ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 533 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 332,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 177

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 533 名订阅者。

根据 05 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 18,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 27.66%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.09% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 297 次浏览,首日通常累积 2 344 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 06 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 533
订阅者
-424 小时
-77
+1830
帖子存档
የቱሉሞዬ ጂኦተርማል ፕሮጀክት የመጀመሪያው ጉድጓድ ቁፋሮ ተጠናቋል ………….////………. በአርሲ ዞን ኢተያ አካባቢ የተጀመረው የቱሉሞዬ የከርሰ ምድር እንፋሎት ኃይል ማመንጫ ግንባታ ፕሮጀክት 150 ሜጋዋት ኃይል ለማግኘት በሁለት ምዕራፎች እየተከናወነ ነው፡፡ የቱሉሞዬ ጂኦተርማል ኢነርጂ የቴክኒክ ኃላፊ ስጉርጉር ጌሪሰን እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ የምትገኝ ሀገር በመሆኗ የእንፋሎት ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል ከፍተኛ እምቅ አቅም አላት፡፡ በቱሉሞዬም እስከ 2000 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚያስችል እምቅ የእንፋሎት ኃይል መኖሩን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በሁለት ምዕራፎች 150 ሜጋዋት ኃይል ለማግኘት 10 የተለያዩ ጉድጓዶች እንደሚቆፈር የገለፁት ኃላፊው ለሥራው የሚያግዙ ሦስት የውሃ ጉድጓዶች ቁፋሮ መጠናቀቁንና አራተኛውም በጅምር ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ሩፋት ማይና በበኩላቸው የመጀመሪያው የኃይል ማመንጫ ጉድጓድ ቁፋሮ ተጠናቆ ወደ ሁለተኛው ቁፋሮ መገባቱን ተናግረዋል፡፡ ወደ መሬት ውስጥ መቆፈር ከሚያስፈልገው 2500 ሜትር ውስጥ አሁን ላይ 1014 ሜትር መቆፈሩንም ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ሲጠናቀቅ ደግሞ ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ባሻገር የተለያዩ የሥራ አማራጮችን መፍጠር እንደሚያስችል ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ በቱሉሞዬ ጂኦተርማል እና በኬንያው ኬንጄን ኩባንያዎች እየተከናወነ የሚገኘው የቱሉሞዬ የከርሰ ምድር እንፋሎት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ በ800 ሚሊዬን ዶላር ወጪ የሚከናወን ሲሆን የግንባታ ሥራውም ሁለት ዓመታትን ይፈጃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 15 ቀን 2013 ዓ.ም

ኢትዮጵያ በቀጣዩ ክረምት ህጋዊና ቴክኒካዊ አካሄዶችን ተከትላ ውሃ ትይዛለች ………./////………. ኢትዮጵያ በቀጣዩ ክረምት ህጋዊና ቴክኒካዊ አካሄዶችን ተከትላ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውሃ እ
ኢትዮጵያ በቀጣዩ ክረምት ህጋዊና ቴክኒካዊ አካሄዶችን ተከትላ ውሃ ትይዛለች ………./////………. ኢትዮጵያ በቀጣዩ ክረምት ህጋዊና ቴክኒካዊ አካሄዶችን ተከትላ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውሃ እንደምትይዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አረጋገጡ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ዓባይን አልገደበም፤ ወደፊትም አይገድብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ የወንዙ ተፈጥሮኣዊ ፍሰት ሳይቋረጥ በክረምት ወራት ከፍተኛ ዝናብ ስለሚዘንብ ዘንድሮም ውሃውን እንይዛለን ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለፁት በክረምት ወራት ውሃውን ሳይሞሉ ማለፍ ሀገሪቱን አንድ ቢሊዮን ዶላር ሀገሪቱን ያሳጣታል፡፡ የኢትዮጵያ ፍላጎት ግብፅና ሱዳንን መጉዳት ሳይሆን በወንዙ በመጠቀም ከጭለማ መውጣት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡ የውሃ አሞላሉን በተመለከተም ኢትዮጵያ ዛሬም ቢሆን ድርድሩን ለመፈረም ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለኢትዮጵያ ህዝብ በገባነው ቃል መሰረት እናሳካዋለን ሲሉ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 14 ቀን 2013 ዓ.ም

ሳሊኒ ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ ካሳ ጠይቆ ነበር ………./////………. የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ተቋራጭ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት ፕሮጀክቱ በመዘግየቱ ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ ካሳ መጠየቁን አስታወቁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለፁት ሳሊኒ ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ ካሳ ጠይቆ የነበረ ቢሆንም ከብዙ ድርድር በኋላ 450 ሚሊየን ዩሮ ለመክፈል ከስምምነት ተደርሷል፡፡ ሳሊኒ ያቀረበውን የካሳ ይገባኛል ጥያቄ በድርድር መፍታት ባይቻል ኖሮ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያስቀመጥናቸውን ወሳኝ ምዕራፎች ማሳካት አንችልም ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት እስካሁን ከግድቡ ግንባታ ጋር በተያያዘ ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተገመተ ዕዳ ያጋጠመ ሲሆን ሀገራዊ ለውጡ ከመጣ በኋላ ግን በግድቡ ላይ የአንድ ብር ዕዳ እንኳ እንደሌለ ገልፀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የጨሞጋ የዳ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ወደፊት ሊሰራ የሚችል ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡ የዓባይ ወንዝ ገባር በሆኑት በጨሞጋና የዳ ወንዞች ላይ የተጠናው ፕሮጀክት ትክክለኛ ፕሮጀክት ነበር ብለዋል፡፡ ይሁንና ብድር ለመስጠት ተስማምቶ የነበረው የቻይና ኤግዚም ባንክ በዓባይ ተፋሰስ ላይ ለሚሰራ ፕሮጀክት ብድር አልሰጥም በማለቱ ምክንያት በፋይናንስ አለመገኘት ፕሮጀክቱ እንዳልቀጠለ ተናግረዋል፡፡ አበዳሪው ባንክ ብድሩን የሚለቅ ከሆነ የጨሞጋ የዳ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት መልሶ ሊቀጥል እንደሚችል የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ የማይሳካ ከሆነ ግን በሌሎች የፋይናንስ አማራጮች ወደፊት የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 14 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

የአሉቶ ጂኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሚያዝያ 10 የጉድጓድ ቁፋሮው ይጀመራል .............../////............. የአሉቶ ላንጋኖ ጂኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሚያዝያ 10 ቀን 2013 ዓ/ም የጉድጓድ ቁፋሮ እንዲጀመር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ አቅጣጫ አስቀመጡ። ለሥራው መጀመር የውሃ አቅርቦት ወሳኝ በመሆኑ ቀሪ ስራዎቹ በፍጥነት እንዲጠናቀቅም ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ንጉሴና ፕሮጀክቱን በፋይናንስ የሚደግፈው የዓለም ባንክ ተወካዮች እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን በስፍራው በመገኘት ገምግመዋል። የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት 7 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ 70 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ይኖረዋል። መጋቢት 13 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+6

የጊንጪ ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተመረቀ ............/////............ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የጊንጪ ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን በዛሬው ዕለት በይፋ መርቀዋል። በምርቃት ሥነ ስርዓቱ ላይ አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው የሚስተዋለውን የኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታትና በአካባቢው ኢንቨስትመንት እንዲስፋፉ ለማድረግ ያግዛል። መንግስት በመላው ኢትዮጵያ የልማት ችግሮችን ለመፍታትና የህብረተሰቡን ኑሮ ለማሻሻል እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በተለያዩ አካባቢዎች የማከፋፈያ ጣቢያዎች ተገንብተው እየተመረቁ መሆናቸውን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ የአካባቢውን ነዋሪዎች በልማቱ ተጠቃሚ ስለሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። ጣቢያው የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አንዱ አካል ለሆነው ለወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የራሱን አስተዋፅዖ ያበረክታል፡፡ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው ማከፋፈያ ጣቢያው እስከ 100 ሜጋ ዋት ኃይል የመሸከም አቅም ያለውና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮችየተገጠሙለት እንዲሁም አስር ባለ15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት ብለዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ለጊንጪ ከተማና አካባቢው ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል አስተማማኝ በሆነ ሁኔታ ከማቅረብ ባለፈ በአካባቢው የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋት ያግዛል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግና የኃይል ተደራሽነት ችግርን ለመፍታት ከተለያዩ የኃይል ምንጮች አስከ 20 ሺህ ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የማከፋፈያ ጣቢያዎች የመነጨውን ኃይል ወደ ውጤት ተጠቃሚው ለማድረስ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ በቀጣይ በሸኮቴ አካባቢ የሚገነባው ማከፋፈያ ጣቢያ የምዕራብ ሸዋን የኃይል ችግር ሙሉ በሙሉ ይፈታል ሲሉ ገልፀዋል። በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጅነር ስለሽ በቀለ ጨምሮ የፌደራልና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ አባ ገዳዎችና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል፡፡ መጋቢት 11 ቀን 2013 ዓ/ም

ተቋሙ ለጥገና ስራ ያወጣ የነበረውን ወጪ የሚታደግ ሥራ እየተሰራ ነው ………….////………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለውሃ ፓምፕ ጥገና ያወጣ የነበረውን ተጨማሪ ወጪ መቀነስ መቻሉን የጢስ አባይ 1 እና 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ጉታ እንዳስታወቁት ኃይል ማመንጫዎች ሲጠቀሙባቸው የነበሩ የውሃ ፓምፖችን ለማስጠገን በጨረታ ለአንድ ፓምፕ 95 ሺህ ብር ዋጋ ቀርቦ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጪ ጣቢያ ሠራተኞች ባደረጉት ጥረት አንዱን ፓምፕ ለመጠገን ሊወጣ በነበረው ገንዘብ መጠን አራቱን መጠገን መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ጣቢያው አብዛኛውን ጊዜ ኃይል የሚያመነጨው ክረምት ላይ በመሆኑ የውሃ ፓምፕ ችግር ይገጥመው እንደነበርና የመለዋወጫ አቅርቦትም በቀላሉ እንደማይገኝ አስታውሰዋል፡፡ የተከናወነው የጥገና ሥራ በጣቢያው የነበረውን የፓምፕ ጥያቄ ከመመለሱ በተጨማሪ አራት ፓምፖችን በመጠገን ለበለስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ደጀኔ ገለፃ በሰከንድ 250 ሺህ ሊትር የተጠራቀመ ውሃ የመሳብ አቅም ያለው ፓምፕ የጥገና ሥራም ተከናውናል፡፡ ይህንን ለማሰራት 150 ሺህ ብር ይጠይቅ እንደነበር የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ በጣቢያው ሠራተኞች ያለምንም ወጪ የጥገና ስራው ተጠናቋል ብለዋል፡፡ የተከናወነው የጥገና ሥራ የጣቢያውን የፓምፕ ችግር ከመቅረፍ ባለፈ ፓምፖች የሚበላሹበትን ምክንያት በማወቅ ችግሩ በድጋሚ እንዳይከስት ጥንቃቄ ለማድረግ ያግዛል ነው ያሉት፡፡ በጣቢያው ከውሃ ፓምፖች የጥገና ሥራ በተጨማሪ የተርባይኑን አካላት የመጠገን ሥራ ማከናወን መቻሉን አቶ ደጀኔ ተናግረዋል፡፡ አቶ ደጀኔ እንዳሉት የጥገና ሥራው በጣቢያው ባለሙያዎች መሰራቱ የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግሩ በተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ያሳያል፡፡ 73 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ1993 ዓ.ም ነበር አገልግሎት መስጠት የጀመረው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 10 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

photo content

photo content

ክለቡ አምስት ወርቅና ስድስት ነሐስ ሜዳሊያዎች አግኝቷል ............/////............ በ38ኛው የአዲስ አበባ ክለቦች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ አምስት የወርቅና ስድስት ነሐስ ሜዳሊያዎች አገኘ። የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ለማ ደበሌ እንደገለፁት በሴቶች 10 ሺህ ሜትር የዓለም ዘውድ የኋላው ውድድሩን በአንደኝነት ከማጠናቀቋ በተጨማሪ የቦታውን ሪከርድ በመስበር ስታሸንፍ በተመሳሳይ ርቀት የወንዶች ውድድር አየልኝ ተሻገር የወርቅ ሜዳሊያ አግኝቷል። በሴቶች 5 ሺህ ሜትር እርምጃ ውድድር የኋልዬ በቀለ፣ በወንዶች 10 ሺህ ሜትር እርምጃ ዮሐንስ አርጋው፣ በወንዶች አራት መቶ ሜትር ብሩክ ታደሰ እነወዲሁም በወንዶች መቶ ሜትር አትሌቲክስ ናታን አበበ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ አሸንፈዋል። በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ዝናሽ አርጋው፣ በወንዶች መቶ ሜትር አዲሱ ሂሬ እና በወንዶች 10 ሺህ ሜትር እርምጃ መሰረት አየልኝ 3ኛ ደረጃ በመውጣት ለክለቡ የነሐስ ሜዳሊያ አስገኝተዋል። በቀጣዮቹ ቀናትም በተለያዩ ርቀቶች የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌቶች ሜዳሊያ ሊያገኙ የሚችሉባቸው ውድድሮች ይጠበቃሉ። መጋቢት 09 ቀን 2013 ዓ/ም

የጊንጪ ማከፋፈያ ጣቢያ ቅዳሜ በይፋ ይመረቃል ........../////......... የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ የጊንጪ ባለ 230/15 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጎበኙ። ሚኒስትሩ የጎበኙት ማከፋፈያ ጣቢያ ለጊንጪ ከተማና ለአካባቢው ኃይል በአስተማማኝ ሁኔታ ለማቅረብ የሚያስችል ሲሆን 8 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ ተደርጎበታል። የማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ተገጥመውለታል። እስከ 100 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ሲኖረው አስር ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። ግንባታውን ላርሰን ኤንድ ቱርቦ የተባለ የህንድ ኩባኒያ ሲያከናውን ኤም ቪ ቪ ዲከን የተባለ የጀርመንና ስዊዘርላንድ ኩባንያ የማማከር ሥራውን ሰርተዋል። ሐምሌ 2012 ዓ.ም ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነው የጊንጪ ማከፋፈያ ጣቢያ ቅዳሜ በይፋ ይመረቃል። መጋቢት 08 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+1

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የኢትዮጵያውያን ህልውና መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሩ ..............///.............. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የኢትዮጵያውያን ህልውና መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ። የግድቡን ግንባታ አስመልክቶ በስካይላይት ሆቴል በተዘጋጀ ሀገር አቀፍ ሲምፓዚየም ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት የዓባይ ተፋሰስ የሃገሪቱን ሁለት ሶስተኛውን የውሃ ተፋሰስ የሚሸፍን በመሆኑ ዓባይን የማልማት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ ነው። ግድቡ መላው ኢትዮጵያውያን አንጡራ ሀብታቸውን ያፈሰሱበት የቀጣይ ልማት የጀርባ አጥንት ሲሉ ገልፀውታል። የግድቡን ግንባታ ለማስተጓጐል በርካታ ዘመቻዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን የገለፁት አቶ ደመቀ ይህን ሴራ ለማክሸፍ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነት ሊቆም ይገባል ብለዋል። የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ፍትሐዊና ምክንያታዊ የጋራ ተጠቃሚነትን እንደምታከብር ተናግረዋል። በቀጣዩ ክረምት ቀጠሮ የተያዘለት ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት በምንም ዓይነት እንደማይራዘም ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ደግሞ የግድቡ የሲቪል ሥራዎች 91 በመቶ እንዲሁም የብረታብረት ሥራዎች 53 ነጥብ 7 በመቶ መከናወናቸውንና አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ 79 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል። የሁለተኛውን ዙር የውሃ ሙሌት ለማሳካትም በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ነው ኢንጂነር ክፍሌ የተናገሩት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሽብር ባልቻ የግድቡን ግንባታ በተያዘለት የጊዜ መርሐ ግብር ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቦርድ አባላት፣ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር÷ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች የግድቡን ግንባታ ከዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በሲምፖዚየሙ ላይ በዓባይ ወንዝ ዙሪያ የተካሄዱ ታሪካዊ፣ ህጋዊ እና ስነ ምህዳራዊ ጥናቶች በተለያዩ ምሁራን በመቅረብ ላይ ነው። መጋቢት 08 ቀን 2013 ዓ/ም