es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 537 suscriptores, ocupando la posición 8 368 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 174 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 537 suscriptores.

Según los últimos datos del 30 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 10, y en las últimas 24 horas de -6, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 24.86%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.87% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 862 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 620 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 537
Suscriptores
-624 horas
-207 días
+1030 días
Archivo de publicaciones
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ደህንነት ለመጠበቅ ችግኞችን መትከል አስፈላጊ ነው …….....///………. የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ውበት ለመጠበቅ ችግኞችን መትከል ወሳኝ መሆኑን የማዕከላዊ ሪጅን ቁጥር ሦስት የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት ችግኞችን መትከል በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሮአዊ ምክንያቶች የተጎዳን ተፈጥሮ ማከም ነው። ከታከመ ተፈጥሮ ውስጥ ተስማሚ የሆነ የአየር ንብረት ከመፍጠርም ባሻገር ንፁህ ውሃ ለማግኘት እንደሚረዳም ጠቁመዋል። ተቋሙ ነገን ዛሬ እንትከል በሚል በሀገርአቀፍ ደረጃ የተከናወነውን የችግኝ ተከላ መርሀግብር በሰበታ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ ማካሄዱ ለመንከባከብ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ነው አቶ ጋሻው የገለፁት። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በሙሉ ንፅህና የሚፈልጉ በመሆናቸው ችግኝ መተከል ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ የኮሙዩኒኬሽንና መሰል ዕቃዎች በአቧራ ምክንያት የአገልግሎት ዘመናቸው ስለሚያጥር ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ ችግሩን መቅረፍ ይገባል። የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች መሰራታቸው ጎርፍ በሚያደርሰው የመሬት መሸርሸር ምክንያት በኃይል ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶዎች፣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ብሬከሮችና ትራንስፎርመሮች እንዲሁም ሌሎች ዕቃዎች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ጉዳቶችን ለመቀነስ እንደሚያስችልም አቶ ጋሻው ገልፀዋል። ሪጅኑ "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የተካሔደውን የችግር ተከላ መርሃግብር ማስተባበሩ እንዳስደሰታቸውም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ፕሮጀክቱ ከ370 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ለአካባቢው ማህበረሰብ አበርክቷል ………..///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ከግንባታ ተቋራጩ ዊ ቢዩልድ ጋር በመገንባት ለአገልግሎት ማብቃቱን በፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች የዕቅድ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ የውሃ፣ የመንገድ፣ የጤና መሰረተ ልማቶችን እና የተለያዩ የአስተዳደር ህንፃዎችን በመገንባት ህብረተሰብ ተጠቃሚ አድርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ በሚገነባበት አቅራቢያ የሚገኙትን የባንካ እና ቦከሬ ቀበሌዎችን ከመለኮዛ ወረዳ ጋር የሚያገናኝ መንገድ ባለመኖሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለተለያዩ ችግሮች ሲዳረጉ እንደነበር አቶ ግዛቸው አስታውሰዋል፡፡ ሁለቱን ቀበሌዎች ከወረዳው ጋር የሚያገናኝ የ24 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና የሦስት ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም ቀበሌዎችን ከቀበሌዎችና ወረዳዎች ጋር የሚያገናኝ 85 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የውስጥ ለውስጥና የመዳረሻ መንገዶች ግንባታ በማከናወን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። በአካባቢው የጤና አገልግሎትንና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ተደራሽነትን ለማስፋት ፕሮጀክቱ የድርሻውን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ እስከ አሁንም አምስት የመጠጥ ውሃ ጉድጓዶችን በመቆፈር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ስለመቻሉ ገልፀዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ፕሮጀክቱ የኮይሻ ፊልድ ሆስፒታል የመሬት ዝግጅት አጠቃላይ ሥራ፤ ለሆስፒታሉ የጤና ባለሙያዎች የሚያገለግሉ የመኖሪያ ቤቶችን ግንባታ፤ የኮይሻ ከተማ የአስተዳደር ህንፃና የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲሁም የፖሊስ ጽ/ቤት ግንባታ አከናውኗል። ከመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች በተጨማሪ በመለኮዛ ወረዳ ለሃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚያገለግል የትራንስፎርመር ግዥ እንዲሁም ለተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት ለግንባታ ሥራ የሚያገለግሉ ግብዓቶች ድጋፍ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡ ለአካባቢው ማህበረሰብ የተደረጉ ድጋፎች አጠቃላይ ግምታዊ ወጪያቸው ከ370 ሚሊዮን ብር በላይ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል። መሠረተ ልማቶቹ በተቋሙ ከመገንባታቸው በፊት በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ የመሰረተ ልማት እጥረት እንደነበር ያነሱት አቶ ግዛቸው በዚህም ህብረተሰቡ ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሲጋለጥ እንደነበር አቶ ግዛቸው አስታውሰዋል፡፡ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ባከናወናቸው ሥራዎች የህብረተሰቡን ችግሮች ከመቅረፍ ባለፈ የአካባቢው ማህበረሰብ ፕሮጀክቱን በባለቤትነት ስሜት እንዲቀበለው እና አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖረው እያደረገ እንደሆነም አቶ ግዛቸው ተናግረዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካሄዱ ........///.......... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ በመትከል አሳልፈዋል። የፕሮጀክቱ የአካባቢና ማህበራዊ ዕቅድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለፁት በዕለቱ የምግብነት ጠቀሜታ ያላቸውን የፍራፍሬ ችግኞች መትከል ተችሏል። ፕሮጀክቱ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከተጀመረበት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የራሱን የችግኝ ማፍያ ጣቢያ በማቋቋም በየዓመቱ በርካታ ችግኞች መትከሉን ተናግረዋል። እንደ አቶ ግዛቸው ገለፃ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ዛፎችን በመትከል የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር  ከመጠበቅ ባሻገር በፕሮጀክት ሳይት የሚገኙ ሠራተኞች ከፍራፍሬ ምርቶች እና ከጓሮ አትክልቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። ፕሮጀክቱ በዛሬው ዕለት ከ500 በላይ የአቮካዶ እና የማንጎ ችግኞች መትከሉንም ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። በተከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ እና አማካሪ ድርጅት ሠራተኞች በንቃት ተሳትፈዋል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+4

photo content
+9

የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብሩ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ ነው .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በሰበታ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሐግብር አከናውኗል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በመርሐግብሩ ላይ እንደገለፁት የችግኝ ተከላው የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ ፋይዳው የጎላ ነው። የችግኝ ተከላው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ከደለል ለመከላከል እንደሚያግዝም ተናግረዋል። የተቋሙ የሰው ኃይል ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ፣ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ፣ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ የችግኝ ተከላውን ጠቀሜታ በተመለከተ አስተያየት ሰጥተዋል። ሥራ አስፈፃሚዎቹ  እንዳሉት ተቋሙ የሚያከናውናቸው ተግባራት ሀገሪቱ ለቀረፀችው የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ አጋዦች ናቸው። የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብሩ ተቋሙ ለሀገር ዕድገትና ለአህጉራዊ ትስስር መሰረት የሚሆን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያግዘው ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚዎቹ ገለፃ የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ ተቋሙ ግንባር ቀደም ሚና ይጫወታል። የተቋሙ የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው የተቋሙ ሠራተኞች በሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።    ሠራተኛው ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ  ሥራዎችን በስፋት እንዲያከናውንም ጥሪ አቅርበዋል። በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችም ተቋሙንና ሀገርን በሚለውጥ መርሐግብር ላይ በመሳተፋቸው መደሰታቸውን ገልፀው የተከሏቸውን ችግኞች እንደሚንከባከቡ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያን አረንጓዴ ለማልበስ ያለመ የአንድ ጀምበር የ500 ሚሊዮን የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ በመካሔድ ላይ ይገኛል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል .........///......... በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ለተያዘው ዕቅድ አካል የሆነው የችግኝ ተከላ መርሐግብር በታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዙሪያ መካሄዱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ እንደገለፁት በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞች እንዲሁም በፕሮጀክቱ የደህንነት ጥበቃ ላይ የተሰማሩ የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ተሳትፈዋል። በፕሮጀክቱ ዙሪያ የሚካሄደው የችግኝ ተከላ ሥራ ግድቡን ከደለል በመከላከል ኃይል የሚያመነጭበትን እድሜ ለማራዘም እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የችግኝ ተከላ ሥራው የሀገሪቱን የዝናብ ሁኔታ የተስተካከለ ለማድረግና የደን ሽፋኑን ቀድሞ ወደነበረበት ለመመለስ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። በፕሮጀክቱ ዙሪያ ከዚህ በፊት የችግኝ ተከላ ሥራ ሲከናወን እንደነበር አስታውሰው በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የግድቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ህብረተሰቡ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥ ኢንጅነር ክፍሌ ጥሪ አቅርበዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት የፕሮጀክቱ ሠራተኛ አቶ ያሬድ ግርማ በበኩላቸው ዓለም ዐይኑን ገልጦ በሚመለከተው ሀገራዊ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ላይ ከመሳተፋቸው ጎን ለጎን በሀገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ መሳተፋቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል። የተከላ ሥራው በግድቡ ዙሪያ መከናወኑ በተፋሰሱ ላይ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና የዝናብ መጠንን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። የዊ ቢውልድ/ሳሊኒ/ ኩባንያ ሠራተኞች ማህበር ተወካይ አቶ ሞገስ የሺዋስ በበኩላቸው በችግኝ ተከላ ሥራው ላይ የኩባንያው ሠራተኞች እየተሳተፉ እንደሚገኙ በመግለፅ በቀጣይ ከፕሮጀክት ቢሮው ጋር በመተባበር ሠራተኞች በችግኝ ተከላ ሥራ ላይ እንዲሳተፉ በትኩረት ተናግረዋል። በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉት በሀገር መከላከያ ሠራዊት የ20ኛ ክፍለ ጦር አባል የሆኑት መቶ አለቃ ድረስ ያለውና የፌደራል ፖሊስ አባል የሆኑት ኮማንደር ጀማል አደም በበኩላቸው የፕሮጀክቱን ደህንነት ለማስጠበቅ እየሠሩት ካለው የሠላም ማስከበር ሥራ በተጨማሪ "ኢትዮጵያን እናልብሳት" በሚል ሀገራዊ ጥሪ እየተከናወነ ባለው የችግኝ ተከላ ሥራ ላይ መሳተፋቸው ትልቅ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው ገልፀዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ላይ የሚያደርጉትን ተሳትፎ  በቀጣይ አጠናክረው እንደሚቀጥሉም  ጠቁመዋል። በዕለቱ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ይህም በምግብ ራስን ለመቻል እየተሰራ ያለውን ሥራ በመደገፍ በኩል የራሱን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተመልክቷል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በእንጦጦ አሻራቸውን አኑረዋል ...///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በእንጦጦ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ንቅናቄ ላይ አሻራቸውን አኑረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተጀመረው መርሐግብር ላይ ለገንዘብ ሚኒስቴር ተጠሪ  የሆኑ ተቋማት አመራሮች በእንጦጦ ችግኝ ተክለዋል። ኢንጂነር አሸብር እንደገለፁት የችግኝ ተከላ መርሀግብሩ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደግና የአየር ንብረት ተፅዕኖን ከማስቀረት ባለፈ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች የተሻለ ውሃ እንዲይዙ በማድረግ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ያስችላል። በመሆኑም በሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ በማከፋፈየ ጣቢያዎችና  በፕሮጀክቶች አካባቢ ሠራተኞች በችግኝ ተከላው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጥሪ አቅርበዋል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋሙ ኢትዮጵያን አረንጓዴ ለማልበስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እየተሳተፈ ነው ...///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢትዮጵያን አረንጓዴ ለማልበስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑን አስታወቀ። ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል የተያዘውን መርሐግብር በሰበታ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ግቢ ውስጥ አካሂዷል። "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በተካሔደው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ላይ የዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች፣ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዳይሬክተሮች፣ የመሠረታዊ ሰራተኛ ማህበር ሊቀመንበር፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ምክትል ሥራ አስኪያጅና ሠራተኞች እንዲሁም የጣቢያው የኦፕሬሽን ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ዝርዝር ዘገባ ይኖረናል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

ከተቋሙ ሠራተኞች ጋር የተካሄደው ውይይት ውጤታማ ነበር ተባለ ..... ....///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ለሚተገብረው የስትራቴጅክ ዕቅድ ዝግጅት ግብዓት ለመሰብሰብ ከሠራተኞች ጋር የተካሄደው ውይይት ውጤታማ እንደነበር በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ገለፀ። ዘርፉ የስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅቱ ስለላበት ደረጃ ለተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አባላት ገለፃ አድርጓል። በኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የፕሮጀክቶች ዕቅድ ክትትልና ዝግጅት ሥራ አሰኪያጅ እና የዕቅድ ዝግጅት ቡድኑ አባል አቶ ቴዎድሮስ ዮሴፍ  ዕቅዱን አሳታፊ ለማድረግ ከተቋሙ ሠራተኛ ማህበር ተወካዮች እና ከሠራተኞች ጋር  ውይይቶች እንደተካሄዱ አስታውሰው  ከውይይቱም ለዕቅዱ ግብዓት የሚሆኑ በርካታ መረጃዎች ተገኝተዋል ብለዋል። ከውይይቱ የተቋሙን ገቢ ሊያሳድጉ እና የአሰራር ስርዓቱን ሊያዘምኑ የሚችሉ መረጃዎች መሰብሰባቸውንም ለአብነት አንስተዋል ። እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለፃ ለዕቅድ ዝግጅቱ የሌሎች ተቋማት እና በኃይል ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የተለያዩ ሀገራት ኩባንያዎች የስትራቴጂክ ዕቅድ፣ የተልዕኮና ራዕይ አቀራረፅ ልምድ ተወስዷል። የዕቅድ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ከመገባቱ በፊት ከሠራተኛው ጋር ውይይት እንደሚካሄድበትም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በተቋሙ ሲተገበሩ የነበሩ ዕቅዶች ሠራተኛውን ያላሳተፋ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ የዕቅድ ዝግጅት ላይ ሠራተኛው እንዲሳተፍ መደረጉ ሁሉን አካታች የሆነ ዕቅድ ለመቅረፅ ያግዛል ብለዋል። የዕቅድ ዝግጅቱ የደረሰበት ሂደት በተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር በየጊዜው እየተገመገመ እንደሆነ ያነሱት ኃላፊዎቹ ለዕቅድ ዝግጅቱ ተፈፃሚነት በየደረጃው የሚገኙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 07 ቀን 2015 ዓ.ም