንም ሳይነኩ ለ24 ሰዓት በጠረጴዛው እንዲቆዩ ያድርጉ። #3. በተቻለ መጠን የገንዘብ ኖቶችንም ሆነ ሳንቲሞችን አይስጡ: አይቀበሉ። የገንዘብ ኖቶችንም ሆነ ሳንቲሞችን ወደ ወደ ቤት የሚያመጡ ከሆነ ለዚህ ጉዳይ ለይተው ባስቀመጡት ጠረጴዛ ላይ ለ24 ሰዓት አቆይተው ይጠቀሙ። #4. ሁሉንም አይነት አትክልቶች ማለትም ቀይ ሽንኩርት: ነጭ ሽንኩርት: ድንች እና ሌሎችንም በፈላ ውሃ ሙልጭ አድርገው ይጠቡ። በፈላ ውሃ ሊታጠቡ የማይችሉ አትክልቶችን አይግዙ። #5. ከቤት ከወጡ በተቻለ መጠን የእጅ ስልክዎን ይዘው አይሂዱ። ይዘው ከወጡ ደግሞ ወደ ቤት ሲመልሱ በአልኮል ያጽዱ። #6. ከቤት ከወጡ በተቻለ መጠን የቤት ቁልፎችን ይዘው አይውጡ። ይዘው ከወጡ ደግሞ ወደ ቤት ሲመልሱ በአልኮል ያጽዱ። #7. ከቤት ወጥተው ሲመልሱ እጅዎንና ፊትዎን በሳሙና ይታጠቡ። ቤት እንደተመለሱ የለበሱትን ልብስ አውልቀው እንዲታጠብ ያድርጉ። #8. ሴት እህቶቻችን ከቤት ስትወጡ ጸጉራችሁ በአግባቡ መጠቅለሉን አረጋግጡ:: ጸጉራችሁን በእጃችሁ አትነካኩ:: ፊታችሁን ጸጉር በነካ እጃችሁ አትንኩ። #9. አትክልት ለመግዛት ሲሄዱ የእጅ ጓንት ያድርጉ። ወይም አትክልቶችን ሲያነሱ የፕላስቲክ ከረጢቶችን በሁለቱም እጅዎት ማጥለቅዎትን እርግጠኛ ይሁኑ። ወደ ቤት ሲመልሱ የእጅ ጓንትዎን ማጠብዎን አይዘንጉ። በፕላስቲክ ከረጢቶች ተጠቅመው ከሆነ ወደ ቤት ሲመልሱ ወይም ወዲያውን ከተጠቀሙ በኋላ ያስወግዱ። #10. ሁልጊዜ ከቤት ከመውጣትዎ በፊት ራስዎን እና የሚያመጧቸውን ነገሮች ደህንነት እንዴት መጠበቅ እንደሚችሉ ያቅዱና በቂ ዝግጅት ያድርጉ። #11. በጣም የግድ ካልሆነ በስተቀር ምግብ ወይም መድሐኒት ለመግዛት ባይሰለፉ ይመረጣል። መሰለፉ ደግሞ የግድ ከሆነ እስከ ሁለት ሜትር ርቀትዎን ይጠብቁ። #12. ከውሾች እና ድመቶች ጋር ያለዎትን ንክኪ ያስወግዱ። #13. በተቻለ መጠን አረጋውያን ወደ ውጪ ባይወጡ ይመክራል። ቤት ውስጥ ያሉ ወይም በአካባቢው ያሉ ሰዎች ለአረጋውያን የሚፈልጉትን ነገር ገዝተው ቢያመጡላቸው ይመክራል። #14. ሁልጊዜ ከቤትዎ ከመውጣትዎ በፊት ከላይ የተጠቀሱትን መልዕክቶች በመመልከት አቅደው ተግባራዊ ያድርጉ። ኮሮና ለመከላከል ከላይ የተባሉትን መተግበር! Keep healthy and safe,

ይህ በተዋቂው የምርምርና የትምህርት ተቋም ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ (Johns Hopkins University) ተፅፎ የተሰራጨውና በደረጀ ድረስ በተባለ ሰው የተተረጎመው የኮሮናን ባህሪና መከላከያ ጠቃሚ ሆኖ ስላገኘሁት SHARE ብታደርጉት ለብዙ ሰው ይጠቅማል፡፡ ⚡️ቫይረሱ ህይወት ያለው ፍጡር ሳይሆን እራሱን በሚከላከልበት ስስ ስብ የተሸፈነ የፕሮቲን ሞሎኪዩል ( ዲኤን.ኤ) ሲሆን ወደ አይን፣ አፍንጫ እና አፍ በሚገባ ጊዜ በነርሱ ውስጥ በሚገኝ ክፍተት ውስጥ በመግባትና የራሱን ተፈጥሯዊ ማንነት በመቀየር ወደ ብዙ እና አጥቂ ተውሳክነት ይቀየራል፡፡ ⚡️ቫይረሱ ህይወት ያለው ፍጡር ሳይሆን የፕሮቲን ሞሎኪዩል ( ዲኤን.ኤ) እስከሆነ ድረስ በራሱ ይበሰብሳል እንጂ አይሞትም፡፡ የሚፈራርስበት ጊዜም በአየሩ የሙቀት መጠን፣ የአየሩ እርጥበት መጠን እና ቫይረሱ በተገኘበት ቁስ ይወሰናል፡፡ ⚡️ቫይረሱ በጣም ስስ/ ተሰባሪ ሲሆን ከመሰበር የሚከላከው ነገር ቢኖር በዙሪያው የከበበው በጣም ስስ ስብ ነው፡፡ ለዚህም ነው ማንኛውም ሳሙና ወይም የጽዳት መጠበቂያ ቫይረሱን ለመከላከል ፍቱን መፈትሄ የሆነው፡፡ ምክኒያቱም የሳሙናው አረፋ የቫይረሱን ስብ መሰል መሸፈኛ ይሰባብረዋል፡፡ ለዚህም ነው እጃችንን ከ20 ሰከንድ ለማያንስ ጊዜ በደንብ የምናሸው/ ምንፈትገው፡፡ የስብ መሸፈኛውን በሳሙና ስናሟሟው የቫይረሱ የፕሮቲን ሞሎኪውሉል( ዲኤን.ኤ) እራሱ ይበታተን እና ይሰባበራል፡፡ ⚡️ሙቀት ስብ መሰል መሸፈኛውን የቀልጠዋል፡፡ ስለዚህ ከ 25 ዲሴ በላይ በሞቀ ውሃ እጃችሁን፣ ልብሳችሁን፣እና ማንኛወንም ነገር እጠቡ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሙቅ ውሃ ሳሙና ብዙ አረፋ እዲያወጣ ስለሚያደርግ የበለጠ ጠቃሚ ይሆናል፡፡ ⚡️አልኮል እና ከ65 እጅ በላይ ከሆነ አልኮል ጋር የተደባለቀ ማኛውም ነገር ማንኛውንም ስብ ያሟሟል በተለይ የቫይረሱን ስስ ስባማ የውጭ ሽፋን ያሟሟዋል፡፡ ⚡️ማንኛውም 1 እጅ ቀለም ማስለቀቂያ (Bleach) ( ለምሳሌ በረኪና) ከ 5 እጅ ውሃ ጋር ተደባልቆ የቫይረሱን ስብ ከውስጡ ያሟሟዋል፡፡ ⚡️አልኮል ፣ ክሎሪን ወይም ሳሙና ከተጠቀምን በኋላ ሃይድሮጂን ፐርኦክሳይድ (Hydrogen peroxide) መጠቀም የቫይረሱን ዲ.ኤን.ኤ ይሰባረዋል፡፡ ነገርግን ነጹህ ሃይድሮጂን ፐርኦክሳይድ መጠቀም አለባችሁ፡፡ ቆዳን ግን ይጎዳል፡፡ ⚡️ ቫይረሱ እንደ ባክቴሪያ ህይወት ያለው ነገር ስላይደለ በጸረ ባክቴሪያ ልንገለው አንችልም ስለዚህ ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች ቶሎቶሎ ልናፈራርሰው ብቻ ነው የምንችለው፡፡ ⚡️ማንኛውንም የተጠቀማችሁበትንም ይሁን ያልተጠቀማችሁበትን ልብስ እና አንሶላ በጭራሽ አታራግፉ፡፡ ምክኒያያቱም ክፍተት ባላቸው ነገሮች (አየር እና ውሃ የሚያሳልፉ) ቫየረሱ ሲጣበቅ ምንም መንቀሳቀስ የማይችል ሲሆን በ3 ሰአት ውስጥ እራሱ ይፈራርሳል፡፡ መዳብ በተፈጥሮው ተዋህስያን አምካኝ በመሆኑ እና እንጨት ደግሞ እርጥበትን በሙሉ ስለሚያስወግድ እና አንዴ ቫይረሱ ካረፈበት ስለማይለቀው ቫይረሱ ለ4 ሰአታት ብቻ ተቀምጦበት ይሰባበራል፡፡ ( cardboard ) ላይ 24 ሰአታት፣ ብረታ ብረት ላይ 42 ሰአታት፣ ፕላስቲክ ላይ 72 ሰአታት ከመፈራረሱ በፊት ሊቆ ይችልል፡፡ ነገርግን ካራገፍን ወይም የአቧራ ማራገፊያ ማሽን ከተጠቀምን ቫይረሱ ለቀጣይ 3 ሰአታት በአየር ውስጥ በመቆየት ወደ አፍና አፍንጫችን የመግባት እድል ያገኛል፡፡ ⚡️የቫይረስ ሞሎኪውሎች በሰው ሰራሽ እንደ መኪና እና የቤት አየር ማቀዝቀዣ ላይ ተደላድለው ይቆያሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ተደላድሎ ለመቆየት እርጥበት እና በተለይ ደግሞ ጨለማ ቦታ ይፈልጋሉ፡፡ ስለዚህ የአየር እርጥበታማነትን ማስወገድ፣ ደረቅ፣ ሞቃት እና ብርሃናማ ሁኔታዎችን መፍጠር ቫይረሱ በቶሎ እንዲዳከም ያደረጉታል፡፡ ⚡️ማንኛውም ዩቪ ( አልትራቫዮሌት) ብርሃን ያለው ቁስ የቫይረሱን ፕሮቲን ይሰባብረዋል፡፡ ለምሳሌ የአፍንጫ እና አፍ መሸፈኛን አክሞ እንደገና ለመጠቀም ፈጽሞ ውጤታማ ነው፡፡ ነገር ግን ተጠንቀቁ ይህ ብርሃን በቆዳችን ላይ ያሉ የፕሮቲን ክፍሎች በመጉዳት በቆይታ የቆዳ መሸብሸብ እና የቆዳ ካንሰር ሊያስከትል ይችላል። ⚡️ቫይረሱ ጤነኛ ቆዳ አልፎ ሊገባ አይችልም፡፡ ( ይህማለት ቁስለት ወይም የተከፈተ ቆዳ ካገኝ በቀላሉ ወደ ስውነታችን ሊገባ ይችላ እና መሸፈን እና መጠንቀቅ አለብን ማለት ነው) ⚡️አቼቶ (Vinegar ) የቫይረሱሱን የውጭ ስባማ አካል ሊያሟሟው ስለማይችል ከቫይረሱ ሊከላከል አይችልም ⚡️ማኛውም የመጠጥ አልኮል ወይም በጣም ጠንካራው ቮድካን ጨምሮ ከ40 ፐርሰንት በላይ አልኮል ስለሌላቸው የሚፈለገው 65 ፐርሰንት አልኮል ስለሆነ ከቫይረሱ ሊከላከሉ አይችሉም፡፡ ⚡️የአፍ መጉመጥሞጫው የአሜሪካው LISTERINA መጠቀም ከፈለግን 65 ፐርሰንት አልኮል አለው፡፡ ( ጠቃሚ ነው ማለት ነው) ⚡️በተፋፈጉ ጠባብ ቦታዎች እና ክፍሎች ውስጥ ቫይረሱ በብዛት ሊኖር የሚችል ሲሆን በተናፈሱ እና በተፈጥሮ ገላጣ ቦታዎች የቫይረሱ መጠን አነስተኛ ነው፡፡ ⚡️ተደጋግሞ ተብሏል ነገርግን እጃችሁን ታጠቡ። አፍንጫችሁን፣ ምግብ፣ የበር መዝጊያዎች፣ እጀታዎች፣ ማብሪያ ማጥፊያዎች፣ የርቀት መቆጣጠሪያዎች፣ የእጅ ስልኮች፣ ሰአት፣ ቴሌ ቪዥን፣ እና መታጠቢያ ቤት ከመጠቀማችሁ በፊት እና በኋላ እጃችሁን መታጠብ አለባችሁ፡፡ ⚡️የቫይረሱ ሞሎኪዩሎች በጥቅጥቅ እና ጥቃቅን የእጃችን ሽብሽብ ወይም በተቆረጠ ቆዳችን መሃል ሊቀመጡ ስለሚችሉ በተቻለ መጠን እጃችንን በብዙ ውሃ ማራስ እና መታጠብ ያስፈልጋል፡፡ እጃችንን ባራስነው መጠን የቫይረሱ መጠን በዛው ልክ ይቀንሳል።

የትራንስፖርት ሚንስትር ዴኤታ በመሆን የተሾሙት አቶ ካሳሁን ጎፌ ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የስራ ሃላፊዎች ጋር በዛሬዉ ዕለት ትዉዉቅ አደረጉ፡፡ በዚህ ወቅት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም እያከናወነ ያለዉን ተግባር እና ቀጣይ እቅዶችን በተመለከተ በኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በቅርቡ ያስገነባዉን ቋሚ የኤግዝቢሽን ማዕከል ከተቋሙ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን ጎብኝተዋል፡፡ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሀገራዊ ሀላፊነቱን ይበልጥ ለመወጣት እያከናወነ ያለውን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ እንዲቀጥል የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ ሚኒስቴር ዴኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ ተናግረዋል። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ የተቋሙን ታሪክ አካቶ የያዘ በመሆኑ አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በዚሁ ጊዜም ወቅታዊዉን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እየተደረገ ያለዉ የቅድመ መከላከል ተግባር በተመለከተ ማብራሪያ ተስጥቷል፡፡ #ማዴቦ