EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 533 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 332,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 177 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 533 名订阅者。
根据 05 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 18,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 27.66%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.09% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 297 次浏览,首日通常累积 2 344 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 06 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 533
订阅者
-424 小时
-77 天
+1830 天
帖子存档
15 530
በእሳት አደጋ ንብረታቸው ለወደመባቸው የኃይል ማመንጫው ሠራተኞች ድጋፍ ተደረገ
………….////……….
የአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ መጋቢት 17 ቀን 2013 ዓ.ም እኩለ ለሊት ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ ምክንያት ንብረታቸው ለወደመባቸው ሠራተኞች 882 ሺህ ብር ድጋፍ ተደረገ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያዩ ሁንዴሳ ድጋፉን ለተጎጂ ሠራተኞች ባስረከቡበት ወቅት በጣቢያው የሠራተኞች መኖሪያ ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ የሰው ህይወት በመጥፋቱ እና ንብረት በመውደሙ በእጅጉ ማዘናቸውን ገልፀዋል፡፡
ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም የተቋሙ ሥራ አመራር ኮሚቴ አዋቅሮ ሲንቀሳቀስ ቆይቷል ያሉት አቶ እያዩ የተጎጂዎቹን ንብረት በተወሰነ መልኩ ለመተካት ጥረት ተደርጓልም ብለዋል፡፡
እንደ አቶ እያዩ ገለፃ ጉዳት የደረሰባቸውን መኖሪያ ቤቶች በአፋጣኝ መልሶ ለመጠገን 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ተመድቦ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡
የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው የእሳት አደጋው በሰው እና በንብረት ላይ ጥፋት በማድረሱ በተቋሙ ሥራ አመራር ስም ሀዘናቸውን ገልፀው መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱም ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
አቶ ሙላት እንዳሉት ሠራተኛው የሚያጋጥሙትን ችግሮች ለመፍታት ተቋሙ ወደፊትም ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ደግሞ ማህበሩ ሠራተኞች አደጋ በገጠማቸው ወቅት ሁሉ ከተቋሙ ሥራ አመራር ጋር በመሆን የመፍትሔ አካል ሲሆን ቆይቷል ብለዋል፡፡
በአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ የተጎዱትን ሠራተኞች ለማቋቋም የተደረገው አፋጣኝ ድጋፍ ምስጋና የሚያስቸረው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ሲወሰድ በነበረው የህግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት ተቋሙ ከ600 እስከ 700 ለሚጠጉ ሠራተኞቹ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በመመደብ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱንም አስታውሰዋል፡፡
በኃይል ማመንጫ ጣቢያው 19 ክፍሎች ባሉት የሠራተኞች መኖሪያ ብሎክ ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉና ከ 3 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙ የሚታወስ ነው፡፡
ተቋሙ ባደረገው እርዳታ ለእያንዳንዱ ተጎጂ እንደየጉዳቱ መጠን ከ13 ሺህ 5 መቶ እስከ 94 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሚያዝያ 04 ቀን 2013 ዓ.ም.
15 530
የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ዛሬ ወደ ኃይል ማመንጨት ስራው ተመለሰ
.............////..........
ለወራት ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ የቆየው የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ዛሬ ሥራ ጀመረ።
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከብሔራዊ የኃይል ቋት (ግሪድ) ጋር የሚገናኝበት መስመር በመቋረጡ ምክንያት ኃይል ማመንጨት አቁሞ እንደነበር ይታወሳል።
ከተከዜ- መቀሌ በተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ሲደረግ የነበረው ጥገና በመጠናቀቁ ዛሬ ቀን ከ 7:18 ሰዓት ጀምሮ በጊዜያዊነት ከሲስተም ጋር ሳይገናኝ ራሱን በራሱ እየተቆጣጠረ (Isolated mode) ኃይል መስጠት ጀምሯል።
በአሁኑ ሰዓት ጣቢያው ካሉት አራት ዩኒቶች መካከል በሁለት ዩኒቶች እስከ 108 ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል እየሰጠ ይገኛል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ካለፈው ሐሙስ ከሰዓት ጀምሮ በትግራይ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ ከተከዜ ኃይል ማመንጫወደ መቀሌ የሚሄደው መስመር ተጠግኖየተከዜ ኃይል ማመንጫ ስራ በመጀመሩ ዳግም አገልግሎት ማግኘት ጀምሯል።
ቀደም ሲል ከአላማጣ መኾኒ አሸጎዳ መቀሌ የሚሄደው መስመር ላይ ባጋጠመችግር ምክንያት የትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ነበር።
በትግራይ በተካሄደውን የህግ ማስከበር ተከትሎ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የተከዜ ግድብ ደግሞ መንግስት በአውሮፕላን ደብድቦ አፍርሶታል ተብሎ የሀሰት ወሬ ተናፍሶ ነበር።
በወቅቱም በግድቡ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰ መግለፃችን ይታወሳል።
የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአራት ዩኒቶች 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ባለ ጥምር ቅስት (double arc)ቅርፅ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው።
መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ/ም
15 530
በምሰሶዎቹ ላይ ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎች ከሰረቁት ንብረት ጋር እጅ ከፍንጅ እየተያዙ ነው
………….//////…………
ከጢስ ዓባይ - ባህርዳር በተዘረጋው ባለ132 ኮሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ምሰሶዎች ላይ ስርቆት የፈፀሙ ሁለት ተጠርጣሪዎች ከሰረቁት ንብረት ጋር በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ኃይሎች በሰጠው ጥቆማ ምሰሶውን በመቆራረጥ በማዳበሪያ ጠቅልለው ከመሸጣቸው በፊት በአማራ ክልል የፀጥታ ኃይሎች የተያዙ ሲሆን ከወንጀሉ ጋር የተገናኙ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ምርመራው መቀጠሉን ለማወቅ ተችሏል።
የኢነርጂ አዋጅ 810/2006 አንቀጽ 26 ላይ በኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ ገንዘብ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ አስቀምጧል፡፡
በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 29 ላይ ደግሞ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ማናቸውንም ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ነገር ያስቀመጠ፣ የኤሌክትሪክ እቃ ያስቀመጠ፣ የተከለ፣ የዘረጋ ወይም እንዲተከል እንዲዘረጋ የፈቀደ፣ በኤሌክትሪክ ‹ኢንስታሌሽን› ይዞታ ውስጥ ግንባታ የሚያከናውን፣ የሚያርስ ወይም የሚቆፍር፣ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ወይም የሚያውኩ ግንባታዎችን አላፈርስም፣ ዛፎችን አልቆርጥም ወይም አልመለምልም፣ ሰብሎችን፣ አትክልቶችን ወይም ሌሎች ነገሮችን አላስወግድም ያለ እንደሆነ፤ ማናቸውም የኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ አካላትን ያለያየ፣ የሰረቀ ወይም በማለያየትና በስርቆት የተባበረ እንደሆነ፣ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ሆን ብሎ ወይም በግዴለሽነት ጉዳት በማድረስ ያቋረጠ እንደሆነ፣ እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም ከብር 25 ሺህ ባልበለጠ የገንዘብ መቀጮ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ያስቀምጣል፡፡
በመሆኑም ከዘረፉት ንብረት ጋር እጅ ከፍንጅ በተያዙት ሰዎች ላይ አስተማሪና ተመጣጣኝ ቅጣት እንደሚወሰድና ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊት ፈፃሚዎችን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ የሚያደርግ ቅጣት እንደሚወሰንባቸው ተስፋ እናደርጋለን።
በዚህ አጋጣሚ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ በማድረጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል።
ምሰሶዎቹ በመዘረፋቸው ተቋሙ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት መዘገባችን ይታወሳል።
መጋቢት 25 ቀን 2013 ዓ.ም.
15 530
በምሰሶዎቹ ላይ የተፈፀመው ስርቆት ተቋሙን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆነ ኪሳራ ዳርጎታል
………….//////…………
በጢስ ዓባይ - ባህርዳር ባለ132 ኮሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶዎች ላይ የተፈፀመው ስርቆት ተቋሙን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆነ ኪሳራ እንደዳረገው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንደገለፁት የማስተላለፊያ መስመሩ 30 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 91 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች አሉት፡፡
ስርቆቱ የተፈፀመውም በመስመሩ ላይ ካሉት ምሰሰሶዎች መካከል በስምንቱ ላይ እንደነበር መግለፃችን ይታወሳል፡፡
በመስመሩ ላይ በዓመት ሁለት ጊዜ መደበኛ ፍተሻ እንደሚካሄድ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ በህዳር ወር 2013 ዓ.ም ፍተሻ ተካሂዶበት እንደነበርና ምንም ዓይነት ችግር እንዳልነበው አረጋግጠዋል፡፡
በምሰሶዎቹ ላይ በተፈፀመው ስርቆት ተመርቶ ወደ ብሔራዊ ግሪድ መድረስ የነበረበት ኃይልን ጨምሮ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል፡፡
የወደቁትን ምሰሶዎች የመጠገንና ወደነበሩበት የመመለስ ሥራ እየተከናወነ ሲሆን ይህም አሥራ አምስት ቀን ሊፈጅ ይችላል ብለዋል፡፡
ህብረተሰቡ መሰረተ ልማቶችን በባለቤትነት መንፈስ ኢንዲጠብቅና የተለየ ነገር ሲመለከት ለፀጥታ አካላት እንዲያሳውቅ ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ.ም.
15 530
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ለማደግ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ
............../////.............
በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በምድብ ሀ ተደልድሎ ጨዋታውን በማድረግ ላይ የሚገኘው የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግ ለማደግ ከፍተኛ ፉክክር እያደረገ እንደሚገኝ የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ተናገሩ፡፡
ከመከላከያ፣ ከደሴ ከተማ፣ ከወልድያ ከተማ፣ ከኮምቦልቻ ከተማ፣ ከገላን፣ ከለገጣፎ ለገዳዲ፣ ከፌደራል ፖሊስና ከደብረብርሃን ከነማ ጋር የተደለደለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እስከአሁን ከተካሄዱት 11 ጨዋታዎች 23 ነጥብ በመሰብሰብ ከመከላከያ ክለብ ጋር በእኩል ነጥብ ምድቡን እየመሩት መሆኑን አሰልጣኝ ክፍሌ ገልፀዋል፡፡
የእግር ኳስ ክለቡ የቴክኒክ ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ ወልዴ በበኩላቸው ቡድኑ በአካል ብቃት፣ በሥነልቦና፣ በታክቲክና ቴክኒክ ብቁ ሆኖ ውድድሩን በአንደኛነት እንዲያጠናቅቅ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡
አምስት ጨዋታዎች ብቻ የቀሩት የከፍተኛ ሊግ ውድድር ወደ ፕሪሜርሊግ ለማደግ ከፍተኛ ፉክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር በመሆኑ ጨዋታው በተመሳሳይ ሰዓት መካሔድ ሲገባው ሌላን ክለብ ያላግባብ ተጠቃሚ ለማድረግ በሚመስል መልኩ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ክለብ በተደጋጋሚ ቀድሞ እንዲጫወት በመደረጉ አሰራሩ እንዲስተካከል ለውድድር አዘጋጁ አካል ቅሬታ ማቅረቡን ክለቡ አስታውቋል፡፡
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እንደ ፈቃደ ሙለታ፣ዮርዳኖስ ዓባይ፣አንዋር ያሲን፣ አንዋር ሲራጅ፣ ሲሳይ ተሰማ እና ሌሎች ስመጥር ተጨዋቾችን ከራሱ አልፎ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ያፈራ አንጋፋ ክለብ ነው፡፡
መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ/ም
15 530
የጢስ ዓባይ ባህር ዳር የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ምሰሶ ስርቆት ተፈፀመበት
............./////............
ከጢስ ዓባይ የውሃ ኃይል ማመንጫ ወደ ባህር ዳር የተዘረጋው ባለ 132 ኮሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ምሰሶ ላይ ስርቆት ተፈፀመ፡፡
ከሰኞ ምሽት ጀምሮ በተፈፀሙ ስርቆቶች ስምንት ምሰሶዎች ወድቀዋል፡፡
ይሁንና በአካባቢው ኃይል እንዳልተቋረጠ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ምሰሶዎቹ በመውደቃቸው ከኃይል ማመንጫው በባህር ዳር ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ይላክ የነበረ እስከ 30 ሜጋ ዋት ኃይል መላክ አልተቻለም፡፡
ችግሩንም በየደረጃው ለሚገኙ የመስተዳድር አካላት እንዲያውቁት የተደረገ ሲሆን የወደቁትን ምሰሶዎች በመጠገን ወደነበሩበት ለመመለስ የጥገና ስራ ተጀምሯል፡፡
መጋቢት 23 ቀን 2013 ዓ/ም
15 530
የሥርዓተ -ጾታ እኩልነትን በሁሉም የስራ ክፍሎች ለማስፋፋትና ለመተግበር እየተሰራ ነው
……….////………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሴቶች፣ ህጻናት እና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ የስርዓተ -ጾታ እኩልነትን በሁሉም የኃይል ማመንጫዎች፣ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በሪጅኖች ለማስፋፋት እና ለመተግበር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡
ቢሮው በሥርዓተ-ጾታ ጽንሰ ሃሳብ ዙሪያ ከኃይል ማመንጫ፣ከማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ከሪጅኖች ለተወጣጡ የሴቶች ፣ህጻናት እና ወጣቶች ጉዳይ ተወካዮች በዋናው መስሪያ ቤት አዳራሽ ለሁለት ቀናት የሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና ውይይት ዛሬ ተጠናቋል፡፡
በስልጠናው ላይ የቢሮው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ አደኤ እንደተናገሩት የስልጠናው ዋና ዓላማ የስርዓተ -ጾታ እኩልነትን በማረጋገጥ የሴቶችን ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነት እንዲሁም በህጻናት ደህንነት በሁሉም የስራ ክፍሎች ለማስጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠርነው፡፡
ሠልጣኞች በጽንሰ ሃሰብ እና በልምድ ያዳበሩትን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባቸው ዳይሬክተሯ አስገንዝበዋል ፡፡
በቢሮው የሥርዓተ ጾታ ባለሞያ አቶ ተስፋዩ ዮሀንስ በበኩላቸው ስልጠናው ከቢሮው ጋር በተቀናጀና በተናበበ መልኩ ለመስራት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
የስልጠናው ተሳታፊዎች በየስራ ክፍላቸው ባሉ የተለያዩ መዋቅሮች በመታቀፍ የሴቶች ፣የህጻናትና ወጣቶች መብትና እና ጥቅማ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ ያግዛቸዋል ብለዋል ፡፡
መጋቢት 17 ቀን 2013 ዓ/ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
