EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 368,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 174 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.86%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.87% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 862 次浏览,首日通常累积 2 620 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
-624 小时
-207 天
+1030 天
帖子存档
15 537
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ደህንነት ለመጠበቅ ችግኞችን መትከል አስፈላጊ ነው
…….....///……….
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ውበት ለመጠበቅ ችግኞችን መትከል ወሳኝ መሆኑን የማዕከላዊ ሪጅን ቁጥር ሦስት የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት ችግኞችን መትከል በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሮአዊ ምክንያቶች የተጎዳን ተፈጥሮ ማከም ነው።
ከታከመ ተፈጥሮ ውስጥ ተስማሚ የሆነ የአየር ንብረት ከመፍጠርም ባሻገር ንፁህ ውሃ ለማግኘት እንደሚረዳም ጠቁመዋል።
ተቋሙ ነገን ዛሬ እንትከል በሚል በሀገርአቀፍ ደረጃ የተከናወነውን የችግኝ ተከላ መርሀግብር በሰበታ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ ማካሄዱ ለመንከባከብ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ነው አቶ ጋሻው የገለፁት።
በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በሙሉ ንፅህና የሚፈልጉ በመሆናቸው ችግኝ መተከል ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ የኮሙዩኒኬሽንና መሰል ዕቃዎች በአቧራ ምክንያት የአገልግሎት ዘመናቸው ስለሚያጥር ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ ችግሩን መቅረፍ ይገባል።
የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች መሰራታቸው ጎርፍ በሚያደርሰው የመሬት መሸርሸር ምክንያት በኃይል ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶዎች፣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ብሬከሮችና ትራንስፎርመሮች እንዲሁም ሌሎች ዕቃዎች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ጉዳቶችን ለመቀነስ እንደሚያስችልም አቶ ጋሻው ገልፀዋል።
ሪጅኑ "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የተካሔደውን የችግር ተከላ መርሃግብር ማስተባበሩ እንዳስደሰታቸውም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ፕሮጀክቱ ከ370 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ለአካባቢው ማህበረሰብ አበርክቷል
………..///……….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ከግንባታ ተቋራጩ ዊ ቢዩልድ ጋር በመገንባት ለአገልግሎት ማብቃቱን በፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች የዕቅድ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ የውሃ፣ የመንገድ፣ የጤና መሰረተ ልማቶችን እና የተለያዩ የአስተዳደር ህንፃዎችን በመገንባት ህብረተሰብ ተጠቃሚ አድርጓል፡፡
ፕሮጀክቱ በሚገነባበት አቅራቢያ የሚገኙትን የባንካ እና ቦከሬ ቀበሌዎችን ከመለኮዛ ወረዳ ጋር የሚያገናኝ መንገድ ባለመኖሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለተለያዩ ችግሮች ሲዳረጉ እንደነበር አቶ ግዛቸው አስታውሰዋል፡፡
ሁለቱን ቀበሌዎች ከወረዳው ጋር የሚያገናኝ የ24 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና የሦስት ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም ቀበሌዎችን ከቀበሌዎችና ወረዳዎች ጋር የሚያገናኝ 85 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የውስጥ ለውስጥና የመዳረሻ መንገዶች ግንባታ በማከናወን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
በአካባቢው የጤና አገልግሎትንና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ተደራሽነትን ለማስፋት ፕሮጀክቱ የድርሻውን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ እስከ አሁንም አምስት የመጠጥ ውሃ ጉድጓዶችን በመቆፈር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ስለመቻሉ ገልፀዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ፕሮጀክቱ የኮይሻ ፊልድ ሆስፒታል የመሬት ዝግጅት አጠቃላይ ሥራ፤ ለሆስፒታሉ የጤና ባለሙያዎች የሚያገለግሉ የመኖሪያ ቤቶችን ግንባታ፤ የኮይሻ ከተማ የአስተዳደር ህንፃና የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲሁም የፖሊስ ጽ/ቤት ግንባታ አከናውኗል።
ከመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች በተጨማሪ በመለኮዛ ወረዳ ለሃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚያገለግል የትራንስፎርመር ግዥ እንዲሁም ለተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት ለግንባታ ሥራ የሚያገለግሉ ግብዓቶች ድጋፍ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
ለአካባቢው ማህበረሰብ የተደረጉ ድጋፎች አጠቃላይ ግምታዊ ወጪያቸው ከ370 ሚሊዮን ብር በላይ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል።
መሠረተ ልማቶቹ በተቋሙ ከመገንባታቸው በፊት በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ የመሰረተ ልማት እጥረት እንደነበር ያነሱት አቶ ግዛቸው በዚህም ህብረተሰቡ ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሲጋለጥ እንደነበር አቶ ግዛቸው አስታውሰዋል፡፡
የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ባከናወናቸው ሥራዎች የህብረተሰቡን ችግሮች ከመቅረፍ ባለፈ የአካባቢው ማህበረሰብ ፕሮጀክቱን በባለቤትነት ስሜት እንዲቀበለው እና አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖረው እያደረገ እንደሆነም አቶ ግዛቸው ተናግረዋል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካሄዱ
........///..........
የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ በመትከል አሳልፈዋል።
የፕሮጀክቱ የአካባቢና ማህበራዊ ዕቅድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለፁት በዕለቱ የምግብነት ጠቀሜታ ያላቸውን የፍራፍሬ ችግኞች መትከል ተችሏል።
ፕሮጀክቱ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከተጀመረበት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የራሱን የችግኝ ማፍያ ጣቢያ በማቋቋም በየዓመቱ በርካታ ችግኞች መትከሉን ተናግረዋል።
እንደ አቶ ግዛቸው ገለፃ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ዛፎችን በመትከል የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር ከመጠበቅ ባሻገር በፕሮጀክት ሳይት የሚገኙ ሠራተኞች ከፍራፍሬ ምርቶች እና ከጓሮ አትክልቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል።
ፕሮጀክቱ በዛሬው ዕለት ከ500 በላይ የአቮካዶ እና የማንጎ ችግኞች መትከሉንም ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት።
በተከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ እና አማካሪ ድርጅት ሠራተኞች በንቃት ተሳትፈዋል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብሩ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ ነው
.........///.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በሰበታ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሐግብር አከናውኗል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በመርሐግብሩ ላይ እንደገለፁት የችግኝ ተከላው የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ ፋይዳው የጎላ ነው።
የችግኝ ተከላው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ከደለል ለመከላከል እንደሚያግዝም ተናግረዋል።
የተቋሙ የሰው ኃይል ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ፣ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ፣ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ የችግኝ ተከላውን ጠቀሜታ በተመለከተ አስተያየት ሰጥተዋል።
ሥራ አስፈፃሚዎቹ እንዳሉት ተቋሙ የሚያከናውናቸው ተግባራት ሀገሪቱ ለቀረፀችው የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ አጋዦች ናቸው።
የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብሩ ተቋሙ ለሀገር ዕድገትና ለአህጉራዊ ትስስር መሰረት የሚሆን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያግዘው ተናግረዋል።
እንደ ሥራ አስፈፃሚዎቹ ገለፃ የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ ተቋሙ ግንባር ቀደም ሚና ይጫወታል።
የተቋሙ የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው የተቋሙ ሠራተኞች በሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ሠራተኛው ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ ሥራዎችን በስፋት እንዲያከናውንም ጥሪ አቅርበዋል።
በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችም ተቋሙንና ሀገርን በሚለውጥ መርሐግብር ላይ በመሳተፋቸው መደሰታቸውን ገልፀው የተከሏቸውን ችግኞች እንደሚንከባከቡ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያን አረንጓዴ ለማልበስ ያለመ የአንድ ጀምበር የ500 ሚሊዮን የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ በመካሔድ ላይ ይገኛል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል
.........///.........
በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ለተያዘው ዕቅድ አካል የሆነው የችግኝ ተከላ መርሐግብር በታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዙሪያ መካሄዱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ።
ሥራ አስኪያጁ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ እንደገለፁት በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞች እንዲሁም በፕሮጀክቱ የደህንነት ጥበቃ ላይ የተሰማሩ የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ተሳትፈዋል።
በፕሮጀክቱ ዙሪያ የሚካሄደው የችግኝ ተከላ ሥራ ግድቡን ከደለል በመከላከል ኃይል የሚያመነጭበትን እድሜ ለማራዘም እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የችግኝ ተከላ ሥራው የሀገሪቱን የዝናብ ሁኔታ የተስተካከለ ለማድረግና የደን ሽፋኑን ቀድሞ ወደነበረበት ለመመለስ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱ ዙሪያ ከዚህ በፊት የችግኝ ተከላ ሥራ ሲከናወን እንደነበር አስታውሰው በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
የግድቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ህብረተሰቡ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥ ኢንጅነር ክፍሌ ጥሪ አቅርበዋል።
በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት የፕሮጀክቱ ሠራተኛ አቶ ያሬድ ግርማ በበኩላቸው ዓለም ዐይኑን ገልጦ በሚመለከተው ሀገራዊ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ላይ ከመሳተፋቸው ጎን ለጎን በሀገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ መሳተፋቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል።
የተከላ ሥራው በግድቡ ዙሪያ መከናወኑ በተፋሰሱ ላይ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና የዝናብ መጠንን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
የዊ ቢውልድ/ሳሊኒ/ ኩባንያ ሠራተኞች ማህበር ተወካይ አቶ ሞገስ የሺዋስ በበኩላቸው በችግኝ ተከላ ሥራው ላይ የኩባንያው ሠራተኞች እየተሳተፉ እንደሚገኙ በመግለፅ በቀጣይ ከፕሮጀክት ቢሮው ጋር በመተባበር ሠራተኞች በችግኝ ተከላ ሥራ ላይ እንዲሳተፉ በትኩረት ተናግረዋል።
በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉት በሀገር መከላከያ ሠራዊት የ20ኛ ክፍለ ጦር አባል የሆኑት መቶ አለቃ ድረስ ያለውና የፌደራል ፖሊስ አባል የሆኑት ኮማንደር ጀማል አደም በበኩላቸው የፕሮጀክቱን ደህንነት ለማስጠበቅ እየሠሩት ካለው የሠላም ማስከበር ሥራ በተጨማሪ "ኢትዮጵያን እናልብሳት" በሚል ሀገራዊ ጥሪ እየተከናወነ ባለው የችግኝ ተከላ ሥራ ላይ መሳተፋቸው ትልቅ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው ገልፀዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ላይ የሚያደርጉትን ተሳትፎ በቀጣይ አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ጠቁመዋል።
በዕለቱ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ይህም በምግብ ራስን ለመቻል እየተሰራ ያለውን ሥራ በመደገፍ በኩል የራሱን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተመልክቷል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በእንጦጦ አሻራቸውን አኑረዋል
...///…
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በእንጦጦ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ንቅናቄ ላይ አሻራቸውን አኑረዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተጀመረው መርሐግብር ላይ ለገንዘብ ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ ተቋማት አመራሮች በእንጦጦ ችግኝ ተክለዋል።
ኢንጂነር አሸብር እንደገለፁት የችግኝ ተከላ መርሀግብሩ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደግና የአየር ንብረት ተፅዕኖን ከማስቀረት ባለፈ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች የተሻለ ውሃ እንዲይዙ በማድረግ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ያስችላል።
በመሆኑም በሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ በማከፋፈየ ጣቢያዎችና በፕሮጀክቶች አካባቢ ሠራተኞች በችግኝ ተከላው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጥሪ አቅርበዋል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ተቋሙ ኢትዮጵያን አረንጓዴ ለማልበስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እየተሳተፈ ነው
...///…
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢትዮጵያን አረንጓዴ ለማልበስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑን አስታወቀ።
ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል የተያዘውን መርሐግብር በሰበታ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ግቢ ውስጥ አካሂዷል።
"ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በተካሔደው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ላይ የዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች፣ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዳይሬክተሮች፣ የመሠረታዊ ሰራተኛ ማህበር ሊቀመንበር፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ምክትል ሥራ አስኪያጅና ሠራተኞች እንዲሁም የጣቢያው የኦፕሬሽን ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ ዝርዝር ዘገባ ይኖረናል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ከተቋሙ ሠራተኞች ጋር የተካሄደው ውይይት ውጤታማ ነበር ተባለ
..... ....///........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ለሚተገብረው የስትራቴጅክ ዕቅድ ዝግጅት ግብዓት ለመሰብሰብ ከሠራተኞች ጋር የተካሄደው ውይይት ውጤታማ እንደነበር በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ገለፀ።
ዘርፉ የስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅቱ ስለላበት ደረጃ ለተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አባላት ገለፃ አድርጓል።
በኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የፕሮጀክቶች ዕቅድ ክትትልና ዝግጅት ሥራ አሰኪያጅ እና የዕቅድ ዝግጅት ቡድኑ አባል አቶ ቴዎድሮስ ዮሴፍ ዕቅዱን አሳታፊ ለማድረግ ከተቋሙ ሠራተኛ ማህበር ተወካዮች እና ከሠራተኞች ጋር ውይይቶች እንደተካሄዱ አስታውሰው ከውይይቱም ለዕቅዱ ግብዓት የሚሆኑ በርካታ መረጃዎች ተገኝተዋል ብለዋል።
ከውይይቱ የተቋሙን ገቢ ሊያሳድጉ እና የአሰራር ስርዓቱን ሊያዘምኑ የሚችሉ መረጃዎች መሰብሰባቸውንም ለአብነት አንስተዋል ።
እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለፃ ለዕቅድ ዝግጅቱ የሌሎች ተቋማት እና በኃይል ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የተለያዩ ሀገራት ኩባንያዎች የስትራቴጂክ ዕቅድ፣ የተልዕኮና ራዕይ አቀራረፅ ልምድ ተወስዷል።
የዕቅድ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ከመገባቱ በፊት ከሠራተኛው ጋር ውይይት እንደሚካሄድበትም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በተቋሙ ሲተገበሩ የነበሩ ዕቅዶች ሠራተኛውን ያላሳተፋ እንደነበር አስታውሰዋል።
በአሁኑ የዕቅድ ዝግጅት ላይ ሠራተኛው እንዲሳተፍ መደረጉ ሁሉን አካታች የሆነ ዕቅድ ለመቅረፅ ያግዛል ብለዋል።
የዕቅድ ዝግጅቱ የደረሰበት ሂደት በተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር በየጊዜው እየተገመገመ እንደሆነ ያነሱት ኃላፊዎቹ ለዕቅድ ዝግጅቱ ተፈፃሚነት በየደረጃው የሚገኙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 07 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
