EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 368,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 174 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.86%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.87% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 862 次浏览,首日通常累积 2 620 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
-624 小时
-207 天
+1030 天
帖子存档
15 537
ማህበሩ ለሁለት ቀናት ሲያካሄድ የቆየውን ጉባኤ አጠናቀቀ
.........///...........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ምክር ቤት ሐምሌ ለሁለት ቀናት ያካሄደውን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ አጠናቋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ከሠራተኞች ደህንነት ጥበቃ፣ ከሠራተኛ ዕድገት ፈተና አዘገጃጀትና የፈተና ቋት አተገባበር፣ ከዕድገት፣ ከደመወዝና ከጥቅማ ጥቅም ፣ከሠራተኞች ደንብ ልብስና የሥራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ ግብዓት አቅርቦት እንዲሁም ሌሎች አስተዳደራዊ ከሆኑ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ሊፈቱ ይገባል ያሏቸውን ጥያቄዎች በማንሳት የተቋሙ ሥራ አመራር ችግሮችን ለመቅረፍ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራም ጠይቀዋል፡፡
በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ በሠጡበት ወቅት እንደገለፁት የደመወዝ፣ የአበልና ሌሎች የጥቅማ ጥቅሞ ጥያቄዎች የተቋሙን የፋይናንስ አቅምና የኑሮ ውድነቱን ባገናዘበ መልኩ የሚፈቱ ይሆናል።
የሠራተኞችን ደህንነት ለመጠበቅ ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ይህም በቀጣይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በሠራተኛው የሚነሱ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እንደሚመለሱ እና ተቋሙን የሚመጥን የሠራተኞች ደንብ ልብስ በአዲሱ በጀት ዓመት ለማቅረብ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ተቋሙ ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበትም አሳስበዋል።
በተቋሙ የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው ከዕድገት፣ ከሥራ ከፈፃፀም ምዘና፣ ከደንብ ልብስና ከሥራ ላይ የደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎች አቅርቦት እና ከሌሎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ሥራ አስፈፃሚው በምላሻቸው በህብረት ሥምምነቱ ላይ የተካተቱ የደንብ ልብሶችን ለሠራተኞች ለማቅረብ ልብሶቹ ገበያ ላይ በቀላሉ አለመገኘታቸው ፈተና እንደሆነ ተናግረዋል።
ከሰው ኃይል አስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ያነሱት አቶ አታላይ እያንዳንዱ የሥራ መሪና ሠራተኛ ለተቋሙ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት መስራት እንዲሰራም ጥሪ አቅርበዋል።
የማህበሩ ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል፡፡
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 07 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ ኃይል በቧንቧ ሠራተኛ የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ግንቦት 11 ቀን 2015 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሠረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ በዋናው መ/ቤት 20ኛ ፎቅ የጽሑፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
15 537
ማህበሩ በበጀት ዓመቱ የሠራተኛውን መብትና ጥቅሞች የሚያስከብሩ ተግባራት ላይ ትኩረት ማድረጉን ገለፀ
...///...
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር በ2015 በጀት ዓመት የሠራተኛውን መብትና ጥቅሞች የሚያስከብሩ ተግባራት ላይ ትኩረት ማድረጉን ገለፀ።
ማህበሩ 9ኛ ጠቅላላ መደበኛ ጉባዔውን ከተቋሙ የሥራ ዘርፍ ማህበራት ተወካዮች ጋር ማካሔድ ጀምሯል።
የተቋሙ የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ የማህበሩን ዓመታዊ ሪፖርት ሲያቀርቡ እንደገለፁት ከ2015 በጀት ዓመት ጀምሮ የዓመታዊ የደመወዝ ጭማሪና የተለያዩ ጥቅማጥቅሞች በሠራተኛው የሥራ አፈፃፀም ላይ የሚወሰን ይሆናል።
ማህበሩ የገንዘብ አቅሙን ለማሳደግ የተለያዩ ባንኮችን አወዳድሮ በጊዜ ገደብ ተቀማጭ ከፍተኛ ገቢ እንዳገኘ የገለፁት አቶ መኮንን በዚህም ለጡረተኛ የሚሰጠውን ድጎማ ከፍ ማድረጉን ተናግረዋል።
በተቋሙ የትምህርት ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት እና በትምህርትና ሥልጠና አፈፃፀም መመሪያ መሠረት በየዓመቱ 55 ሴት ሠራተኞችን ለማስተማር ከሥምምነት ላይ መደረሱን የተናገሩት ሊቀመንበሩ ሠራተኞችም የዕድሉ ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።
ማህበሩ የኑሮ ውድነቱን ታሳቢ ያደረገ ዓመታዊ የደመወዝ ጭማሪ ድርድርን ጨምሮ የአበልና ሌሎች የሠራተኛውን ጥቅም የሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም አቶ መኮንን ገልፀዋል።
በዋናው መስሪያ ቤት፣ በፕሮጀክቶች፣ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚገኙ ሠራተኞች የሚያቀርቧቸውን ቅሬታዎች ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በጋራ በመነጋገር እንዲፈቱ መደረጋቸውን አመልክተዋል።
ማህበሩ የበረሃ አበል የሌላቸውና ሊሻሻሉ የሚገባቸውን ጥያቄዎች ኮሚቴ በማቋቋም ምላሽ መስጠቱን ያነሱት አቶ መኮንን የመኝታ፣ የምግብና ሌሎች አበሎች ተጠንተው ለቦርድ በማቅረብ ውሳኔ እየተጠበቀ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
እንደ ሊቀመንበሩ ገለፃ በ2016 በጀት ዓመት ጥራት ያላቸውን የደንብና የሥራ ልብሶችና የደህንነት መጠበቂያ ዕቃዎች በወቅቱ ለማቅረብ ታቅዷል።
በሰሜኑ የሀገራችን ጦርነት ሳቢያ ባለፉት ሁለት ዓመታት በማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ያልተሳተፉ የአሸጎዳ እና የተከዜ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የዘርፍ ማህበራት ተወካዮች እየተካሔደ በሚገኘው 9ኛው የምክር ቤት ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ጉባዔው በዛሬው ዕለት የሚቀጥል ሲሆን የተቋሙ ሥራ አስፈፃሚዎች ከዘርፍ የማህበራት ምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጉባዔው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሀገር አቀፍ ማመንጫ፣ የኬሚካልና ማዕድን ሠራተኛ ማህበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ዋና ፀሐፊ አቶ ፀሐዬ አክሎም እንደገለፁት መንግሥት የአሰሪና ሠራተኛ ቦርድ እንደ ሀገር እንዲቋቋም ማድረግ አለበት።
ፌዴሬሽኑ የሠራተኛው ዝቅተኛ የደመወዝ ጣሪያ በአዋጅ ሊደነገግ እንደሚገባም ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ማሳወቁን አቶ ፀሐዬ ተናግረዋል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 06 ቀን 2015 ዓ.ም፣
15 537
የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጠቅላላ ጉባዔውን እያካሄደ ነው
……..///………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር 9ኛ ጠቅላላ መደበኛ ጉባዔውን ከተቋሙ የሥራ ዘርፍ ማህበራት ተወካዮች ጋር በራስ ሆቴል ማካሄድ ጀምሯል።
ማህበሩ ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች እና በማህበሩ የፋይናንስ ሪፖርት ላይ ውይይት እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ምክር ቤቱ የማህበሩን የ2016 በጀት ዓመት የፊዚካል እና የፋይናንስ ዋና ዋና ዕቅዶች ላይም ውይይት በማድረግ ዓመታዊ በጀቱን በማፅደቅ ጉባዔውን ያጠናቅቃል ተብሎ ይጠበቃል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 06 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡
ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የተግባር ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 3 (ሶስት) የስራ ቀናት ውስጥ በዋናው መ/ቤት ሜክሲኮ በሚገኘው ኬኬር ህንጻ 2ኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡
15 537
የኢትዮ - ኬኒያ ማስተላለፊያ መስመር እና ኮንቨርተር ጣቢያ የተገነባበት ቴክኖሎጂ ወጪን ለመቀነስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል
………///………
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል የማስተላለፊያ መስመር እና የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ የግንባታ ወጪ የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎች መጠቀሙን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ።
የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደተናገሩት ከዚህ በፊት በሀገሪቱ የተገነቡ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በተለዋጭ ዥረት (Alternative Current) የቴክኖሎጅ ዓይነት የተገነቡ እንደነበር አስታውሰዋል።
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ስቴሽን የተገነባበት የቴክኖሎጅ ዓይነት ቀጥተኛ ዥረት (Direct Current) መሆኑ ለግንባታ የሚወጣ የኮንዳክተር መጠንና የማከፋፈያ ጣቢያ ብዛት እንዲሁም ሌሎች ግብዓቶችን ለመቀነስ እንዳስቻለ ተናግረዋል።
እንደ አቶ ክብሮም ገለፃ መስመሩ የተገነባበት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ዘዴ በተለዋጭ ዥረት ቢሆን ኖሮ መስመሩ በተዘረጋበት ርዝመት ውስጥ ሦስት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን መገንባት ያስገድድ ነበር።
ይሁንና ኮንቨርተር ጣቢያው በቀጥተኛ ዥረት የማስተለለፊያ ዘዴ መገንባቱ በከፍተኛ ደረጃ የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነትንና መቆራረጥን እንደሚቀንስ አቶ ክብሮም ጠቁመዋል።
ከማከፋፈያ ጣቢያው ወደ ኬኒያ ወጪ መስመር ኃይል ለማስተላለፍ ሦስት አማራጮች እንዳሉት የጠቆሙት ሥራ አስፈፃሚው ይህም አንደኛው አማራጭ የተለያዩ ችግሮች ሲያጋጥሙት በሌላኛው አማራጭ ቀጣይነት ባለው መልኩ ኃይል ለማስተላለፍ ይረዳል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ በቴክኖሎጂ ከዚህ በፊት ከነበሩት በዓይነቱ የተለየ በመሆኑ ለግንባታ ሥራ የሚያስፈልጉ ወጪዎችን መቀነስ እንዳስቻለም ነው አቶ ክብሮም ያስታወቁት።
በወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ስቴሽን ሜካኒካል ኢንጂነር የሆኑት መላኩ አግማስ በበኩላቸው ጣቢያው በአዲስ ቴክኖሎጂ መገንባቱ ችግሮች ሲያጋጥሙ ሰውና ማሽን በማቀናጀት በርቀት አመልካች መሳሪያ አማካኝነት የት ቦታ ላይ ችግሩ እንደተከሰተ በመለየት ለችግሮቹ አፋጣኝ የመፍትሄ እርምጃዎችን ለመውሰድ ያግዛል ብለዋል።
በጣቢያው ላይ የተተከሉ የተለያዩ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ላይ የፍተሻ ሥራዎችን በቀላሉና በወቅቱ በማከናወን የኃይል ማስተላለፍ ሥራው አስተማማኝ እንዲሆን እያገዘ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የኦፕሬሽን ሥራውን የመቆጣጠሩ ሥራ በሦስት ዓይነት አሠራር በቴክኖሎጂ ራስ ሰርነት (automatic)፣ በእጅ ሰርነት (manual) እና መቆጣጠሪያ ክፍል (control room) ውስጥ በመሆን እንደሚከናወን ገልፀው የተገጠሙ ሲስተሞች ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል እና ከኬኒያው ግሪድ ጋር ጤናማ ሆኖ እንዲሰራ እያደረጉ እንደሆነም ነው ባለሙያው የተናገሩት።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል እየፈጠረ ነው
……..///……..
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ስቴሽን ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ዐቢይ አታኩሬ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ ከሚያስገኘው የውጭ ምንዛሪ በተጨማሪ የአካባቢው ህብረተሰብ ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች ምግብ በማዘጋጀትና ለግንባታው አስፈላጊ የሆኑ እንደ አሸዋ፣ ጠጠርና ድንጋይ የመሳሰሉ ግብዓቶችን በማቅረብ የሥራ ዕድሎች ተፈጥረውለታል፡፡
በአሁኑ ወቅትም በጥበቃ፣ በፅዳትና ውበት ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ሥራ አስኪያጁ በመጠቆም ፕሮጀክቱ በአካባቢው ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር በመቀነስ በኩል የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።
ለሀገርና ህዝብ ጥቅም ተብለው በከፍተኛ በጀት የሚገነቡት ፕሮጀክቶች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶች ከማህበረሰቡ ዕይታ ውጭ ስለማይሆኑ ስርቆትን በመከላከል፣ ሌቦችን በመጠቆምና በማጋለጥ ህብረተሰቡ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ አቶ ዐቢይ አሳስበዋል።
የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ማህበራት መካከል “ማስተዋል የጥበቃ እና የጽዳት አገልግሎት ማህበር” ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ተካ አይዛ እንደገለፁት ማህበራቸው ከተቋሙ ጋር ሥምምነት በማድረግ የኮንቨርተር ስቴሽኑን፣ የግራውንድ ኤሌክትሮድ እና የሶዶ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ግቢዎችን የጥበቃ እና የውበት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
በእነዚህ የሥራ ቦታዎች ለ131 የማህበሩ አባላት የሥራ ዕድል መፈጠሩን የጠቆሙት ምክትል ሥራ አስኪያጁ ማህበራቸው ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አረጋገግጠዋል።
የማህበሩ አባል አቶ ዘበነ ቦጋለ በበኩላቸው ማህበሩ በፈጠረላቸው የሥራ ዕድል ተጠቅመው ቤተሰባቸውን ማስተዳደር የሚችሉበት የገቢ አቅም እየፈጠሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም.
15 537
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሰረት ሰኔ 14 ቀን 2015 የጹሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ ለተግባር ፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
15 537
ማህበሩ የፋይናንስ አቅሙን ለማሳደግ የሚረዱ ስትራቴጂያዊ ስልቶች ላይ እንደሚመክር አስታወቀ
………///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር በሐምሌ ወር በሚያካሂደው ዓመታዊ የምክር ቤት ስብሰባ የአባላቱን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ የማህበሩ ሊቀመንበር ገለፁ፡፡
ሊቀመንበሩ አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት ከሁሉም የሥራ ዘርፎች ሠራተኛውን የሚወክሉ የዘርፍ ማህበራት ተወካዮች የሚገኙበት ዓመታዊ የምክር ቤት ጉባዔ ሐምሌ 6 እና 7 ቀን 2015 ዓ.ም በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡
ምክር ቤቱ የማህበሩን የ2015 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም እንደሚገመግም እና የማህበሩን የ2016 በጀት ዓመት የፊዚካል እና የፋይናንስ ዕቅድ ተመልክቶ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ጉባዔው በተለያዩ ምክንያቶች የተጓደሉ የማህበር አመራሮችን በሌሎች እንደሚተካ እና የማህበሩን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ስትራቴጂያዊ ስልቶች ላይ እንደሚመክር አቶ መኮንን ገልፀዋል፡፡
ምክር ቤቱ ተለዋዋጭ ከሆነው ሀገራዊ እና ተቋማዊ ሁኔታ ጋር ሊጣጣሙ የሚገባቸው የመተዳደሪያ ደንቦችን ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ እንደ አዲስ የተቋቋመ ሲሆን ከአራት ሺህ በላይ አባላት አሉት፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ.ም.
15 537
ማስታወቂያ
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. በኤሌክትሮ መካኒክ ቴክኒሽያን አወዳድሮና አሰልጥኖ ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
ስለሆነም የስልጠና ውል የሞላችሁ የስም ዝርዝራችሁ ከታች የተገለፀው አመልካቾች ሐምሌ 03 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ስልጠናው የሚጀመር በመሆኑ ከጠዋቱ 3፡00 ኮተቤ በሚገኘው የሰው ኃይል ስልጠና እና ልማት ቢሮ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
