ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 342 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 342 名订阅者。

根据 18 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 91,过去 24 小时变化为 11,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.44% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 491 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 348
订阅者
+1124 小时
+477
+9130
帖子存档
የአሳይታ- አፋምቦ-ጅቡቲ ድንበር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡ ወደ ጅቡቲ ለመሄድ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኘው የጋላፊ መስመር ሌላ ተጨማሪ አማራጭ ሆኖ የሚያገለግለው የአሳይታ-አፋምቦ-ጅቡቲ ድንበር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እየተጠናቀቀ ይገኛል። የፕሮጀክቱ ስራ 94 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ ቀሪ የማጠቃለያ ስራዎችን በቅርቡ ለማከናወን እየተሰራ ነው። በእስካሁኑ አፈፃፀም የአፈር ጠረጋ እና ቆረጣን ጨምሮ የሰብ ቤዝ ስራ ፣ የቤዝኮርስ ፣ የውሃ ማፋሰሻ ፣ የስትራክቸር ፣ የመንገድ ዳር ምልክቶች መትከል እና ቀለም መቀባት ስራዎች ከሞላ ጎደል የተከናወኑ ሲሆን ፣ የ46 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ማንጠፍ ስራም ተካሂዷል፡፡ የፕሮጀክቱ አካል የሆኑት የሶስት ድልድዮች ግንባታም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል። የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን የተመደበው በጀት 1,600,901,379.89 ብር ወጪ ሙሉ ለሙሉ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገዱ ርዝማኔ 50.34 ኪሎ ሜትር ሲሆን ፣ የጎን ስፋቱ ትከሻን ጨምሮ በገጠራማ ሥፍራዎች 10 ሜትር ፣ በወረዳ ከተሞች 19 ሜትር እና በዞን 21.5 ሜትር ስፋት አለዉ። ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው ሀገር በቀሉ የስራ ተቋራጭ አሰር ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ይዲዲያ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንትስ እያከናወነው ይገኛል። በአካባቢው ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረ በመሆኑ ህብረተሰቡ በመንገድ እጦት ምክንያት በእግር እና በግመል ከመጓዝ ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበረም። መንገዱ በዋናነት ኢትዮጵያን በአሳይታ በኩል ከጅቡቲ ጋራ በቅርበት ያስተሳስራል። ከዚህ በተጨማሪም አሳይታ ከተማን ከአፋምቦ ወረዳ ብሎም በርካታ ቀበሌዎችን በማገናኘት የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን ይበልጥ ያጠናክራል። ይህ አካባቢ የአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ የሚገኝበት በመሆኑ በርካታ ምርቶች የሚመረትበት መስመር ነው። ከእነዚህ ምርቶች መካከል እንደጥጥ ፣ ቴምር ፣ ሰሊጥ ፣ ቲማቲም ፣ ሽንኩርት ብርቱካን ፣ ሃባብ እና በርካታ ፍራፍሬዎች ይጠቀሳሉ። የመንገዱ መገንባት እነዚህን ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ብሎም ወደ ጀቡቲ ለማድረስ ይበልጥ ያግዛል። ከዚህም ባሻገር በመስመሩ የትምህርት ፣ ጤና እና መሰል ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግልጋሎቶችን በአፋጣኝ አንዲስፋፉ ያደርጋል። በተጨማሪም ይህ መስመር አሁን ላይ ያለውን የሚሌ - ዲቼ ኦቶ - ጋላፊ - ጅቡቲ ወደብ መንገድ በ 30 ኪሎ ሜትር ያሳጥረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

ሣምንታዊ_የሚዲያ_ትንተና_01_04_2016.docx0.48 KB

የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው ጅግጅጋ፣ ኅዳር ፣ 2016 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል በ672,098,730 (ስድስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊዮን) ብር ወጪ የሚገነባው የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከቶጎውጫሌ መገንጠያ አንስቶ እስከ ሐረር መውጫ ድረስ ያለውን ሥፍራ የሚሸፍን ሲሆን፣ 6 ነጥብ 93 ኪሎሜትር ርዝመት እና 30 ሜትር ስፋት አለው። በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራ ግንባታ ያካትታል። በእስከአሁኑ የግንባታ ሥራዎች መካከል የመሬት ጠረጋ፣ የሙሌት፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ፣ የድልድይ ግንባታ እንዲሁም የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው። የፕሮጀክቱ የግንባታ ደረጃ አሁን ላይ ከ50 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን፥ ቀሪ የግንባታ ሥራውን በግንቦት ወር 2016 ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። ግንባታውን የሚያከናውነው ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኤልዳ አማካሪ ድርጅት ይሠራል። ለግንባታው የተመደበው ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ በከተማዋ ውስጥ እንዲሁም መግቢያና መውጫ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ በእጅጉ የሚቀንስ ነው። ከሐረር ወደ ቶጎ ውጫሌ እና ቀብሪበያህ ወይም ቀብሪደሀር የሚጓዙ ተሸከርካሪዎች ጅግጅጋ ከተማ መግባት ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ መጓዝ ያስችላቸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት በማሳለጥ በኩል ግንባር ቀደም ሚና ይጫወታል፡፡ ፕሮጀክቱ ከ350 በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ የዕውቀት እና የልምድ ሽግግር እንዲፈጠር አስችሏል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook (https://www.facebook.com/www.era.gov.et)

የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመንግስት የስራ አፈጻጸምን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ ፣ ህዳር 26 ቀን 2016 ዓም (ኢመአ)፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመንግስት የስራ አፈጻጸምን አስመልክቶ ውይይት ውይይት አደረጉ፡፡ ውይይቱ የተካሄደው በዋናው መሥሪያ ቤት ፣ በመንገድ ምርምር ማዕከል   እና በዓለምገና ኢንጂነሪንግና ማኔጅመንት የሥልጠና ማዕከል የመሰብሰቢያ አዳራሾች ሲሆን ፤ ሁሉም የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተገኙበት የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመንግስት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።  በሰባት አበይት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የመንግስት የሩብ አመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ሰነድ በኢመአ የስራ  ኃላፊዎች ከቀረበ በኋላ ነው ውይይቱ የተካሄደበት፡፡  ሰነዱ  ጥቅል የኢኮኖሚ ሁኔታና አዝማሚያ ፣ የህዝብ ተጠቃሚነት ፣ የሀብት አስተዳደር ውጤታማነት ፣የሠው ሀብት ልማት ፣  የኢኮኖሚ ዘርፍ አፈፃፀም ፣ የመሠረተ ልማት አፈፃፀም ፣ እንዲሁም የፍትህና ዴሞክራሲ አፈፃፀሞችን የያዘ ነው፡፡ ሪፖርቱን አስመልክቶ ከተሳታፊዎቹ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን ፣  የቀረቡ ሃሳቦችን አስመልክቶ በአወያዮቹ ተገቢው ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር በመንግስት ደረጃ የታቀደው ዕቅድ የታለመለትን ግብ ሊመታ የሚችለው ሁሉም ሴክተር የድርሻውን ወስዶ  በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ሲችል መሆኑን በመገንዘብ ፣ እያንዳንዱ ሰራተኛ እና የስራ ኃላፊ  እንደ ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያቀደውን ዕቅድ በአግባቡ በመፈፀም ተቋማዊና ሀገራዊ ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ የስራ መመሪያ ከተሰጠ በኋላ የዕለቱ የውይይት መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የፑኝውዶ- ጎግ -ጊሎ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የግንባታ አፈጻጸም ላይ ይገኛል፡፡ በጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በአኝዋሃ ዞን እየተገነባ የሚገኘዉ የመንገድ ፕሮጀክት በጥሩ የግንባታ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከጋምቤላ እና አካባቢዉ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤት የተገኘዉ መረጃ ያመላክታል፡፡አሁናዊ የግንባታ አፈጻጸሙ 70 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ በመንገድ ግንባታው በእስከ-አሁኑ  99.61% የአፈር ጠረጋ ሥራ ፣ 50% የፍሳሽ ማስወገጃ ፣ 87% የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም  72% የስትራክቸር ስራዎች ተከናዉነዋል፡፡ በተያያዘም 38 ኪሎሜትር የአስፓልት ንጣፍ ስራ ተከናውኗል። ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 876 ኪሎ ሜትር  ርቀት ላይ ከምትገኘዉ ፒኝውዶ ከተማ መነሻዉን በማድረግ ጊሎ ወንዝን ተሻግሮ ፍጻሜዉን ያገኛል፡፡ መንገዱ የሚገነባበት መልከዓ ምድራዊ አቀማመጥ 12.5 % ሜዳማ ሲሆን ፣ 87.5% ወጣገባ ነው፡፡ የመንገዱ የቀድሞ ይዞታ ከፊሉ ነባር የጠጠር መንገድ ሲሆን ፣ የተቀረዉ ምንም አይነት የመንገድ አውታር ያልተዳረሰበት ነበር፡፡ በመሆኑም ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የአካባቢዉ ህብረተሰብ ተጠቃሚ ያደርጋል። የመንገዱ የጎን ስፋት የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣  በወረዳና ዞን ከተሞች ደግሞ 19 እና 21.5 ሜትር ተጨማሪ ስፋት ይኖረዋል። ቻይና ሬይል ወይ ሰቭንዝ ግሩፕ የተባለ የቻይና አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ  የመንገድ ግንባታውን እያከናወነ ሲሆን፣ የማማከር እና ቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኢንጅነር ዘውዴ እስክንድር ኮንሰልቲንግ እና ኢንሲራድ ሲቪል ሲስተምስ ኢንጂነሪንግ በጣምራ እያሰሩት ይገኛሉ፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ 60 ሜትር ርዝማኔ ያለዉ የጊሎ ወንዝ ድልድልይ ስራ የሚያካትት ሲሆን ተጨማሪ 110 በላይ ጥቃቅን የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦዎች ግንባታም የፕሮጀክቱ አካል ናቸዉ፡፡ ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አኝዋሃ ዞን ዉስጥ የሚገኙ ጎግ ወረዳን ጨምሮ  በርካታ ከተሞችን እና ቀበሌዎችን በቅርብ ርቀት የሚያስተሳስር ከመሆኑም ባሻገር በመቶ ኪሎ ሜትሮች ተራርቀዉ ይገኙ የነበሩትን የዲማ ወረዳና የዞኑን ዋና ከተማ አቦቦና ከክልሉ ዋና ከተማ ጋምቤላ ጋራ እንዲሁም ከአጎራባች ጎግ ወረዳ ጋር በቅርበት ያገናኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አካባቢው ሰፊ የኢንቨስትመንት እና የማዕድን ሃብትን የተላበሰ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት የአገራችን ኢኮኖሚያዊ እድገት ከማጠናከር አኳያ ትልቅ ጥቅም ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የቆሬ -ጊቤ ወንዝ መንገድ የከባድ ጥገና ስራ በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የአዲስ -ጊቤ ወንዝ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት አካል የሆነው ኮንትራት 3፡ የቆሬ - ጊቤ ወንዝ 93 ኪሎ ሜትር ከባድ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክት ( Asphalt Overlay maintenance project) በጥሩ የግንባታ ሂደት ላይ ነው፡፡ ጥገናውን ቲክስ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከኤም.ሲ.ጂ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ጋር በጥምረት በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኤስጅ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከዴልታ ኮንሰልቲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ጋር በጋራ እያካሄደ ነው። አሁን ላይ የግንባታ ግብዓት የማምረት ፣ ሰብ ቤዝና ቤዝ ኮርስ የማንጠፍ ፣ የቅድመ አስፋልት ልባስ ስራ ፣ የተበላሹ ቦታዎችን ለይቶ የመቁረጥና በአስፋልት መልሶ የመጠገን ስራዎች እንዲሁም የአስፋልት ድረባ ስራ (Asphalt Overlay) በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ ለመንገዱ ጥገና የሚውለው የግንባታ ወጪ አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሀምሳ አንድ ሚሊዮን ስምንት መቶ ስምንት ሺህ ሶስት መቶ ሀምሳ አንድ ብር ከአስራ ሰባት ሳንቲም (1,651,808,351.17) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ መንገዱ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት የሚያስተናግድ ከመሆኑም ባሻገር ጉልህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው ሲሆን የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እንዲችል ታስቦ ነው ከፍተኛ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው፡፡ ባለፈው በጀት ዓመት የተስተዋሉ የስራ ተቋራጩ የአቅም እና ግብአት ውስንነቶች እንዲሁም አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የፀጥታና ተያያዥ ችግሮች ፕሮጀክቱ በተያዘው ዕቅድ መሰረት እንዳይካሄድ አድርገውት የቆዩ ቢሆንም ፥ ችግሮቹን ለመቅረፍ በኢመአ በኩል ሰፊ ክትትልና ድጋፍ በመደረጉ በአሁኑ ወቅት ፕሮጀክቱ በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ በተያያዘም አዲስ-ጊቤ ወንዝ አስፓልት ኦቨርሌይ ፕሮጀክት ሎት 2: አዲስ-ቆራ 64 ኪሎሜትር ከፍተኛ የመንገድ ጥገና ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የዚህን መንገድ ግንባታ ቤአይካ ጠቅላላ ንግድ ስራ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነው የሚገኝ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ቤዛ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ/ እየተከታተለው ነው፡፡ በመንገድ ፕሮጀክቱ ላይ የግንባታ ግብዓቶችን በሚፈለገው ጊዜ ውስጥ አለመጓጓዝ እና የሳይት አስተዳደር (Site coordination management) ችግሮች የመንገዱን ጥገና በሚፈለገው ልክ እንዳይከናወን አድርጎት መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በዚህም ረገድ ፕሮጀክቱን ለማሻሻል በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ አሁን ላይ የአስፋልት ንጣፍ፣የጠጠርና የሌሎች የግንባታ ግብዓቶች ማምረት፣የተለዋጭ መንገድ ማዘጋጀት፣የአስፋልት ድረባ (Asphalt Overlay) ስራዎች እተከናወኑ የሚገኙ በመሆኑ የጥገና ግንባታው በተሻለ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ነዉ። በአጠቃላይ መንገዱ ተጠግኖ ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባ-ወልቂጤ-ጅማ ኮሪደር ይስተዋል የነበረውን የትራፊክ እንቅስቃሴ መስተጓጎልና እንግልት ከመቅረፍም ባሻገር በአካባቢዉ የሚመረቱ እንደ ቡና ፣ ጤፍ ፣ በቆሎ ፣ እንሰት ፣ ሽንብራ እና አቦካዶ የመሳሰሉ ምርቶችን በቀላሉ ወደ ገበያ ለማቅረብ ያስችላል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የድሬዳዋ-ሽንሌ እና የድሬዳዋ ከተማ ተለዋጭ 29 ነጥብ 29 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 46 በመቶ ደርሷል ድሬዳዋ፣ ኅዳር 13፣ 2016 (ኢ መ አ)፡- የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ከሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ጋር የሚያገናኘው የድሬዳዋ-ሽንሌ እና የድሬዳዋ ከተማ ተለዋጭ 29 ነጥብ 29 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 46 በመቶ ደርሷል፡፡  በመንገድ ግንባታው አሁን ላይ የጠረጋ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት የሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ፣ የመፋሰሻ ቱቦ ማምረት እንዲሁም የስትራክቸር  ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የአንድ ከፍተኛ  ድልድይ ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ 100 ሜትር ርዝማኔና እና 15 ሜትር ስፋት ያለው ሁለተኛው ድልድይ በግንባታ ላይ ይገኛል። በአንድ ወር ጊዜ ውስጥም አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ለመጀመር ዕቅድ ተይዟል፡፡  በመንገድ ወሰን ክልል ውስጥ የሚገኙ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ንብረቶች በወቅቱ ማንሳት አለመቻሉ የግንባታው ዋናው ማነቆ መሆኑ የተመለከተ ሲሆን፣ በሥራ ተቋራጩ በኩል ደካማ የፕሮጀክት አመራር እንዲሁም የግንባታ ግብዓት እጥረት እና ዋጋ መናር በፕሮጀክቱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል፡፡ ችግሮቹን ለመቅረፍ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና ከሽንሌ ወረዳ ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማድረግ የተወሰኑ የመንገድ ክፍሎችን ነፃ ማድረግ ተችሏል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህም አዎንታዊ ለውጦች ታይተዋል፡፡ በቀጣይም የቅርብ ድጋፍ እና ክትትሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ዓለም-አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከፌደራል መንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘ ሲሆን፣ ቤዛ ኢንጂነሪንግ ኬንያ ሊሚትድ ፕሮጀክቱን በማማከር እና በመቆጣጣር በኩል ይሳተፋል፡፡ የመንገዱ መገንባት የከተማዋን የትራፊክ መጨናነቅ የሚያስተነፍስ ከመሆኑም ባለፈ ከጅቡቲ በድሬዳዋ ደወሌ መንገድ የሚመጡ ተሸከርካሪዎች ከተማውን ሳያቋርጡ ማለፍ ያስችላቸዋል፡፡ በተጨማሪም በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን የሚያገናኝ ብቸኛ መንገድ ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የአዴሌ-ግራዋ 53 ነጥብ 03 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ እየተካሄደ ነው ሐሮማያ፣ ኅዳር 11፣ 2016 (ኢ መ አ) ፡- በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የአዴሌ-ግራዋ 53 ነጥብ 03 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል። በአሁኑ ወቅትም ፕሮጀክቱ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራ ከ52 በመቶ በላይ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ አሁን ላይ የአፈር ጠረጋ፣ የቆረጣ፣ የተመረጠ አፈር ሙሌት፣ የሰብ ቤዝ፣ የስትራክቸር፣ የቤዝ ኮርስ ምርት እንዲሁም የአስፋልት ፕላንት ተከላ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በተጨማሪም የመንገድ ግንባታው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያስተጓጉል የተለዋጭ መንገድ ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ በዚህ ዓመት መጨረሻ የአስፋልት ንጣፍ ለመጀመር ዕቅድ ተይዞ ነው እየተሠራ የሚገኘው፡፡ ግንባታው የሚከናወነው በቻይናው ሂቤ ኮንስትራክሽን ግሩፕ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ ሲሆን፣ የማማከሩን ሥራ የሚሠራው ጎጎት አማካሪ መሐንዲሶች ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ነው፡፡ ለግንባታው የተመደበው 1ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት በጀት ነው የሚሸፈነው፡፡ በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል በዋናነት አደሌ፣ ዳዊ፣ ኩርፋ እና ግራዋ ከተሞች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የወሰን ማስከበር ሥራ አለመጠናቀቁ፥ የግንባታ ቁሳቁስ ዋጋ መናር እና አቅርቦት እጥረት፥ በተቋራጩ በኩል የተስተዋለ የአመራር ክፍተት እንዲሁም ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በግንባታው ሂደት ላይ እክል ፈጥሯል፡፡ ችግሮቹን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የተለያየ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡ የመንገዱ መገንባት፥  አደሌ፣ ኩርፋ፣  ጨሌ  እና  ግራዋ  ወረዳዎችን  እንዲሁም  ቆርኬ_አውሜራ  ቢፍቱ  ዳዌ  እና  ኦሮሚቱ ቀበሌዎችን  የሚያገናኝ  ሲሆን፣  በዚህ  ሥፍራ  የሚኖረው  ማኅበረሰብ    የጫት፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ገብስ እና  ስንዴ ምርቶችን ለማዕከላዊ ገበያ  ለማቅረብ   ያስችለዋል  ። ከዚህም ባለፈ የመንገዱ  መሠራት የቱሪስት  መስህብ  የሆነውን እና በሥፍራው  የሚገኘውን የልጅ እያሱን  ቤተ-መንግሥት ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ ረገድ  ከፍተኛ  አስተዋጽኦ  ይኖረዋል ።

በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮ -ጅቡቲ ትራንስፖርት ኮሪደር ፕሮጀክት አካል የሆነው የአዳማ - አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ ኪሎ ሜትር 60 የፍጥነት መንገድ የአስፋልት የማንጠፍ ሥራ ተጀመረ። የአዳማ-አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ ኪሎ ሜትር 60 የፍጥነት መንገድ 61.5 ኪሎ ሜትር እርዝማኔ ያለው ሲሆን ፣ ግንባታው ከአፍሪካ ልማት ባንክ እና ከኢትዮጵያ መንግሥት በተገኘ በ 6.6 ቢሊየን ብር ወጪ እየተከናወነ ነው። ግንባታውን የሚያከናውኑት ጂ. ኤም.ሲ እና ኤል.አር .ቢ.ሲ.ኤል የሚባሉ አለም አቀፍ ተቋራጮች በጋራ ሲሆን የማማከሩን ሥራ የሚያከናውኑት ደግሞ ኤል.ኤ.ኤስ.ኤ እና ዩ.ኒ.ኮን ናቸው። ይህ 61 ኪ.ሜ የሚሸፍነው የፍጥነት መንገድ አገናኝ መንገዶችን ፣ ማሳለጫ መንገዶችን ፣ የክፍያ ጣቢያዎችን ፣ የመኪና እና የእግረኛ መሸጋገሪያ ድልድዮችን ያካትታል። የፕሮጀክቱ አሁናዊ አፈጻጸም 12.5 በመቶ ሲሆን፣ በዚህም የአፈር ጠረጋ፣ የቆረጣ ሥራ፣ የአፈር ሙሌት፣ የሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን በእስካሁኑ 1.6 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ማንጠፍ ስራ ተከናውኗል። ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ የሚታዮ መስተጓጉሎችን በመቅረፍ በቀጣይ በተሻለ ፍጥነት እንዲከናወን ከፍተኛ ክትትል እና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል። መንገዱ ትልልቅ የድልድይ ግንባታ ፣ ማሳለጫዎችና ማቋረጫዎች ፣ የአቃፊ ግንብ ፣ የመንገድ ዳር የትራፊክ ምልክቶች ፣ የደህንነት ካሜራዎችን ፣ ሌሎች ተጨማሪ ሥራዎችን አካቶ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ የሚዘልቀው 80 ኪሎ ሜትር የአዲስ-አዳማ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል ፤ የዚህ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የመስመሩን የትራፊክ ፍሰት ለማቀላጠፍ ብሉም የተሽከርካሪዎች የጉዞ ጊዜና ዋጋ በመቀነስ አዎንታዊ ተጽዕኖ የሚያሳድር ይሆናል፡፡ ከዚህም ባሻገር የዚሁ የፍጥነት መንገድ አካል ለሆነው የሜኦሶ-ድሬዳዋ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአለም ባንክ የ730 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ማጽደቁ ይታወቃል፡፡ ይኸው የአዳማ-አዋሽ-ሜኦሶ-ድሬዳዋ የፍጥነት መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከድሬደዋ-ደወሌ የክፍያ መንገድ ጋር በመተሳሰር ለአዲስ አበባ-ሰመራ-ጋላፊ መንገድ አማራጭ ሆኖ በማገልገል የኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ወጪና ገቢ ንግድ ይበልጥ እንዲጠናከር ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et