uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 533 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 332-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 177-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 533 obunachiga ega bo‘ldi.

05 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 18 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.66% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.09% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 297 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 344 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 06 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 533
Obunachilar
-424 soatlar
-77 kunlar
+1830 kunlar
Postlar arxiv
በእሳት አደጋ ንብረታቸው ለወደመባቸው የኃይል ማመንጫው ሠራተኞች ድጋፍ ተደረገ ………….////………. የአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ መጋቢት 17 ቀን 2013 ዓ.ም እኩለ ለሊት ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ ምክንያት ንብረታቸው ለወደመባቸው ሠራተኞች 882 ሺህ ብር ድጋፍ ተደረገ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያዩ ሁንዴሳ ድጋፉን ለተጎጂ ሠራተኞች ባስረከቡበት ወቅት በጣቢያው የሠራተኞች መኖሪያ ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ የሰው ህይወት በመጥፋቱ እና ንብረት በመውደሙ በእጅጉ ማዘናቸውን ገልፀዋል፡፡ ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም የተቋሙ ሥራ አመራር ኮሚቴ አዋቅሮ ሲንቀሳቀስ ቆይቷል ያሉት አቶ እያዩ የተጎጂዎቹን ንብረት በተወሰነ መልኩ ለመተካት ጥረት ተደርጓልም ብለዋል፡፡ እንደ አቶ እያዩ ገለፃ ጉዳት የደረሰባቸውን መኖሪያ ቤቶች በአፋጣኝ መልሶ ለመጠገን 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ተመድቦ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው የእሳት አደጋው በሰው እና በንብረት ላይ ጥፋት በማድረሱ በተቋሙ ሥራ አመራር ስም ሀዘናቸውን ገልፀው መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱም ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ አቶ ሙላት እንዳሉት ሠራተኛው የሚያጋጥሙትን ችግሮች ለመፍታት ተቋሙ ወደፊትም ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ደግሞ ማህበሩ ሠራተኞች አደጋ በገጠማቸው ወቅት ሁሉ ከተቋሙ ሥራ አመራር ጋር በመሆን የመፍትሔ አካል ሲሆን ቆይቷል ብለዋል፡፡ በአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ የተጎዱትን ሠራተኞች ለማቋቋም የተደረገው አፋጣኝ ድጋፍ ምስጋና የሚያስቸረው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ሲወሰድ በነበረው የህግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት ተቋሙ ከ600 እስከ 700 ለሚጠጉ ሠራተኞቹ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በመመደብ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱንም አስታውሰዋል፡፡ በኃይል ማመንጫ ጣቢያው 19 ክፍሎች ባሉት የሠራተኞች መኖሪያ ብሎክ ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉና ከ 3 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙ የሚታወስ ነው፡፡ ተቋሙ ባደረገው እርዳታ ለእያንዳንዱ ተጎጂ እንደየጉዳቱ መጠን ከ13 ሺህ 5 መቶ እስከ 94 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ሚያዝያ 04 ቀን 2013 ዓ.ም.

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ዛሬ ወደ ኃይል ማመንጨት ስራው ተመለሰ .............////.......... ለወራት ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ የቆየው የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ዛሬ ሥራ ጀመረ። የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከብሔራዊ የኃይል ቋት (ግሪድ) ጋር የሚገናኝበት መስመር በመቋረጡ ምክንያት ኃይል ማመንጨት አቁሞ እንደነበር ይታወሳል። ከተከዜ- መቀሌ በተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ሲደረግ የነበረው ጥገና በመጠናቀቁ ዛሬ ቀን ከ 7:18 ሰዓት ጀምሮ በጊዜያዊነት ከሲስተም ጋር ሳይገናኝ ራሱን በራሱ እየተቆጣጠረ (Isolated mode) ኃይል መስጠት ጀምሯል። በአሁኑ ሰዓት ጣቢያው ካሉት አራት ዩኒቶች መካከል በሁለት ዩኒቶች እስከ 108 ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል እየሰጠ ይገኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ካለፈው ሐሙስ ከሰዓት ጀምሮ በትግራይ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ ከተከዜ ኃይል ማመንጫወደ መቀሌ የሚሄደው መስመር ተጠግኖየተከዜ ኃይል ማመንጫ ስራ በመጀመሩ ዳግም አገልግሎት ማግኘት ጀምሯል። ቀደም ሲል ከአላማጣ መኾኒ አሸጎዳ መቀሌ የሚሄደው መስመር ላይ ባጋጠመችግር ምክንያት የትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ነበር። በትግራይ በተካሄደውን የህግ ማስከበር ተከትሎ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የተከዜ ግድብ ደግሞ መንግስት በአውሮፕላን ደብድቦ አፍርሶታል ተብሎ የሀሰት ወሬ ተናፍሶ ነበር። በወቅቱም በግድቡ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰ መግለፃችን ይታወሳል። የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአራት ዩኒቶች 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ባለ ጥምር ቅስት (double arc)ቅርፅ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው። መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content

photo content
+1

በምሰሶዎቹ ላይ ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎች ከሰረቁት ንብረት ጋር እጅ ከፍንጅ እየተያዙ ነው ………….//////………… ከጢስ ዓባይ - ባህርዳር በተዘረጋው ባለ132 ኮሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ምሰሶዎች ላይ ስርቆት የፈፀሙ ሁለት ተጠርጣሪዎች ከሰረቁት ንብረት ጋር በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ህብረተሰቡ ለፀጥታ ኃይሎች በሰጠው ጥቆማ ምሰሶውን በመቆራረጥ በማዳበሪያ ጠቅልለው ከመሸጣቸው በፊት በአማራ ክልል የፀጥታ ኃይሎች የተያዙ ሲሆን ከወንጀሉ ጋር የተገናኙ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ምርመራው መቀጠሉን ለማወቅ ተችሏል። የኢነርጂ አዋጅ 810/2006 አንቀጽ 26 ላይ በኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ ገንዘብ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ አስቀምጧል፡፡ በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 29 ላይ ደግሞ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ማናቸውንም ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ነገር ያስቀመጠ፣ የኤሌክትሪክ እቃ ያስቀመጠ፣ የተከለ፣ የዘረጋ ወይም እንዲተከል እንዲዘረጋ የፈቀደ፣ በኤሌክትሪክ ‹ኢንስታሌሽን› ይዞታ ውስጥ ግንባታ የሚያከናውን፣ የሚያርስ ወይም የሚቆፍር፣ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ወይም የሚያውኩ ግንባታዎችን አላፈርስም፣ ዛፎችን አልቆርጥም ወይም አልመለምልም፣ ሰብሎችን፣ አትክልቶችን ወይም ሌሎች ነገሮችን አላስወግድም ያለ እንደሆነ፤ ማናቸውም የኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ አካላትን ያለያየ፣ የሰረቀ ወይም በማለያየትና በስርቆት የተባበረ እንደሆነ፣ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ሆን ብሎ ወይም በግዴለሽነት ጉዳት በማድረስ ያቋረጠ እንደሆነ፣ እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም ከብር 25 ሺህ ባልበለጠ የገንዘብ መቀጮ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ያስቀምጣል፡፡ በመሆኑም ከዘረፉት ንብረት ጋር እጅ ከፍንጅ በተያዙት ሰዎች ላይ አስተማሪና ተመጣጣኝ ቅጣት እንደሚወሰድና ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊት ፈፃሚዎችን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ የሚያደርግ ቅጣት እንደሚወሰንባቸው ተስፋ እናደርጋለን። በዚህ አጋጣሚ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ በማድረጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል። ምሰሶዎቹ በመዘረፋቸው ተቋሙ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት መዘገባችን ይታወሳል። መጋቢት 25 ቀን 2013 ዓ.ም.

በምሰሶዎቹ ላይ የተፈፀመው ስርቆት ተቋሙን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆነ ኪሳራ ዳርጎታል ………….//////………… በጢስ ዓባይ - ባህርዳር ባለ132 ኮሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶዎች ላይ የ
በምሰሶዎቹ ላይ የተፈፀመው ስርቆት ተቋሙን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆነ ኪሳራ ዳርጎታል ………….//////………… በጢስ ዓባይ - ባህርዳር ባለ132 ኮሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶዎች ላይ የተፈፀመው ስርቆት ተቋሙን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆነ ኪሳራ እንደዳረገው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንደገለፁት የማስተላለፊያ መስመሩ 30 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 91 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች አሉት፡፡ ስርቆቱ የተፈፀመውም በመስመሩ ላይ ካሉት ምሰሰሶዎች መካከል በስምንቱ ላይ እንደነበር መግለፃችን ይታወሳል፡፡ በመስመሩ ላይ በዓመት ሁለት ጊዜ መደበኛ ፍተሻ እንደሚካሄድ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ በህዳር ወር 2013 ዓ.ም ፍተሻ ተካሂዶበት እንደነበርና ምንም ዓይነት ችግር እንዳልነበው አረጋግጠዋል፡፡ በምሰሶዎቹ ላይ በተፈፀመው ስርቆት ተመርቶ ወደ ብሔራዊ ግሪድ መድረስ የነበረበት ኃይልን ጨምሮ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል፡፡ የወደቁትን ምሰሶዎች የመጠገንና ወደነበሩበት የመመለስ ሥራ እየተከናወነ ሲሆን ይህም አሥራ አምስት ቀን ሊፈጅ ይችላል ብለዋል፡፡ ህብረተሰቡ መሰረተ ልማቶችን በባለቤትነት መንፈስ ኢንዲጠብቅና የተለየ ነገር ሲመለከት ለፀጥታ አካላት እንዲያሳውቅ ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ.ም.

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ለማደግ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ ............../////............. በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በምድብ ሀ ተደልድሎ ጨዋታ
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ለማደግ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ ............../////............. በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በምድብ ሀ ተደልድሎ ጨዋታውን በማድረግ ላይ የሚገኘው የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግ ለማደግ ከፍተኛ ፉክክር እያደረገ እንደሚገኝ የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ተናገሩ፡፡ ከመከላከያ፣ ከደሴ ከተማ፣ ከወልድያ ከተማ፣ ከኮምቦልቻ ከተማ፣ ከገላን፣ ከለገጣፎ ለገዳዲ፣ ከፌደራል ፖሊስና ከደብረብርሃን ከነማ ጋር የተደለደለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እስከአሁን ከተካሄዱት 11 ጨዋታዎች 23 ነጥብ በመሰብሰብ ከመከላከያ ክለብ ጋር በእኩል ነጥብ ምድቡን እየመሩት መሆኑን አሰልጣኝ ክፍሌ ገልፀዋል፡፡ የእግር ኳስ ክለቡ የቴክኒክ ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ ወልዴ በበኩላቸው ቡድኑ በአካል ብቃት፣ በሥነልቦና፣ በታክቲክና ቴክኒክ ብቁ ሆኖ ውድድሩን በአንደኛነት እንዲያጠናቅቅ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ አምስት ጨዋታዎች ብቻ የቀሩት የከፍተኛ ሊግ ውድድር ወደ ፕሪሜርሊግ ለማደግ ከፍተኛ ፉክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር በመሆኑ ጨዋታው በተመሳሳይ ሰዓት መካሔድ ሲገባው ሌላን ክለብ ያላግባብ ተጠቃሚ ለማድረግ በሚመስል መልኩ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ክለብ በተደጋጋሚ ቀድሞ እንዲጫወት በመደረጉ አሰራሩ እንዲስተካከል ለውድድር አዘጋጁ አካል ቅሬታ ማቅረቡን ክለቡ አስታውቋል፡፡ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እንደ ፈቃደ ሙለታ፣ዮርዳኖስ ዓባይ፣አንዋር ያሲን፣ አንዋር ሲራጅ፣ ሲሳይ ተሰማ እና ሌሎች ስመጥር ተጨዋቾችን ከራሱ አልፎ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ያፈራ አንጋፋ ክለብ ነው፡፡ መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ/ም

የጢስ ዓባይ ባህር ዳር የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ምሰሶ ስርቆት ተፈፀመበት ............./////............ ከጢስ ዓባይ የውሃ ኃይል ማመንጫ ወደ ባህር ዳር የተዘረጋው ባለ 132 ኮሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ምሰሶ ላይ ስርቆት ተፈፀመ፡፡ ከሰኞ ምሽት ጀምሮ በተፈፀሙ ስርቆቶች ስምንት ምሰሶዎች ወድቀዋል፡፡ ይሁንና በአካባቢው ኃይል እንዳልተቋረጠ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ምሰሶዎቹ በመውደቃቸው ከኃይል ማመንጫው በባህር ዳር ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ይላክ የነበረ እስከ 30 ሜጋ ዋት ኃይል መላክ አልተቻለም፡፡ ችግሩንም በየደረጃው ለሚገኙ የመስተዳድር አካላት እንዲያውቁት የተደረገ ሲሆን የወደቁትን ምሰሶዎች በመጠገን ወደነበሩበት ለመመለስ የጥገና ስራ ተጀምሯል፡፡ መጋቢት 23 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+2

photo content

photo content

photo content

የሥርዓተ -ጾታ እኩልነትን በሁሉም የስራ ክፍሎች ለማስፋፋትና ለመተግበር እየተሰራ ነው ……….////……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሴቶች፣ ህጻናት እና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ የስርዓተ -ጾታ እኩልነትን በሁሉም የኃይል ማመንጫዎች፣ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በሪጅኖች ለማስፋፋት እና ለመተግበር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡ ቢሮው በሥርዓተ-ጾታ ጽንሰ ሃሳብ ዙሪያ ከኃይል ማመንጫ፣ከማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ከሪጅኖች ለተወጣጡ የሴቶች ፣ህጻናት እና ወጣቶች ጉዳይ ተወካዮች በዋናው መስሪያ ቤት አዳራሽ ለሁለት ቀናት የሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና ውይይት ዛሬ ተጠናቋል፡፡ በስልጠናው ላይ የቢሮው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ አደኤ እንደተናገሩት የስልጠናው ዋና ዓላማ የስርዓተ -ጾታ እኩልነትን በማረጋገጥ የሴቶችን ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነት እንዲሁም በህጻናት ደህንነት በሁሉም የስራ ክፍሎች ለማስጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠርነው፡፡ ሠልጣኞች በጽንሰ ሃሰብ እና በልምድ ያዳበሩትን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባቸው ዳይሬክተሯ አስገንዝበዋል ፡፡ በቢሮው የሥርዓተ ጾታ ባለሞያ አቶ ተስፋዩ ዮሀንስ በበኩላቸው ስልጠናው ከቢሮው ጋር በተቀናጀና በተናበበ መልኩ ለመስራት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊዎች በየስራ ክፍላቸው ባሉ የተለያዩ መዋቅሮች በመታቀፍ የሴቶች ፣የህጻናትና ወጣቶች መብትና እና ጥቅማ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ ያግዛቸዋል ብለዋል ፡፡ መጋቢት 17 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content

photo content