EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
-724 小时
-77 天
+2630 天
帖子存档
15 538
የሥራ ዘርፉ የመጀመሪያውን የሩብ በጀት ዓመት ግምገማ አካሄደ
..….//……
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ የ2014 በጀት ዓመት የአንደኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማው ውይይት ላለፉት ሁለት ቀናት በአዋሳ ከተማ አካሄደ፡፡
የሥራ ዘርፉን የውጤት ተኮር የሥራ አፈጻጸም ምዘና ስርዓት ትግበራን በተቀናጀ እና በተናበበ መልኩ ለመተግበር ከሪጅን ዳይሬክተሮች እና ከዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የዘርፍን የቁልፍ አፈጻጸም መለኪያ (KPI) ዕቅድ በጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ እንደሆነ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሐብታሙ ውቤ በውይይቱ ላይ ገልፀዋል፡፡
በሩብ ዓመቱም የKPI አፈጻጸም 98.22 በመቶ የደረሰ ሲሆን ከባለፈው ተመሳሳይ የሩብ በጀት ዓመት ከተመዘገበው የ14.02 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተነግሯል፡፡
የግምገማው ዋና ዓላማም በውጤት ተኮር የKPI ምዝና ትግበራ ወቅት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ይበልጥ ለማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ እንዲታረሙ አቅጣጫ የማስቀመጥ፣ የልምድ ልውውጥ እና መልካም ተሞክሮን የማካፍል፣ የተሸለ አፈጻጸም ያመጣውን ሪጀን እውቅና በመስጠት የውድድር ስርዓቱን ይበልጥ የማጠናከር፣ የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲጠናከር ምቹ ሁኔታን መፍጠር እና ማከፍፈያ ጣቢያዎች ላይ የመስክ ምልከታ ጉብኝት ማካሄድ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
ትላንት በተጠናቀቀው እና ለሁለት ቀናት በቆየው ግምገማዊ ውይይት ሪጂኖቹ በቀረቡት ስድስት የKPI መለኪያ ውጤት አንጻር የታየባቸውን ክፍተቶች በግልጽ በመወያያትና በመገማገም የመፍተሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡ በቀጣይም ድክመቶቹ ተስተካክለው እንዲመጡ የጋረ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
በሩብ በጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገበው የደቡብ ምዕራብ ሪጅን እውቅና ተሰጥቷል፡፡
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 03 ቀን 2014 ዓ.ም
Facebook (https://www.facebook.com/Ethioelectric)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
15 538
የሱዳን ኤሌክትሪክ ኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች አዲስ አበባ ገቡ
..........////..........
በሱዳን ኤሌክትሪክ ኩባንያ (ሱዳን ኤሌክትሪክ ትራንስሚሽን ኮርፖሬሽን) ዋና ሥራ አስፈጻሚ የቴክኒክ አማካሪ የተመራ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያና ሱዳን መካከል በቀጣይ ስለሚኖረው የኃይል ትስስር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ጋር ለመደራደር አዲስ አበባ ገብቷል፡፡
በዋና ሥራ አስፈጻሚው የቴክኒክ አማካሪ ሚስተር አህመድ አደም ኡመር የተመራዉና አምስት አባላትን ያካተተው የልዑካን ቡድን ትላንት ምሽት አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስትራቴጂና ኢንቨስትመንት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ተሾመ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡
አቶ ወንድወሰን የልዑካን ቡድኑን በተቀበሉበት ወቅት እንደተናገሩት የልዑካን ቡድኑ አዲስ አበባ የገባው በሁለቱ ሃገራት መካከል የኃይል ትስስሩን ለማጠናከር እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ላይ ድርድር ለማድረግ ነው፡፡
ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በመገኘት ከኩባንያው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ድርድር መካሄዱን አስታውሰዋል፡፡
በአዲስ አበባ የሚካሄደው ድርድር ከዚህ በፊት በነበሩ ድርድሮች የተነሱ ጉዳዮች እልባት እንዲያገኙና በቀጣይ ስለሚኖረው የአሰራር ሁኔታ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል፡፡
ድርድሩ የሱዳን የኤሌክትሪክ ኩባንያ ከኢትዮጵያ ተጨማሪ 1 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ባቀረበው ጥያቄ ላይ እንዲሁም ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ መከናወን ባለበት የመስመር ዝርጋታ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎች ላይ ትኩረት የሚያደርግ እንደሚሆን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
ድርድሩ ከጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣዮቹ አምስት ቀናት የሚካሄድ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ለሱዳን 230 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸጥ ላይ ትገኛለች፡፡ ከሱዳን በተጨማሪም ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸጥ ላይ የምትገኝ ሲሆን ለኬንያ የአሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ እቅድ መያዙ ተጠቁሟል።
በቀጣይ ከሶማሌ ላንድ፣ ከሶማሊያ፣ ከታንዛኒያ፣ ከኤርትራ፣ ከደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ለመፍጠር የሁለትዮሽ ግንኙነት በማድረግ ላይ የምትገኝ መሆኑን ከዚህ በፊት በተለያየ ጊዜ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 01 ቀን 2014 ዓ.ም
15 538
በተቋሙ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ
-----------------------//////-----------------------
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓልን በዋናው መ/ቤት አክብሯል፡፡
የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን “በአዲስ ምዕራፍ በተሟላ ሉዓላዊነት ለሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ዛሬ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
ሰንደቅ ዓላማ የብሔራዊ አንድነት መገለጫ፤ ዜጎች ሀገራዊ ፍቅርና ብሔራዊ ስሜት የሚገልፁበት፤ ታሪካዊ ትስስርና የስነ-ልቦናዊ አንድነት የሚንፀባረቅበት የአንድነትና ህብረት አርማና ምልክት ነው፡፡
የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የውስጥና የውጭ ጠላቶቻችን ብሔራዊ አንድነታችንን እና ሉዓላዊነታችንን እየተፈታተኑ ባሉበት ወቅት መከበሩ ተናበንና ተደራጅተን በተባበረ ክንድ የተጋረጠብንን የህልውና አደጋ ለመመከትና ለመቀልበስ በጋራ በምንቆምበት አጋጣሚ ስለሆነ ልዩ ያደርገዋል፡፡
የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል በየዓመቱ የጥቅምት ወር መጀመሪያ ሰኞ እንዲከበር መወሰኑ ይታወሳል፡፡
ለብሔራዊ አንድነታችንና ሉአላዊነታችን ያለንን ቁርጠኝነት በሰንደቅ ዓላማችን ፊት ዳግም ቃላችንን እናድሳለን!!
ጥቅምት 01 ቀን 2014 ዓ/ም
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
15 538
የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን በራስ አቅም ለመግጠም ታቅዷል
በምዕራብና በሰሜን ሪጅን ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚተከሉ የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን በራስ አቅም ለመግጠም እቅድ መያዙን በተቋሙ ትራንስሚሻን ሰብስቴሽን ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ አስታወቁ፡፡
በሁሉም ሪጅኖች ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል በ130 ጣቢያዎች ላይ የስማርት ሜትር ቆጣሪ ገጠማ ሥራን ለማከናወን “Siemens Proprietary Limited” ከተሰኘ ኩባንያ ጋር ስምምነት በማድረግ ስራው ሲከናወን እንደነበር ሥራ አሰኪያጇ አስታውሰዋል፡፡
ይሁን እንጅ በሁለቱ ሪጅኖች ላይ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ሥራ ተቋራጩ የገጠማ ሥራውን ማከናወን ባለመቻሉ በሪጅኖች የሚተከሉ የቆጣሪ ገጠማ ሥራዎችን በተቋሙ የራስ አቅም ለማከነወን እቅድ ተይዟል ነው ያሉት ኃላፊዋ፡፡
ይህ ሥራ በራስ አቅም እንዲከናወን በተቋሙ ከፍተኛ አመራር በኩል ውሳኔ እንደተሰጠበትም ወ/ሮ ሃይማኖት ተናግረዋል፡፡
እንደ ወ/ሮ ሃይማኖት ገለጻ በሁለቱ ሪጅኖች በሚገኙ 21 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 216 የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን ለመግጠም እቅድ ተይዟል፡፡
ለዚህም ስራውን በተገቢው የኮንትራት አስተዳደር መርህ መሰረት ለማከናወን ከስራ ተቋራጩ ለይ በመውሰድ (de-scope በማድረግ) በተቋሙ የራስ አቅም ለመስራት ባለሞያዎችን የማብቃት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡
ቆጣሪ የመግጠማ ሥራውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን የጠቆሙት ወ/ሮ ሃይማኖት በአካባቢዎች የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር መፍትሄ እንዳገኘ ወደ ስራ እንደሚገባ አስታውቀዋል፡፡
በራስ አቅም ለሚከናወነው ስራም ከ3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ እና 43 ሺህ 1 መቶ የአሜሪካ ዶላር ገንዘብ ከውሉ ላይ ተቀናሽ በማድረግ ለዚህ ስራ በጀት መያዝኑ ነው ስራ አስኪያጇ የተናገሩት፡፡
ስራ ተቋራጩ በ109 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 9 መቶ 92 የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን መግጠም መቻሉን ወ/ሮ ሃይማኖት ገልፀዋል፡፡
አጠቃላይ የገጠማ ስራውን እስከ ታህሳስ 2013 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የተስተዋላው የጸጥታ ችግር፣ የሳይቶቸ በመላው ሀገሪቱ ክፍል ተበታትነው መገኘታቸው እንዲሁም በጉምሩክ በኩል አዳዲስ አሰራሮች በየጊዜው መቀያየራቸው በመርሃ ግብሩ መሰረት ላለመከናወኑ በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡
የቆጣሪ ገጠማ አጠቃላይ ስራውን (Supply, Installation, Test and Commissioning) ለማከናወን በአለም ባንክ የሚሸፈን ከ25 ነጥብ 28 ሚሊዮን በላይ ብር እና ከ2.17 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካ ዶላር በጀት መያዙን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 28 ቀን 2014ዓ.ም
15 538
ማከፋፈያ ጣቢያው የኦፕሬሽን ስራዬ ላይ ተደጋጋሚ እንቅፋት እየገጠመኝ ነው አለ
………/////………
ከደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ወጪ የሆኑት የ33 እና የ15 ኪ ቮልት ማሰራጫ መስመሮች በጣቢያው የዕለት ተዕለት የኦፕሬሽን ስራዎች ላይ እንቅፋት እየፈጠሩ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ይገርማል ዓለሙ አስታወቁ፡፡
እንደ ኃላፊው ገለፃ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የማሰራጫ መስመሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚያጋጥማቸው ችግር እየጨመረ በመምጣቱ በማከፋፈያ ጣቢያው መቆጣጠሪያዎች (Breakers)፣ ትራንስፎርመር እና የኃይል አገናኝ ሽቦዎች feeder power cable) ላይ ጉዳት እያደረሱ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተፈራረሙት የሰርቪስ ሌቭል ስምምነት መመሪያ ክፍል ሁለት (1) ላይ እንደተመለከተው መስመሮቹ በሚቋረጡበት ጊዜ የሚደረገው ፍተሻ በብሬከር መሆን የለበትም፡፡
ብልሽቱ የግድ በብሬከር የሚፈተሸ ከሆነም በ24 ሰዓት ውስጥ ከሁለት ጊዜ በላይ እንዲሁም በአንድ ወር ውስጥ ከ25 ጊዜ በላይ እንዳይሞከር በግልፅ የተቀመጠ ቢሆንም ከስምምነቱ ውጭ በቀን እስከ ስምንት ጊዜ ብሬከር የሚሞከርበት ጊዜ እንዳለ አቶ ይገርማል ጠቁመዋል፡፡
ኃላፊው እንደሚሉት ከማከፋፈያ ጣቢያው በአንድ ምሶሶ የሚወጡ ሁለት ባለ 15 ኪሎ ቮልት የማሰራጫ መስመሮች ለሁለቱ ተቋማት አለመግባባት ዋነኛ ምክንያቶች ከመሆናቸው ባለፈ መስመሮቹ በተደጋጋሚ እንዲቋረጡና የጣቢያው የኦፕሬሽን ስራዎች እንዲስተጓጎል ምክንያት ሆኗል፡፡
ዲስትሪክቱ ተጨማሪ ኃይል ለመጫን ሲፈልግ የጭነት ፍላጎቱንና የማሳወቅና የማከፋፈያ ጣቢያውን የኃይል አቅርቦት አቅም የመጠየቅ ግዴታ ያለበት ቢሆንም ይህን ሳያደርግ በራሱ ፈቃድ በፈለገበት ጊዜ ተጨማሪ ኃይል መጫኑ በጣቢው ሥራ ላይ ጫና እየፈጠረ ነው ብለዋል፡፡
ከዚህ በፊት ከ285 አምፔር በላይ ኃይል ጭኖ የማያውቀው መስመር ከጣቢያው ዕውቅና ውጭ በአንድ ቀን ተጨማሪ 40 አምፔር የተጫነበት ጊዜ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡
ችግሩን ለአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደብረ ማርቆስ ዲስትሪክት በተደጋጋሚ የማሳወቅ ስራ ቢሰራም እስከአሁን መፍትሄ እንዳልተሰጠው ተናግረዋል፡፡
ዲስትሪክቱ ማሰራጫ መስመሮችን እንዲያስተካክል በተደጋጋሚ ቢገለጽለትም ችግሮችን በወቅቱ ከመፍታት ይልቅ ወደ ጣቢያዉ የሚገፋበት ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል የጣቢያው ኃላፊ፡፡
የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እነዚህና ሌሎች ያልጠቀሱ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ገልፀው ከአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎች ጋር ለመነጋገርና ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 28 ቀን 2014
15 538
የጣቢያውን ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት የሚቀርፍ ግንባታ እየተከናወነ ነው
……..///……….
በጊቤ 2ኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተጀመረው የሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሲጠናቀቅ ያለውን የመኖርያ ቤት ችግር ሙሉ በሙሉ እንደሚቀርፍ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 2ኛ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ብርሃኑ ደበላ እንደገለፁት በሚያዚያ ወር 2013 ዓ.ም የተጀመረው የመኖሪያ ቤት ግንባታ አፈጻጸሙ 18 በመቶ ደርሷል፡፡
ግንባታውን በ18 ወራት ውስጥ ሰርቶ ለማጠናቀቅ የታቀደ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ የዕቃ አቅርቦት፣ የተዳፋት ግንባታ አቃፊ ሥራዎች፣ መሰረት የማውጣትና የኮንክሪት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው ብለዋል፡፡
በቀጣይም ቀሪ የቁፋሮ እና የመሰረት ሥራዎችን አጠናቆ ግንባታውን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ለመጨረስ የሲሚንቶ አቅርቦት ችግር እንዳይሆን ከወዲሁ ለማሟላት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ተቋራጭ የሳይት ስራ አስኪጅ አቶ አዲስ ፈንታ በበኩላቸው ፕሮጅክቱ ላይ የአናፂና የግንብ ሥራ ባለሙያና የጉልበት ሰራተኛ እጥረት ችግር ቢኖርም ከተቋሙ ጋር በተገባው ውል መሰረት ግንባታውን ሰርቶ ለማስረከብ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ከመኖሪያ ቤት በተጨማሪ የቢሮ፣ የስፖርት መዝናኛ ማዕከል፣ የክሊኒክ እና የትምህርት ቤት ግንባታም ያካተተ ሲሆን ለግንባታው 380 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ተመድቦለታል፡፡
የፕሮጀክቱን ግንባታ ዓይናለም ጋሻው እና ሉሲ ኢንጅነሪንግ የተባሉ የሀገር ውስጥ ተቋራጮች እያከናወኑት ሲሆን ፕሮጀክቱ 100 ለሚሆኑ የአካባቢው ወጣቶች ጊዚያዊ የሥራ እድል ፈጥሯል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 27 ቀን 2013
15 538
በበጀት ዓመቱ 28 የቴክኒክ እና የፋይናንስ ኦዲቶችን ለማከናወን እቅድ ተይዟል
……….////………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው የበጀት ዓመት 28 ቴክኒካልና የፋይናንስ ኦዲት ምርመራ ለማከናወን አቅዶ እየተሰራ መሆኑን የተቋሙ የውስጥ ኦዲት መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገ/እግዚአብሔር መዝገበ እንዳስታወቁት የኦዲት ምርመራው በተቋሙ ስር የሚገኙ ሁሉንም የስራ ዘርፎችና መምሪያዎችን ባካተተ መልኩ ይካሄዳል፡፡
የኦዲት ምርመራው በተቋሙ ያለውን የስጋት አስተዳደር፣ የመልካም አስተዳደርና የቁጥጥር ስርዓቱ በመፈተሽ ለሚስተዋሉ ክፍተቶች የማሻሻያ ሀሳብ ለማቅረብ እንዲሁም ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን ያቀዳቸውን ተግባራት ከግብ ለማድረስ እንደሚያግዝ ተመላክቷል፡፡
በበጀት ዓመቱ የሂሳብና የቴክኒክ ኦዲት ምርመራ ለማካሔድ የስጋት አባቢዎችን በመለየት፣ ለተቋሙ ያላቸው ፋይዳ እንዲሁም ከዚህ ቀደም የኦዲት ምርመራ ያልተደረገባቸውን ጉዳዮች መነሻ በማድረግ ምርመራ ለማከናወን መታቀዱን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡
የምርመራ ስራዉ የሚሸፍነው ጊዜ እንደ ኦዲት የምርመራ ዓይነቱ የሚለያይ መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ከዚህ ቀደም ኦዲት የተደረገ የስራ ዘርፍ የኦዲት ምርመራው የሸፈነው ጊዜ ያበቃበትን መነሻ በማድረግ የኦዲት ሥራው ይከናወናል ብለዋል፡፡
ከዚህ በፊት ኦዲት ያልተደረጉ ፕሮጀክቶችም ፕሮጀክቶቹ ከተጀመሩበት ጊዜ አንስቶ እንዲሁም በኦፕሬሽንና ሌሎች ዘርፎች ላይ የሚከናወነው የኦዲት ምርመራ ስራ የኦዲት ምርመራው እስከሚሰራበት ጊዜ ድረስ ያለውን እንደሚሸፍን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
ከፋይናንስና የቴክኒክ የኦዲት ምርመራ ስራዎች በተጓዳኝ በበጀት ዓመቱ የአመራሩንና እና የሠራተኞችን ተግባራትና አፈፃፀም ከተቋሙ ፖሊሲ፣ ደረጃ፣ የአፈፃፀም ስርዓት እና ተፈፃሚነት ሊኖራቸው ከሚገቡ ህጎች፣ ፕሮግራሞች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር የተጣጣመ መሆኑን መመርመርና በሚታዩ ክፍተቶች ላይ የማሻሻያ ሃሳቦችን ለማቅረብ እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በበጀት ዓመቱ በተቋሙ የሚፈጸሙ ግዥዎች የድርጅቱን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ መከናወናቸው ይጠናል፡፡
የተቋሙን የጥናት፤ ዲዛይን፣ የፕሮጀክቶች ግንባታ ክትትልና የቁጥጥር ስራዎችን፣ የኃይል ብክነትን ቅነሳ ፍተሻ፣ የመደበኛና የአስቸኳይ ጥገና ስራዎች በተገቢ ሁኔታ መከናወናቸው፤ የገቢ አሰባሰብ እና የወጪ/የክፍያ አስተዳደር ስርዓቱን የማየት እና ወጪን ለመቀነስ በተቋሙ መከናወን ያለባቸው ስራዎች መከናወናቸውንና እና ያስገኙት ዉጤቶችን የመመርመር ስራዎች በበጀት ዓመቱ ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በተጠናቀቀው የ2013 በጀት ዓመት በተመረጡ የስራ ክፍሎች እና ፕሮጀክቶች ላይ 35 የኦዲት ምርመራ ሥራዎች መከናወናቸውንና በተለያዩ ጊዚያት ከተደረጉ የኦዲት ሪፖርቶች መካከል የ66ቱ ሪፖርቶች የግኝት መከታተያ መዘጋጀቱን ዳይሬክተሩ አንስተዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመት ለማከናወን የታቀደውን የኦዲት ስራ በጥራት ለማከናወን የስራ ክፍሉን በሰለጠነና ብቃት ባለው የሰው ኃይል ለማደራጀት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ሁሉም አመራርና ሠራተኛ የኦዲት ምርመራው የሚከናወነው ለተቋሙ ግብ ስኬት መሆኑን ተገንዝቦ ለስራው አስፈላጊ እገዛ እንዲያደርጉ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 26 ቀን 2014 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
